en
Feedback
Bahir Dar | ባህር ዳር

Bahir Dar | ባህር ዳር

Open in Telegram
471
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1230 days
Posts Archive
#አማራ_ባንክ ዲያስፖራ ወገኖቻችንን አሳታፊ ለማድረግ በዳሽን ባንክ፣ በአባይ ባንክ፣ በአቢሲንያ ባንክ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አካውንት ከፍቷል። ትውልደ ኢትዮጵያው
#አማራ_ባንክ ዲያስፖራ ወገኖቻችንን አሳታፊ ለማድረግ በዳሽን ባንክ፣ በአባይ ባንክ፣ በአቢሲንያ ባንክ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አካውንት ከፍቷል። ትውልደ ኢትዮጵያውያን አክሲዮኑን ለመግዛት በተጠንቀቅ ጠብቁ። አክሲዮኑ የሚገዛው በውጭ ምንዛሬ ነው። የባንኩ የመስራች አክሲዮን ሽያጭ እስከ የካቲት 30, 2012 ዓ.ም ድረስ ይቆያል።

የባንኮች የተከፈለ ካፒታል አማራ ባንክ በአሁኑ ሰዓት የተከፈለ ካፒታሉን ከ 4:0 ቢሊዮን ብር በላይ በማድረስ ወደ ስራ ለመግባት በሂደት ላይ ሲሆን ከ80,000 በላይ ባለአክሲዮኖችም ተሳትፈውበታል። እስከ የካቲት 30/2012 ዓ.ም አክሲዮን በመሸጥ ላይ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ይህም የተከፈለ ካፒታል አሁን በስራ ላይ ካሉት የግል ባንኮች ጋር ሲነጻጸር ግዙፍ እና ባለ ቀዳሚ ካፒታል ታሪካዊ ባንክ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ። ለአብነትም በስራ ላይ ያሉት የግል ባንኮች የተከፈለ ካፒታል ከዚህ በታች የተጠቀሰውን ይመስላል። የግል የንግድ ባንኮች የተከፈለ ካፒታል እ.ኤ.አ ሰኔ 30/2019 ላይ /Paid up capital of Ethiopian Private Commercial Banks as of June 30/2019. #አባይ ባንክ አ.ማ 1.67 ቢሊዮን ብር #አቢሲንያ ባንክ አ.ማ 2.81 ቢሊዮን ብር #አዲስ ኢንተርናሽናል 0.83 ቢሊዮን #አዋሽ ባንክ 4.38 ቢሊዮን #ቡና ባንክ 1.77 ቢሊዮን ብር #ብርሃን ባንክ 2.00 ቢሊዮን #ዳሽን ባንክ 2.71 ቢሊዮን ብር #ደቡብ ግሎባል ባንክ 0.72 ቢሊዮን #እናት ባንክ 1.19 ቢሊዮን #አንበሳ ባንክ 1.60 ቢሊዮን #የኦሮሚያ ህብረት ስራ 2.05 ቢሊዮን #ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል 2.40 ቢሊዮን #ህብረት ባንክ 2.26 ቢሊዮን ብር #ወጋገን ባንክ 2.54 ቢሊዮን ብር #ዘመን ባንክ 1.40 ቢሊዮን ብር #ንብ ባንክ 2.1 ቢሊዮን ብር በላይ* *ምንጭ የየባንኮች አመታዊ ሪፓርት #ካፒታል ማለት ለአንድ ድርጅት እጅግ በጣም አስፈላጊ ሲሆን አሁን ባለሁ የካፒታል መጠንም አማራ ባንክ አ.ማ #አለለም ላይ ያለን ዘመናዊ የባንክ ቴክኖሎጅ ለመግዛት፥ የተሻለ የሰው ሀይል ለመቅጠር ፤የተሻለ የስራ ቦታ ለመከራየት እና በአንድ ጊዜ ብዙ ቅርንጫፎችን ለመክፈት ወይም ተደራሽነትን ለማስፋት አቅም ይኖረዋል። በተጨማሪም ብዙ ባለአክሲዮን ማለት መሰረተ ሰፊ የደንበኛ አቅም ማለት ነው። አማራ ባንክ ገና በምስረታ ላይ እያለ ከ4.0 ቢሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒቲል ከሰበሰበ ለኢኮኖሚ ጋሬጣዎቻችን መፍቻ ቁልፍ ተቋም ይሆናል።

የአማራ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አካውንት ሊከፍት በእንቅስቃሴ ላይ ነው ። ትውልደ ኢትዮጵያውያን በተጠንቀቅ ጠብቁ ። 👮

#ሰበር_ዜና ለአማራ ባንክ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነገር ዛሬ ፀድቋል ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አክሲዮን እንዲገዙ የሚፈቅደው አዋጅ ዛሬ ፀድቋል ። በውጭ የምትኖሩ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ ያላ
#ሰበር_ዜና ለአማራ ባንክ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነገር ዛሬ ፀድቋል ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አክሲዮን እንዲገዙ የሚፈቅደው አዋጅ ዛሬ ፀድቋል ። በውጭ የምትኖሩ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ ያላችሁ። አሻራችሁን አማራ ባንክ ላይ አሳርፉ። Via. Dr Letenah Ejigu Wale.

የአማራ ባንክ የሥራ ቅጥር በተመለከተ እንዴት አደራችሁ? በርካታ ሰዎች የ አማራ ባንክ ሰራተኛ መቅጠር እንደጀመረ ለማወቅ ጥያቄዎቻቸውን ለአማራ ምጣኔ ሃብት መማክርትን እያቀረቡ ይገኛሉ። የአማራ ባንክ የሥራ ማስታወቂያም ሆነ ቋሚ የሠራተኛ ቅጥር ሂደት አልጀመረም ። የቅጥር ማስታወቂያ የሚወጣው እና ቅጥር የሚጀምረው፥ ጠቅላላ ጉባኤ ተሰብስቦ ቦርድ ከመረጠ በኋላ፥ ቦርዱ ደግሞ ዋና ዋና ስራ አስፈፃሚዎችን ከመረጠ ( ከሾመ) ፥ እና ሂደቱም በብሄራዊ ባንክ ከፀደቀ ብሎም በህግ መቋቋሙ በይፋ ለህዝብ ከተገለፀ በኋላ ነው። ሂደቱቶችን በዝርዝር ስንመለከት፦ 1. የአክሲዮን ሽያጭ ይጠናቀቃል ። (የካቲት 30፤ 2012) 2. የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ይካሄዳል፣ (በመጋቢት መጨረሻዎቹ ይጠበቃል) 3. የባንኩ የቦርድ አባላት ይመረጣሉ፥ 4. ሁሉም አከሰሲዮን የገዙ ግለሠቦችና ድርጅቶች በአካል ወይም በወኪሎቻቸው አማካኝነት ውልና ማስረጃ ቀርበው በመተዳደሪያ ደንብና መመሥረቻ ፅሁፍ ላይ ይፈርማሉ። ይህ ሂደት አዲስና የተለየ አሠራር ከሌለ በስተቀር ጥቂት ሳምንታት ጊዜ ሊወስድ ይችላል። 5. ቦርዱ የባንኩን ከፍተኛ የስራ አመራሮች ይመረጣሉ ። 6. የቦርድ አባላት እና ቁልፍ አመራር ስም ዝርዝር ወደ ብሄራዊ ባንክ ተልኮ የብቃት ምርመራ ይደረግባቸዋል፤ ለህዝብም ይፋ ይሆናል። (አሁን ያለው አሥተባባሪ ቡድን፥ የተመረመረ ሂሳብና የሥራ ሂደት አዲስ ለተመረጡ የቦርድ አባላት ያስረክባል) የቦርድ አባላትና ዋና ስራ አስፈፃሚው በዋና የሃገሪቱ ጋዜጦች በይፋ ይወጣል። 7. በተራ ቁጥር 6 ላይ ምርመራ የተደረገባቸው የባንኩ ቦርድ አባላትና ስራ አስፈፃሚ(አንድ ሰው ቢሆንም) የብሄራዊ ባንክ መሥፈርት የማያሟሉ ከሆነ፥... ወዘተ በምትኩ ሌላ አባል ለመምረጥ ሂደቱ እነደ አዲስ ሊጀምር ይችላል። 8. ከላይ የተጠቀሱት ሂደቶች አልፎ በብሄራዊ ባንክ ክትትል መሥፈርት ይሁንታን ሲያገኝ፥ የቅርንጫፎች ኪራይ፥ የኮር ባንኪንግ እና የባንክ ቁሳቁሶች ግዢ ...ጎን ለጎን ደግሞ፥ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ በዋና ዋና የሚዲያ አውታሮች ይለቀቃል። ባንኩ ሁሉንም ቅርንጫፎች በራሱ ዲዛይን በመሥራት፥ የውስጥ አሠራር መዘርጋት፥ ዕቃዎችን ማሟላት፥ የ IT ፋሲሊቲ መዘርጋት/መትከል እና የሠው ሃይል ቅጥር ሂደት ካጠናቀቀ በኋላም በብሄራዊ ባንክ ተረጋግጦ ጊዜያዊ የሥራ ፍቃድ ማግኘት አለበት። የቅጥር ማስታወቂያ፥ ቅጥር እና ምደባ በሃገሪቱ የሠው ሃይል ቅጥር ህግና ደንብ ተከትሎ ይከናወናል። በአጠቃላይ እንደ Amhara Economic Think Tank ግንዛቤ፥ የሠው ሃይል ቅጥር ቀደሞ(ጎን ለጎን) የሚሠራ ክንውን ቢሆንም፤ ሂደቶችን ሁሉ አጠናቅቆ ባንኩን መደበኛ ስራ ለማስጀመር ከ6 እስከ 12 ወራት የሚደርስ ጊዜ መታገስን ይጠይቃል። መልካም ቀን ይሁንላችሁ!

