en
Feedback
TIKVAH-ETH

TIKVAH-ETH

Open in Telegram
6 346
Subscribers
-524 hours
+17 days
+10830 days
Posts Archive
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#መግለጫ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባቀረበው ጥያቄና ከተለያዩ አካላት ጋር ባደረገው ጥረት፣ በዛሬው ዕለት ከ600 በላይ ሰዎች ከእስር መፈታታቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ በላከልን
+1
#መግለጫ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባቀረበው ጥያቄና ከተለያዩ አካላት ጋር ባደረገው ጥረት፣ በዛሬው ዕለት ከ600 በላይ ሰዎች ከእስር መፈታታቸውን ገልጿል። ኮሚሽኑ በላከልን መግለጫ፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው እና ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ዜጎች ጉዳያቸው