✅ Amhara bank s.c Please please please share it???

አማራ ባንክ ወቅታዊ መረጃ! በዚህ መከራ በበዛበት ወቅት ስለ ምጣኔ ሃብትና ተዛማጅ ችግሮች መፃፍ አግባብ ባይሆንም፥ የሚከተለውን መረጃ አቅርበናል። 1) መጀመሪያ በንግድና ኢንደስትሪ የተመዘገበበት ቀን፦ የካቲት 15 ቀን 2011 ዓ.ም 2) 12 የፕሮጀክቱ ጠንሳሾች፥ 3) የአክሲዮን ሽያጭ የተጀመረበት ቀን፦ ነሃሴ 11 ቀን 2011 4) የአንድ አክሲዮን ሽያጭ 1000 ብር 5) መግዛት የሚፈቀደው ዝቅተኛ የአክሲዮን ብዛት 10( 10,000 ብር)፤ ከፍተኛው 100 ሚሊዮን ብር 6) የአገልግሎት ክፍያ 5% 7) እስካሁን የተከፈለ ካፒታል(ጥሬ ገንዘብ) ብር 3.5 ቢሊዮን ብር 8) የተፈረመ ካፒታል ፦ ብር 4.7 ቢሊየን ብር 9) በመሥራችነት የተሣተፉ ባለአክሲዮኞች ብዛት፦ አልተረጋገጠም (ከዚህ በፊቱ አሃዝ በመነሳት ከ 80 ሽ ባለአክሲዮኖች በላይ) 10) ከባለአክሲዮኖች የተሠበሰበ የተከፈለ(5%) የአገልግሎት ክፍያ 225 ሚሊዮን ብር በላይ። ይህ ገንዘብ አስተባባሪዎች የሚያንቀሳቅሱት እና ለባንኩ መመሥረቻ የሚውል የሥራ ማስኪያጃ ነው። 11) አክሲዮን ሽያጭ የሚያበቃበት ጊዜ የካቲት 30 ቀን 2012 ዓ.ም 12) ጠቅላላ ጉባኤ የሚካሄድበት ቀን…በፕሮግራም፥ ቦታና ቀን ተወስኗል። ወደፊት ይገለፃል። 13) 34 አስተባባሪዎችና ከ10 ያላነሡ የፕሮጀክት ፅ/ቤት ሰራተኞች 14) ዲያስፖራ: ዲያስፖራው አክሲዮን መግዛት እንዲችል አዋጁ ቢፈቅድለትም፥ ተፈፃሚ የሚሆነው በውጭ ሃገር ገንዘብ ብቻ እንደሆነ ያብራራል። አፈፃፀሙ ግን አልተገለፀም። 15) እንደአማራ ምጣኔ ሃብት ዕይታ፦ መልካም አጋጣሚዎች፦ ቁርጠኛ ባለአክሲዮኖች ፤ ሁሉን አቀፍ፤ ሰፊ መሠረት ያለው እና ትልቅ የገንዘብ አቅም ይዞ መነሣቱ፥ ተግዳሮቶች፦ • ከባንኩ አስተባባሪዎች ውስጥ፥ ፕሮጀክቱን ዘግይተው የተቀላቀሉ፥ በዘርፉ ተዛማጅ እና ልምድ የሌላቸው፥ ፖለቲከኞችና በትርፍ ሰአታቸው የሚሳተፉ ግለሠቦች ተፅኖ እየጨመረ መሄዱ እንዳይፋጠን ዋና ምክንያት ነው። • ፕሮጀክቱ ውስጥ በዘርፉ በቂ ልምድ ያላቸው ሙያተኞች ቁጥር አነስተኛ መሆን፤ ልምድ እና ችሎታ ያለው የህዝብ ግንኙነት ከመቅጠር ይልቅ አክቲቪስት ላይ የተንጠለጠለ ማድረግ ሌላው የሚታይ ሃቅ ነው፤ የአማካሪዎችና የህግ ባለሙያ ቡድን አለመኖር ትልቅ ክፍተት ይታያል ፤ • ከፍተኛ የባለአክሲዮኖች ቁጥር ተሳትፎ በውልና ማሥረጃ ቀርቦ ለማስፈረም የሚወስደው ጊዜ ረጅም እና ውስብስብ ሊሆን ይችላል፥ • ጠንካራ ልምድ ያለው እና ባንኩን የሚመጥን ቦርድ ስብስብ ለመምረጥ የጠራ አካሄድ አለመኖር፤ • የምስረታው መጓተት ከባንኩ ላይ የሚኖረው ተፅኖ ፥ ለምሳሌ፦የተሠበሰበው ገንዘብ ከጊዜ መራዘም አኳያ ሊኖር የሚችለው የዋጋ መቀነስ (ግሽበት) መሠረታዊ ማሳሰቢያ(መፍትሄ)፦ አማራ ባንክን ዘመናዊ፥ አለማቀፋዊና ሃገርን የሚጠቅም ሁነኛ ባንክ አድርጎ ለማቋቋም፥ ጠንካራ ቦርድ እና በአለምአቀፍ ባንኮች የሠራ “ጥይት የማይበሳው” ዋና ስራ አስፈፃሚ መቅጠር(ሊኖረው) የግድ ይላል። የአማካሪዎች እና በባንክ ላይ የሠሩ ህግ ሙያተኞች ቡድን ማዋቀር፤ በቢዝነስ እና ምጣኔ ሃብት፥ በፕሮጀክት ክትትል እና/ወይም ህዝብ አስተዳደር የሠለጠነ እና ባንክ ላይ የሠራ ባለሙያ መቅጠር። የምዝገባ ሂደቱን ከውልና ማስረጃ ሃላፊዎች ጋር ተነጋግሮ፥ ተጨማሪ የሰው ሃይል ቀጥሮና አሰልጥኖ፥ ከስራ ሰአት ውጭ፥ በተለየ መሥኮት(ቢሮ)፤ በክፍያ፣ በሁሉም ዞኖች የተዋቀረ አሰራር መፍጠር። አሁን ያሉት በዘርፉ ልምድ የሌላቸው አስተባባሪዎችና ፖለቲከኞች ቦታውን ለባለሙያተኞች ማስረከብ አለባቸው። ይህን በማድረግ ባንኩ ወደ ስራ የሚገባበትን ጊዜ ማፋጠን ይቻላል።

Amhara bank s.c @amharabank Together we Can!!!

የአክሲዮን ሽያጭ ቀን እንደገና ተራዘመ! የአክሲዎን ሽያጭ ቀነ ገደቡ ለሁለተኛ ጊዜ ተራዝሟል። የተከፈለው አክሲዎን ሽያጭ 3 ቢሊየን፥ የተፈረመ ደግሞ 4.1 ቢሊየን ሆኗል። መራዘሙ ዲያስፖራው ዋና ተሳታፊ እንዲሆን መልካም አጋጣሚን ፈጥሮላቸዋል። አማራ ባንክ የራሱ የሆነ በማህበራዊ ሚዲያ በስሙ የተከፈተ የማስታወቂያ ገፅ የለውም። 1) ጊዜ ገደብ፦ የምስረታ ሂደትና የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜ ገደብ እስከ የካቲት 30 እንዲራዘም ተወስኗል። በርካታ ግለሰቦች፥ ዲያስፖራው፥ ባለሃብቱና አርሶአደሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በበቂ ሁኔታ እንዳልተሳተፉ ስለታወቀና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲራዘምላቸው በጠየቁት መሠረት፥ የመሥራችነት ዕድል የሚያስገኘው የአክሲዎን ሽያጭ ለሁለት ወራት ተራዝሞ የካቲት 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ከቀኑ 12 ሰዓት ላይ በይፋ ይዘጋል። ከ70,000 በላይ የሚሆኑ ባለአክሲዎን በግዥ ሂደት መሣተፍ፥ የዳታ ማጣራቱን እና ሂሳብ ማስተካከሉ ስራ፥ ሌላው በቂ ጊዜና ብቁ ባለሙያ የሚፈልግ ክንውን እንደሆነ አስተባባሪዎች አምነውበታል። 2) የአክሲዮን ሽያጭ መጠን፦ እስካሁን ድረሥ 3(ሶስት) ቢሊዮን ብር የተከፈለ እና ከ 4.1 ቢሊየን ብር የተፈረመ ካፒታል መድረሡን መረጃዎች ያመለክታሉ። “አማራ ባንክ 5 ቢሊዮን የሚደርስ አክሲዮን ሸጦ ጠንካራ ተቋም በመሆን፥ በሃገር ልማትና አለማቀፋዊ አገልግሎት በመሥጠት ረገድ ጉልህ ሚና መጫዎት አለበት” ሲሉ አስተያየት ሰጭዎች ለ Amhara Economic Think Tank ገልፀዋል። 3) ዲያስፖራው፦ ዲያስፖራው አክሲዮን በመግዛት ተሳታፊ የሚሆንበት አግባብ ለማመቻቸት፥ መመሪያው ከብሄራዊ ባንክ እየተጠበቀ እንደሆነ ታውቋል። የብሄራዊ ባንክ መመሪያ(Directive) በሶስት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ይደርሳል ተብሏል። 4) ቅጥር፦ የአማራ ባንክ ፕሮጀክት የሠራተኛ ቅጥር አላወጣም። የሰው ሃይል ቅጥር የሚጀምረው ባንኩ ከተቋቋመ በኋላ ይሆናል። 5) ማስታወቂያ፦ የአማራ ባንክ ፕሮጀክት የማስታወቂያ ክንውን በቂ እንዳልሆነና ተደራሽነቱም አነስተኛ በመሆኑ የመረጃ ክፍተት እንደታየ አስተያየት ሰጭዎች አቅርበዋል። ስለሆነም ተዛማጅ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውና በህዝብ ግንኙነት ስራ ባንክ ላይ ልምዱ ያላቸው፥ በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ዘርፍ ተጨማሪ ስልጠና የወሰዱ ሙያተኞችን በመቅጠር በቂ መረጃ ማሰራጨት ይቻል ነበር በማለት አስተያየት ሰጭዎች አመልክተዋል። 6) አክሲዮን የገዙ መሥራቾች ጥቅም፦ ይህ ጉዳይ በጠቅላላ ጉባኤው ላይ ቀርቦና ውይይት ተደርጎበት፥ የሃገሪቷን ንግድ ህግና የብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት አድርጎ በመመስረቻ ሰነዱ የሚፀድቅ እንጅ፥ አሁን ባለበት ደረጃ የሚወሰን አይሆንም። 7) የተጠቀሱ ስልኮች አይሰሩም፦ ከዚህ ቀደም የተጠቀሱ ስልኮችን መሥመራቸው አንዳንድ ጊዜ እንደማይገኝ፥ እንደማይነሱ ወይም እንደማይሰሩ ይጠየቃል። ስልኮቹ ስራ ይበዛባቸዋል። ከዚህ ባለፈ፥ ከባንኩ አስተባባሪ አባላት መካከል ለስራ ጉዳይ ከሃገር መውጣታቸው ለባለፉት ሁለት ሳምንታት ክፍተቱ ተፈጥሮ ቆይቷል። የአክሲዮን ሽያጭ መረጃ በ10 ባንኮችና በቅርንጫፎቻቸው ቀርቦ ማግኘት ይቻላል። ከዚህ በተጨማሪ፥ የሚከተሉት ቁጥሮች አገልግሎት ላይ ናቸው። 0912001819/0911133014/0911248160/ 0941466607 Telegram, Vibr, and WhatsApp +251911600388 ጉርሻ! Amhara Economic Think Tank ለህዝብ የሆኑ ምጣኔ ሃብታዊ ዋልታ ተቋማት እንዲመሰረቱ እገዛ በማድረግ እየሰራ ያለ የመማክርት ቡድን ነው። መልካም ምሽት!

“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ሉቃ2;11 እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ:: የሀሴት በዓል ይ
“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ሉቃ2;11 እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ:: የሀሴት በዓል ይሁንልን❤️👏

ምስጋና! በምስረታ ላይ የሚገኘው የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ የሚጠናቀቀው ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ነው። እስካሁን የተፈረመ 3.12 ቢሊዮን እና የተከፈለ 2.35 ቢሊዮን ደርሷል። የአክሲዮን ሽያጭ ከመጠናቀቁ በፊትና የወደፊት አመራር ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ግን በፕሮጀክቱ ተሳትፎ ላደረጉት አካላት ምስጋና እናቅርብ። የአማራ ባንክ አ.ማ ምስረታ እውን ለማድረግ በርካታ ሰዎች በቅንነት እና በቁርጠኝነት ለአንድ አመት ያክል ደክመዋል። ይህ ፕሮጀክት ከ 50 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያደረገበት የቤተ ንዋይ ፕሮጀክት ነው። በምስረታ ላይ ያለው የአማራ ባንክ ፕሮጀክት የአንድ ግለሰብ፥ የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የአንድ አካባቢ ቡድኖች ብቻ የስራ ውጤት አይደለም። ገንዘቡ፥ የስራ ሂደቱ፥ አመራር መምረጡ፥በብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት፥ የባንኩን የወደፊት አቅጣጫ በበላይነት የሚወስኑት ባለ አክሲዮኖች ናቸውና ለባለ ድርሻ አካላት አደራና ምስጋና ይድረስልን። ባላክሲዮኖች እስከ ሶስት ቢሊየን ብር የሚጠጋ ካፒታል ማሰባሰብ የቻሉት፥ ለሃገር ህልውና የሚጠቅም፥ ለብዙሃኑ የህብረተሰብ ክፍል የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ አወንታዊ ለውጥ ሁነኛ ሚና ይጫወታል የሚለውን የፕሮጀክቱ አላማ አምነውበት እንጅ፥ በአንድን ግለሰብ ተማምነው በስሜት የወሰኑት እንዳልሆነ እንረዳለንና በድጋሜ ክብር ለህዝብ፤ ትልቅ ምስጋና ለባለ አክሲዮኖች ይገባቸዋል!! በፕሮጀክቱ ቆይታ ሁሉም 50 ሚሊዮን ህዝብ ፍፁም እኩል የሆነ አስተዋፅኦ ላይኖረው ይችላል፤ ለባንኩ ዕውን መሆን ግን የሁሉም ተሳታፊዎች፥ የሁሉም ባላክሲዮኖች፥ የባንኮች፥ የሴክተር መስሪያ ቤቶች ወዘተ የጋራ ውጤት መሆኑ ታሪካዊ ሃቅ ነው። ሆኖም፥ ባሳለፍነው ከባድ የፖለቲካ ሞገድ በነበረበት አመት፥ ለኢትዮጵያውያን የሚበቃ ቤተ ንዋይ ፕሮጀክት ቀርፀው ለዚህ ላበቁ ወጣት ምሁራን እና ዘግይተውም ቢሆን ተቀላቅለው ፕሮጀክቱ ከዚህ ደረጃ እንዲደርስ ጥረት ላደረጉ ሃላፊዎች፥ አስተባባሪዎች፥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች አበርክቷቸውን በጥቅል ለመዘከር መልካም ስራን እንድናስታውስ ይረዳናል። ስለ አማራ ባንክ እና ሌሎች ቀጣይ ፕሮጀክቶች ለ 8 ወራት ያክል ሲወያዩ፥ አካሄድ ሲነድፉና ሰነድ ሲያዘጋጁ ቆይተው፥ ይህን ፕሮጀክትን ወደ መሬት በተግባር በማውረድ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ወጣት ሙሁራንን ወደፊት እንጠቅሳለን። ለዛሬው ግን እደጉልን በሏቸው። እስካሁን ባለው የፕሮጀክቱ እንቅስቃሴ በተሳካ ሁኔታ እንዲሄድ ተሳትፎ ያደረጉ ግለሰቦች፥ በስራ ሂደቱ ላይ ያበረከቱት ጉልህ ሚና እና መልካም ስራቸው ማህበራዊ ሚዲያው እንዲያስታውሰውና፥ የመልካም ስራ መንፈስ መንሸራሸር ትርጉሙ በቃላት ከሚገለፀው በላይ ሊሆን ስለሚችል፥ ቅን ልቦች ሁሉ ይባረኩ። ሲቀጥልም፥ እንደ አማራ ምጣኔ ሃብት መማክርት አባላት እምነት፥ አብረውን ለደከሙ ሁሉ ከወዲሁ እጅ መንሳታችን እንጅ፥ በስምና በግብር ተዘርዝሮ ጊዜ በሚፈቅደው፥ በሚመጥናቸው ቦታ እና ሁኔታ፥ አስተዋጽኦቸው እንዲዘከር ቀጣይ ሌላው የቤት ስራችን ይሆናል ። ከወዲሁ ግን እግዚያብሄር ይባርካችሁ ብለናል። ልዩ ምስጋና፦ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እና የአዲስ ባንኮች ክትትል ክፍል የስራ ባልደረቦች፥ የስራ መሪዎች፤ ለሁላችሁም እጅ ነስተናል! ለንግድ ባንኮች፦ አቢሲኒያ ባንክ፥ አባይ ባንክ ፥ ቡና ባንክ፣ ዳሽን ባንክ፣ ኦሮሚያ ህብረት ስራ ማህበር፣ ሕብረት ባንክ፣ አንበሳ ባንክ፣ ንብ ባንክ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፥ እና አዋሽ ባንክ ... ስማችሁ በአወንታዊ ጎኑ፥ Basel III ከፍ አድርጎ ይጥራው፤ የአለም ባንኮች ጉልላት ሁኑልን፤ በጣም እናመሰግናለን!!! የሴክተር መስሪያ ቤቶችና ድርጅቶች፥ የኢትዮጵያ ንግድና ኢንድስትሪ፥ የጥበብ ሰዎች፥ የማስታወቂያ ድርጅቶች፥ የዜና አውታሮ፦ Amhara Mass Media, ASRAT Media House, SBS Radio, Ethiopian Broadcast Service, The Reporter, Walta Television, Fana Broadcast Corporation, Amhara FM Radio, Ahadu Radio, Amhara Media Center, አዲስ ማለዳ ጋዜጣ .......... ሁላችሁንም ከልብ እናመሰግናለን። ሰላማዊ አርብ ከሰአትና መልካም ምሽት፥ የደስታ በአል ይሁንላችሁ!!

ሠላም ሠላም ውድ ወንድሞቸ እህቶቸ እንዲሁም አባቶቸ እንደምን አላችሁ🙏🙏

የባንክ ኢንደስትሪ (ለግንዛቤ ብቻ) እንደ 2018 የበጀት አመት መጨረሻ፥ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ሪፖርት፥ 107 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፥ የባንክ ቁጥር 18 ሲሆን 16 የግልና 2ቱ የመንግስት ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የውጭ ባንክ የለም። ቅርንጫፍ፦ በቅርንጫፍ ደረጃ በሃገሪቱ ጠቅላላ 4757 የባንክ ቅርንጫፎች አሉ። በ2071/18 ብቻ 500 ያክል የባንክ ቅርንጫፎች ተከፍተዋል። ዋና ዋና ባንኮችና ያሏቸው ቅርንጫፍ ቁጥር A) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1375 B) ልማት ባንክ.....................107 የመንግስት ባንኮች ድምር 1482 C) የግል ባንኮች …….........3275 ሲሆን አዋሽ፥ዳሽን እና አቢሲኒያ ባንኮች በቅደም ተከተላቸው 382፤ 381 እና 284 ቅርንጫፎች እንዳላቸው ሪፖርቱ ያሳያል። በዚህ መሠረት አንድ ባንክ ለ20,286.5 ሰዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ማለት ነው። የባንክ ቅርንጫፎች መገኛ፦ የኢትዮጵያ ባንኮች በብዛት የሚገኙት በከተማ አካባቢ ነው። ለአብነትም፥ አዲስ አበባ ብቻ 1675 ቅርንጫፎች (35.2%ቱ) የሚገኙ ሲሆን፥ ሌሎች ክፍለሃገራት 3082 (64.8%) ቅርንጫፎች እንደሚገኙት መረዳት ይቻላል። የባንኮች ጠቅላላ ካፒታል እና የሚያንቀሳቅሱት ገንዘብ፦ የሁሉም ባንኮች ጠቅላላ ካፒታል ተደምሮ 85.8 ቢሊየን እንደሆነ የ2018 በጀት አመት መጨረሻ ሪፖርት ያሳያል። ሆኖም እንደ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ፖርት “Total resources mobilized by the banking system in the form of deposit, borrowing and loan collection ... reached Birr 298.2 billion..” ይላል። ገፅ 97. የተናጠል ካፒታል መጠን እና ድርሻቸው፦ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 43.851 ቢሊዮን =51.1%፥ ልማት ባንክ 7.676 ቢሊዮን = 9% ሁለቱ የመንግስት ባንኮች የካፒታል መጠን 51.528 ቢሊዮን ሲሆን ፥ ከጠቅላላ በሃገሪቱ የሚገኙ ባንኮችን ካፒታል 60.1% ድርሻ ይዟል። የግል ባንኮች(የ 16ቱ) ድምር 34.22 ቢሊዮን ብር ሲሆን ድርሻቸውም 39.9% ነው። የግል ባንኮች ካፒታል በተናጠል፦ አዋሽ፥ ዳሽን እና አቢሲኒያ ባንኮች በቅደም ተከተል ብር 4.21 ቢሊየን (4.9%)፥ 3.725 ቢሊየን (4.3%) እና 3.265 ቢሊየን (3.8%) ሆነው እየመሩ አንደነበር ታይቷል። የአማራ ባንክ Paid Up Capital አሁን ባለበት ብቻ ጠንካራ አቋም ይዞ ወደ ዘርፉ መቀላቀል እንደሚችል ያመላክታል።

2.6 ቢሊዮን የተፈረመ ካፒታል። ይህ በምስረታ ላይ ያለው የአማራ ባንክ ሪፓርት ነው፣ የተከፈለ ካፒታል ብር 2 ቢሊየን ሞልቷል። የአክሲዮን ሽያጭ መግለጫ ከተነገረበት ነሃሴ 11 ዓ.ም. ጀምሮ ፥ ልክ በአራት ወሩ 2(ሁለት) ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል አክሲዮን ተሽጧል። የ120 ቀናት የአክሲዮን ሽያጭ ውጤት፤ ከ32,000 በላይ ባለአክሲዮኖች ተሳትፎ፤ በ6 የስልክ ጥሪ መሥተንግዶ፤ ያልታከቱ አምስት ግለሰቦች የሰልክ ጥሪ መቀበል አገልግሎት፤ በ10 የመንግስትና የግል ንግድ ባንኮች በመላ ሃገሪቱ የተካሄደው የሽያጭ ክንውን፤ እና በ Amhara Economic Think Tank ጊዜውን የጠበቀ ሪፖርት አቅርቦት፥ እነሆ ዛሬ ላይ የተከፈለ ካፒታል ብር 2 ቢሊዮን እና የተፈረመ ብር 2.6 ቢሊዮን ካፒታል ደርሷል። የአማራ ባንክ ፕሮጀክትን ሃሳብ የጠነሰሱ የ12ቱ ወጣት ሙሁራን፥ አክሲዮን የገዙ፥ የባንኩን መመሥረት በጉጉት የሚጠባበቁ፥ አደራጆች እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚናፍቀው ባንክ ዕውን እንዲሆን ዛሬም ተግተን እንስራ። የአማራ ባንክ ካፒታል ከፍተኛ መሆን የአንድ ፋይናንስ ተቋም ጥንካሬ ዋና መለኪያ ስለሆነ፥ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ከጅምሩ ተወዳዳሪ ሆኖ በመቅረብ በሃገር ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶታል። የ አክሲዮን ሽያጭ ክንውን በአጭር ጊዜ ይህን ያክል ካፒታል ውጤት ሲያስመዘገብ አማራ ባንክ የመጀመሪያው እንደሆነ፥ የተለያዩ ተቋማትና የሚዲያ አውታሮች መስክረውለታል። ድንቅ አንድነት፤ አመርቂ የሽያጭ ክንውን፤ የተባረኩ የአደራጅ አስተባባሪዎች፤ ቁርጠኛ ባላክሲዮኖች። ፈጣሪ በያላችሁበት ሰላሙን ያብዛላችሁ!!

Amhara Economic Think Tank

ፈጥር እያየ፥ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶችን የሚገፋ ካድሬ እንዳለ እናውቃለን። የብድርና ቁጠባ ትንተና ሰርተው፥ የ Portfolio አዘጋጅተው፣ የገንዘብ ፍሰታቸውን (Cash flow) አሰላስለው እና ውሳኔ አሳልፈው የሚያቀርቡ ረቂቅ ሶፍትዌሮች እንዳሉ አውቀን፥ ከቴክኖሎጅው ጋር መግባባት የሚችል ባለሙያ ማፈላለግ የግድ ይለናል እንጅ ጥርሱን በሴራ የጨረሰ ካድሬ አማራ ባንክ ጉያ ስር ምን ይሰራል? Cyber Security and Resilience ላይ መስራት የጦር ቀጠና ውስጥ ሆኖ መታገል እንደሆነ መቸ ልብ ይላልና!? Robotic Process Automation ውድድር የአለምን ፋይናንስ ተቋማት ትንፋሽ አሳጥቶታል። አቶ “ጎሳዩ ተስፋዬ ” የሚያስበው ግን በዘመድ አዝማድ የታጀበ ቁልፍ ቦታዎችን መያዝ ሊሆን ይችላልና አደብ እንዲገዛ ንገሩልን። ዛሬ ላይ የቁጠባ ሂሳብ ደብተር መያዝ ታሪክ ሆኗል፤ ሂሳብ ለመክፈትና ገንዘብ ለማውጣት ፎቶ፥ መታወቂያ፥ የፊርማ ናሙና ወዘተ ጡረታ ላይ ናቸው። የፋይናንስ ቴክኖሎጅ ከዚህ በደረሰበት ዘመን የሰፈራችን ካቢኔና ተመራጭ ጋሽ “እያየህ ተራመድ” ከእቁብና እድር ያገኘውን ልምድ ይዞ የአማራ ባንክ ደንበኞች አገልግሎት ሃላፊ ሆኖ ለመሥራት እንዳይቀርብ ምከሩልን፤ አማራ ባንክን ከሌሎቹ የፖለቲከኞች ቦርድ ስብስብ በሚዘወሩ ባንኮችና የቁጠባ ተቋማት ጋር ለመጨፍለቅ የሚደረገው ህልም፥ ከቅዠትም አልፎ እብደት ነውና አደብ እንዲገዙ ለነ አቶ "ልማቱ ፈጠነ" በአፅኖት ሊነገራቸው ይገባል!! አማራ ባንክን ትክክለኛ የህዝብ ፋይናንስ ድርጅት እናድርገው። አማራ ባንክ ቤት ውስጥ ለፖለቲከኞች የሚሆን ምንም አይነት መቀመጫ እንደሌላቸው ማወቅ አለባቸው። በለመዱት የዝምድና፥ ሙስና፥ ቢሮክራሲ ያናወዘው ተቋም እንዲሆን አንፈልግምና አስረዱልን። ባንኩን የመሠረትኩት እኔ ነኝ፥ የኔ ልፋት ውጤት ነው...ለማለት ከአስተባባሪዎች ውስጥ በሰንሰለት ሰርገው የገቡ ካድሬዎች አይጠፉም። መኖራቸው ችግር የለውም። ከቴክኖሎጅ እጅግ እሩቅ ከመሆናቸው ባሻገር ፥ አቅመ ቢስነታቸውን፥ ሴረኝነታቸውና ቅናታቸው ግን ከባለሙያ ፀባይ ጋር አይገጥምም ። የተደበቀ ሴራቸውን እፍኝ የማትሞላ የአክሲዮን ድርሻ ይዘው ከቦርድ እንዳይቀላቀሉብን ለሁሉም ባለአክሲዮኖች የማሳወቅ ሃላፊነት አለብንና ልብ አድርጉልን። አለማቀፋዊ ወዝና ቁመና ያለው ጀግና ባንክ አቋቁመን ይህን ከፍተኛ ካፒታል ለካድሬ ካስረከብነው፥ ሃገራችንን፥ ብሎም ህዝባችንን ዳግም ሊነሳ በማይችልበት ውድቀት አንዳንጥለው እንጠንቀቅ። ትልቅ ክስረት እንዳይደርስ ነቅተን እንጠብቅ። የራሳችንን ፍላጎት እንገድብ፤ ጥፍራቸውንም ጥርሳቸውንም በፋይናንስ ተቋማት ሥራ የነቀሉ አርበኞችን ጊዜ ወስደን በባትሪ አፈላልገን እናስገባቸው እንጅ በችኮላ ለአማራ ባንክ የማይመጥኑ ግለሰቦችን መጋበዝ የለብንም ። በባንክ ኢንደስትሪው የቴክኖሎጅ ሙያ ሱስ ሆኖ ያሰከራቸውን ወጣት ኤክስፐርቶች ወዲህ በሉልን!? አዳዲስ ምሩቃን ስልጠና ወስደው እንዲቀጠሩ ዕድሉ ይመቻችላቸው። በሌሎች ንግድ ባንኮች ውስጥ በዋና ወይም ምክትል ስራስኪያጅነት የሰሩ ባለሞያዎች ከባንካችን እንዲቀላቀሉ እድሉን እንስጣቸው። ይህ ከሆነ፥ በእርግጠኝነት ፦ አማራ ባንክ በጥቂት አመታት ውስጥ ሻምፒዎን ይሆናል ፤ የባለ አክሲዮኖችን ፋይናንስ መዋለንዋይ ውሳኔ የልብ ያደርሳል፤ ትኩረት አድርጎ የሚሰራበትን የደንበኛ ክፍል ያረካል፤ ለሃገር የምጣኔ ሃብት እድገት አስተዋጽኦም እንደታሰበው ይሆናል። ስለሆነም ከፖለቲከኞችና ሴራ ጠንሳሾች ርቀን የፋይናንስ ቤታችንን እናንጽ!! በገንዘባቸው የገዙት የአክሲዮን ድርሻቸው፥ የባንኩን አመራር ለመምረጥ የሚጠቀሙበት ዋና መሣሪያ እንደሆነ ግንዛቤ እናስጨብጥ። በጋራ አንድ ሆነው፥ በቢዝነስ ፍልስፍና እና ፈጠራ ላይ አተኩረው የሚሰሩ ባለሙያዎች እንዲመሩት ትኩረታችንን ሁሉ የባንክ ኤክስፐርቶች ፍለጋ ላይ ይሁን። ከጎጥና ቅናት መንፈስ ተላቀን፣ የራሳችንን ጥቅም አስወግደን፥ በዕቅድ፥ በስልትና በቅንጅትና መዳረሻ ግብ ያለው ሥራ ክንውን ላይ እናተኩረን፥ ጊዜ ወስደን የባንኩን አመራር እንምረጥ ። የአሻራችን ማህተም የሚያርፍበት ከአማራ ህዝብ አልፎ ሃገራዊ መመኪያ የሚሆን አለማቀፋዊ ዕውቅና ያለው አንዱ የፋይናንስ ተቋም እንዲሆን ጊዜያችንን እና እውቀታችንን መስዋዕት እናድርግ። ወንድሞቻችን ተጨናንቀው ለዘመናት ያጠራቀሟትን ጥሪት እኛን አምነው ለዚህ ቤት የምርግ ግብአት አበርክተዋል። የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል፤ እናቶቻችን ከመቀነታቸው ሸልቅቀው ነው አክሲዮን የገዙት!! ተማሪዎች፥ መምህራን፥ የመንግስት ሰራተኞች፥ ሾፌሮች፥ በቀን ስራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች...፣ዝቅተኛውን የአክሲዮን ድርሻ የገዙት ተርፏቸው አይደለም። ከዚህ መሃል ላይ የካድሬ መመሸጊያ ጎሬ፥ የጡረተኞችም ማንቀላፊያ ሰባራ አልጋ አንሰራም፥ የፖለቲካ ንግድ ማትረፊያ ...ተቋም ሆኖ ማየት ለህዝባችንም ሆነ ይህን ፕሮጀክት ቀርፀው ወደተግባር ለቀየሩት ወጣት ሙሁራን የዘላለም ጠባሳ ሆኖ እንዳያልፍ የሁላችሁንም እርዳታ እንሻለን። እናም፦ ስራን ለሰሪው፥ እሾህን ለአጣሪው ነውና...፦ የፖለቲካ ወንበሩን እና ምህዳሩን የያዙ ግለሰቦች ህልቆ መስፈርት የሌለው ሃላፊነተ እንዳለባቸው ይረዱ። ቢሮክራሲውን፥ ሙስናውን፣ በትውውቅ ቅጥር፥ ጎጠኝነት፥ ስራ አጥነት፥ የመሠረተ ልማት መጓተት፥ ደካማና የተበላሸ የኢኮኖሚ ፖሊሲ፥ የመሬት አሰጣጥ ችግር፥የዲሞክራሲ ምህዳር ጥበትና ወጣቶችን ማሰር.. መፈናቀል፣ የሰራተኞች ስነ ምግባርና ሙያዊ ስልጠና እጥረት፥ የፀጥታና ፍትህ፥ ውሃና ሃይል አቅርቦት ችግሮች ላይ አተኩረው ይስሩ...። ግዴለም እንመርጣቸዋለን። ወንድሞቻችን ናቸው!! ባንክ አቋቋምንም፥የምግብ..ዘይት..ሲሚንቶ..ስኳር..ዱቄት ፋብሪካ ብንተክል፥ ያለ መብራት፥ ውሃ፣ መንገድ፥ድልድይ፥ መሥኖ ልማት ወዘተ የትም አያደርሰንምና፥ እናንተ የፖለቲካ ሰዎች፦ በህፃኑ ጨርቆስ ብላችሁ ከነዚህ ችግሮች ላይ አተኩራችሁ ስሩልን!? ባንካችን ላይ አትተንፍሱበት! እናንተ የመሠረተ ልማቱን ሂደት አንቀው የያዙ ገመዶችን በጥሱልን፤ በኢንቨስትመንቱ ጫንቃ ላይ የተቆለሉ ችሮችን አስወግዱልን፤ በአገልግሎትና ማስፈፀም የስራ ሂደት ላይ ያሉትን የብቃት ችግር አፅዱልን፥ የኢኮኖሚው፥ ፖለቲካ፥ ደህንነት፥ ማህበራዊና ቴክኖሎጅ ዘርፎች ላይ አላግባብ ተቀረፀው ህዝባችንን እየጎዱ ያሉ ፖሊሲዎችን አስተካክሉ።

ከውስጥ የፈለቀ ምርጥ መልዕክት!! አማራ ባንክን አለማቀፋዊና ተወዳዳሪ ተቋም እናድርገው!! የአማራ ባንክን ለማቋቋም ስናስብ ፋናንስ ለሌሎች የምጣኔ ሃብት ዘርፎች ያለውን መሠረታዊ ዕንድምታ ጊዜ ወስደን ተወያየንበት ስምምነት ላይ በመድረስ ነው። ስለሆነም ዝቅተኛውን የህብረተሰብ ክፍል በተለይም ጥቃቅን እና አነስተኛ ማህበራት፣ የንግድ ተቋማት፣ እና ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን በማተኮር አብሮ የማደግ ፍልስፍና ይዞ የተነሳ ነው። አገልግሎቱን ለመስጠት ትኩረት ካደረገበት የቢዝነስ ግዛት የሚገኘው የፋይናንስ አቅርቦት /Finance Supply/፥ የገንዘቡ ፍጆታ /Financial Consumption/ እርቆ ሳይሄድ ከተገኘበት አካባቢ መልሶ እንዲፈስ ማድረግ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ በወጉ የተተለመ የፋይናንስ ሰነ-ዘዴ/Financial System/ ተበጅቶ ማራኪና አላማ ተኮር/Purpose Lead Or Objective Based/ የባንክ አገልግሎቶችን ለመሥጠት መዘጋጀት እንዳለበት ያሰመርንበት ጉዳይ ነው። ከተለመደው የባንክ አገልግሎት በተለየ መልኩ ፈጠራ የታከለባቸው የቁጠባ፣ ብድር፣ መዋለ ንዋይ፣ ንብረት አስተዳደር፣ የስራ ፈጠራ ስልጠናና፣ምክርና ክትትል …አገልግሎት ለመስጠት ህልመኛ ባንክ እንዲሆን በቢዝነስ ሞዴሉ ላይ ስንወያይና ፕሮጀክቱን ስንቀርጽ እንቅልፍ አላየንም። ቴክኖሎጅ፦የሳይበር ትውልዱን የሚመጥን የሞባይል፣ኢንተርኔት እና ኤ.ቲ.ኤም አገልግሎቶች ተለይተው የስትራቴጅው አካል ሆነዋል። የሰው ሀይል፦ ዋናው የባንኩ አካል ስለሆነ ማህበረሰቡን በብቃት፣ በቅንነት እና በትጋት ለማገልገል ዝግጁ የሆኑ አዳዲስ ምሩቃንን እና ልምዳማ ባለሙያዎችን በመመልመል አሰባጥሮ መቅጠር፥ ማሰልጠንና መመደብ ከተለመደው የባንክ አገልግሎት ባህል የተለዬ ሆኖ ለመቅረብ በፕሮጀክቱ ቴክኒክ ክፍል ባለሙያዎች አዋቅረን ስንሰራ ቆይተናል። ባለቤትነት እና ተደራሽነት፦ የአማራ ባንክ ብዙሀኑን የህብረተሰብ ክፍል አክሲዮን እንዲገዛና ባለቤት እንዲሆን ባደረግነው እንቅስቃሴ ያሳያችሁት ተሳትፎ፥ ለዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል የባንክ ባለቤት እንዲሆንና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ በማድረግ ሰፊ፣ የተረጋጋና ቀጣይነት ያለው የቢዝነስ ምህዳር እንዲኖረው የሚያስችል ባህል ተግባራዊ እንዲሆን ልክ እንደ ዛሬው ነገም ከህዝብ ጎን እንድትቆሙ በአክብሮት እንጠይቃለን። የአማራ ባንክ ፕሮጀክት ስጋቶች ፦ • በብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥጥር ስለሚደረግበት በአብዛኛው ስጋቱ ቀላል ነው ፡፡ ሆኖም ከሃገራችን፣ ከማህበረሰባችን እና ከዘርፉ ባህሪ አንፃር በርካታ አስተዳደራዊ፥ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስጋቶችን ሊከሰቱ ይችላሉ በሚል እሳቤ ምክረ ሃሳባችንን እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችንም ለመጠቆም እንወዳለን። 1) የፖለቲከኞች በአማራ ባንክ ላይ ከልክ ያለፈ ፍላጎት መኖር፦ ፖለቲከኞች፥ የሴራ ግለሰቦች፥ብዙ የስራ ሃላፊነት ተሸክመው ባንኩን ቢቀላቀሉ ሊጎዱት የሚችሉ፣ በቂ የትምህርት ዝግጅት የሌላቸው ወይም በዘርፉ ተዛማጅ የስራ ልምድ የሌላቸው፣ ከቴክኖሎጅ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፥ በማህበራዊ ህይወታቸው ምስጉን ቢሆኑም በዘርፉ ያልተፈተሸ ብቃት ያላቸው፥ ልምዱና የትምህርት ዝግጅቱ ቢኖራቸውም የሴራ ተልኮ ሰንቀው የሚጠባበቁ አካላት ... ወደ አመራርነት መጋበዝ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅኖ እጅግ አደገኛውና ዋነኛው ነው። ለዚህ ሁሉ ችግር መነሻ ሊሆን የሚችለው የቦርድ አባላት እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ ግልፅነት የጎደለው፤ ያልተቀናጀ እና በችኮላ የሚሰራ ከሆነ ነው ። እንደ አማራ ባንክ የመጀመሪያወቹ የፕሮጀክት አስተባባሪዎች አቋም ከሆነ ለዋና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ ዋና ዋና መሥፈርቶች እና ቅደም ተከተሎች የሚከተሉት ናቸው። 1) የብሄራዊ ባንክ መመሪያ የሚጠይቀውን መሥፈርት በላቀ ሁኔታ የሚያሟላ ሆኖ፥ ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ መሠረታዊና ቀዳሚ መሥፈርት ነው። (ጉዳዩ አሁን አስተባባሪ ሆነው የሚሰሩትን ግለሰቦችንም ይጨምራል) ይህ ስጋት እንዲቀረፍ ደግሞ የቅድመ የመፍትሄ መላዎች/Proactive Measures ሊሆኑ የሚችሉት፥ ሀ) መጀመሪያ የቦርድና ዋና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ ከመጀመሩ በፊት የምርጫ ሂደቱ ግልፅ መሆኑን የሚያረጋግጥ ገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ማቋቋም ግዴታ ነው። ይህ ቡድን ከተመሠከረላቸው የህግ አማካሪዎች፣ ከብሄራዊ ባንክ ኤክስፐርቶች፥ ጠቀም ያለ አክሲዮን ከገዙ ግለሰቦች፥ ኦዲተሮች፥ አለማቀፍ ባንክ ውስጥ የስራ ልምድ ያላቸው የፋይናንስ ባለሙያዎች፥ የወጣቶች ተወካይና ጠቅላላ ባለአክሲዮኖችን ሊወክል የሚችል ግለሰብ...የተውጣጣ ቡድን እንዲሆን ምክረ ሃሳባችን ነው። ለ) ለቦርድና ዋና ስራ አስፈፃሚ ምርጫ የሚሆን ሙያዊ መሥፈርቶችን የያዘ ፕሮፖዛል ሰርተው ለውይይት ቀርቦ እንዲተች ቢደረግ፥ ሐ) በቅድመ ቦርድ ምርጫ ወቅት እጩ ተወዳዳሪዎችን መመዝገብ እና ለጠቅላላ ጉባኤው ከመቅረባቸው በፊት ለህዝብ ይፋ ቢሆኑ፥ የምርጫ ቅስቀሳ ቢያደርጉና እራሳቸውን ቢያስተዋውቁ፥ መ) የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ዕለት አስመራጭ እና ድምፅ ቆጠራ አስተባባሪ ኮሚቴ ቢመረጥ፥ ሠ) የቦርድ እና ዋና ስራ እኪያጅ ምርጫ በቴክኖሎጅ የታገዘ ከመሆኑም ባሻገር፥ ምርጫው በቴሌቭዥን ጣቢያዎች የቀጥታ ስርጭት መርሐግብር ተዘርግቶ ቢተላለፍ፥ (ይህ የኬንያ ተሞክሮ ነው) 2) ሁለትና ሶስት በላይ አባላት ያሉት በብቃቱ የተመሠከረለት አቅም ባላቸው የህግ ባለሙያ ስብስብ የተዋቀረ የጠበቃ ቡድን ቢቀጠር። 3) የፋይናንስ እና የስራ ሂደቱን የሚመረምርና የሚከታተል የኦዲተሮች ቡድን ቢዘጋጅ፥ 4) አሁን ፕሮጀክቱን የሚያስተባብሩት ግለሰቦች የፖለቲካ አቋማቸው ሳይፈተሽ በቦርድ ምርጫ እጩ ሆነው እንዳይካተቱ ቢደረግ። (በብዙ የህብረተሰብ ክፍል ስጋት ስላለ) ከአማራ ባንክ የአክሲዮን ድርሻ የገዙ ሁሉ ሊያውቁት የሚገባው ቁም ነገር ፥ የባንኩ እጣ ፋንታ የሚወሰነው በሚመርጡት ዋና ስራ አስፈፃሚና የቦርድ ስብስብ ስለሆነ፥ ይህም የገዙት የሸር መጠን ዋና ድምፃቸው መሆኑን ተገንዝበው፥ ሲመርጡ የብሄራዊ ባንክ መሥፈርት የሚያሟሉ፥ በሙያ ብቃት ፥በትምህርት ዝግጅት እና የስራ ልምድን መሠረት አድርገው እንጅ የባንክ ተቋም ለፖለቲከኞች ምንም አይነት ኩርሲ የሌለ መሆኑን እንዲያውቁ ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቢሰጥ። ፖለቲከኞች ቦርድ ውስጥ ቢገቡ ሊኖር የሚችለው ጉዳት እጅግ አደገኛ ነው። በሌላ ጠርዝ የባንክ ኢንደስትሪ የደረሰበት የቴክኖሎጅ ደረጃ በጣም ሩቅ ነው። ለአብነት ያክል፦ ኢትዮጵያ ላይ ሆነን አሜሪካ ባለው የሂሳብ ቋት(Account) የእጅ ስልካችን ተጠቅመን የያዝነውን ቸክ ማስገባት (Deposit) ማድረግ ይቻላል። የትም ቦታ ሆነን የድምፅ ጋቤና (Voice Interface) አማካኝነት በድምፅ ትዕዛዝ ብቻ (በ Voice order) ከሂሳብ ቋታችን ገንዘብ ማውጣት፣ የሂሳብ ሚዛን ወይም ቀሪ ገንዘብ ማወቅ፣ የክፍያ ማረጋገጫ መሥጠት፥ መዋለ ንዋያችንን መከታተል... በሚቻልበት ደረጃና ጊዜ ላይ ደርሰናል። የወረቀት ስራ ታሪክ ሆኖ የሳይበር ቴክኖሎጅ ውጤት የሆነው Cloud Computing አማካኝነት በቲሪሊዮን የሚቆጠር የፋይናንስ መረጃ ማስቀመጥ ተችሏል። የዝርፊያ ወንጀል ጭንብል አጥልቆ መሳሪያ ደግኖ ገንዘብ አስገድዶ የሚወስድ ብቻ የሚመሥለው፥ በምዕናቡ በአማራ ባንክ የ CEO ሃላፊነት ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ እራሱን እያወዛወዘ ብድር የሚጠይቁ ነጋዴዎች ላይ ቢሮክራሲ ሲ

የአማራ ባንክ የጠቅላላ ጉባኤ ሂደት ምክክር፦ ውድ የአክሲዮን ባለድርሻዎች፥ የባንኩን አክሲዮን ሽያጭ ቀን በቀን ስትከታተሉ የቆያችሁ ሁሉ፦ የአማራ ባንክ አ.ማ በአጭር ጊዜ ውስጥ መልካም የአክሲዮን ሽያጭ ውጤት ያስመዘገበው ሁሉም የባለ ድርሻ አካላት የነበራቸው ቀና አመለካከትና ብርቱ ተሳትፎ ነው። ይህን አወንታዊና መልካም አስተሳሰብ ይዘን የሚቀጥለው የምስረታ ሂደት፥ ዝግጅት ላይ መሰረታዊ ግንዛቤ ብሎም ቅድመ ዝግጅት አስፈላጊ ነውና፦ 1)ያማረና የተዋጣለት እንዲሆን ከአደራጆች ጎን መሆን አለብን፤ 2) በትምህርት፥ በልምድ እና ከዚህ በፊት ባሳዪት የፋይናንስ ተቋም አመራር ብቃት መሠረት ለዘመኑ ቴክኖሎጅ ቅርብ የሆኑ ባለሙያዎችን ለመምረጥ እንዘጋጅ። 3) ፖለቲከኞች፥ የሴራ ግለሰቦች፥ብዙ የስራ ሃላፊነት ተሸክመው ባንኩን ቢቀላቀሉ ሊጎዱት የሚችሉ፣ በቂ የትምህርት ዝግጅት የሌላቸው ወይም በዘርፉ ተዛማጅ የስራ ልምድ የሌላቸው፣...ግለሰቦች ወደ አመራርነት መጋበዝ ሊያስከትል የሚችለውን ተፅኖ ከወዲሁ መነጋገር አለብን። 4) ለአካሄዳችን እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ስጋቶችንም ከወዲሁ ብትጠቁሙን ደስታችን ወደር የለውም። 5) ለአማራ ባንክ ጠቅላላ ጉባኤ ሂደትና የቦርድ ምርጫ ግብአት ይሆናሉ የምትሏቸውን ሙያዊ ምክረ ሃሳቦች፥ ጥያቄዎች፥ የታዪ ድክመቶች እና የዕርምት አስተያየቶች ከእናንተ እንጠብቃለን። 6) አስተያየታችሁን እና ሌሎች ነባራዊ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።

ሪከርድ ተሰብሯል። የአክሲዮን ሽያጭ ቀነ ገደቡም ተራዝሟል፤ እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም የተከፈለ የአክሲዮን ሽያጭ (Paid up capital) ብር 1.7 ሚሊየን ደርሷል። የተፈረመ የአክሲዮን ሽያጭ ደግሞ 2 ቢሊዮን አልፏል። የአማራ ባንክ የመስራችነት ዕድል የሚያበቃበት ቀን ለአንድ ወር ተራዝሞ ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓም ሆኗል። ከ30,000 በላይ ግለሰቦችና ድርጅቶች በአክሲዮን ግዥ የተሳተፉና፥ ከ 1.7 ቢሊዮን ብር አክሲዮን በላይ በካሽ የተሸጠ ቢሆንም፥ አያሌ ሰዎች እንዳልገዙ ጠቅሰው ጊዜው እንዲራዘምላቸው ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ ዲያስፖራው እንዲሳተፍ በአዋጅ ቁጥር 1159/2011 ጳጉሜ 3 ቀን ፀድቋል። ነገር ግን ከብሄራዊ ባንክ ዝርዝር መመሪያው እስኪደርስና የውጭ ሃገር ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሸር እንዲገዙ እድል ለመሥጠት ሲባል የመሥራችነት አክሲዮን ሽያጭ ሂደቱ እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ተራዝሟል። ዲያስፖራው የሚሳተፍበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከብሄራዊ ባንክ ጋር አየተነጋገርን ስለሆነ፥ ዝርዝር መግለጫ እስከምናወጣ ድረስ በትግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን። የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን የባንክ አክሲዮን መግዛት የሚችሉት ተቀባይነት ባለው የውጭ ምንዛሬ ብቻ መሆኑ በአዋጁ ተገልጿል። ምስጋና፦ ለብሄራዊ ባንክ ለሁሉም ንግድ ባንኮች ለመገናኛ ብዙሃን ለአክሲዮን ገዝዎች ለአማራ ባንክ አደራጅ ቡድን ለማህበራዊ አንቂዎች እናመሠግናለን! መልካም ጊዜ!!

የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜ ገደብ!? የአማራ ባንክ ሸር ሽያጭ እንደቀጠለ ነው። አላቆመም! በጥሬ ገንዘብ የተከፈለ የአማራ ባንክ አክሲዮን መጠን 1,100,000,000(አንድ ቢሊየን አንድ መቶ ሚሊዮን) ብር ደርሷል። በርካታ ግለሰቦች እና ድርጅቶች እስካሁን አልገዙም። የመሥራችነት ጊዜ ገደቡም እንደቀጠለ ነው። ጎን ለጎን፥የአስተባባሪ ቡድኑ የጠቅላላ ጉባኤ ፕሮግራም ዝግጅት ሽር ጉድ እያለ ነው። ማንኛውም አክሲዮን የገዛ ግለሰብ/ድርጅት በአካል ወይም በወኪሉ አማካኝነት በመገኘት በመመሥረቻ ፅሁፉና በመተዳደሪያ ሰነዱ መፈረም ግዳጅ ነው። ዝርዝር ቦታ፥ ጊዜና የመርሃ ግብሩን ሁኔታ እንገልፃለን። በአካል የማይገኝ ግለሰብ ከወዲሁ ህጋዊ ወኪል፥ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የመንጃ ፈቃድ፥ አክሲዮ ሲገዛ የተሞላ ፎርምና ገንዘብ ገቢ ያደረገበትን Deposit Slips መያዝ አለበት። በመሥሪያ ቤት፥ በትምህርት ቤት፥ የምስክር ወረቀቶች ወዘተ የሸር ባለድርሻ ለመሆን ከውልና ማስረጃ (ህግ) ፊት ተቀባይነት የላቸውም። ለህፃናት አክሲዮን ሲገዙ፣ የህፃኗን/ኑን የልደት ምስክር ወረቀትና የአባት ወይም የእናት ወይም የአሳዳጊ የታደሰ መታወቂያ አብሮ መቅረብ አለበት። ባለትዳሮች በጋራ ወይም በተናጠል አክሲዮን መግዛት ይችላሉ። ህጋዊ የምዝገባ ሰነድ ያላቸው፦ማህበራት ፣ እቁብ፣ ዕድር፥ የሽርክና ድርጅቶች፥ በጎ አድራጎት ድርጅቶች፥ ቤተ ዕምነታት፥ ወዘተ አክሲዮን የመግዛት መብት አላቸው። ለሌላ ግለሰብ/ድርጅት በስጦታ መልክ ለማበርከት ወይም በትዕዛዝ ለመግዛት ህጋዊ ውክልና ያስፈልጋል። የአማራ ባንክ ሸር ሽያጭ እና በግዥ ጊዜ የሚሞሉ ቅጾች በአቅራቢያዎ ካለው አቢሲኒያ፥ አባይ፥ ቡና፥ ኢንባ፥ ዳሽን፥ አዋሽ፥ ኦህባ፥ አንበሳ፥ ንብ፥ እና ህብረት ባንክ ይገኛሉ። ግዢውንም ከነዚህ ባንኮች መጨረስ ይችላሉ። በአክሲዮን ግዥ ጊዜ ፎቶ አያስፈልግም። በጥሬ ገንዘብ የተከፈለ የአማራ ባንክ አክሲዮን መጠን 1,100,000,000(አንድ ቢሊየን አንድ መቶ ሚሊዮን) ብር ደርሷል። አጃ’አይብ ነው! ይቀጥላል!! Follow us!! Share it. መልካም ውሎ!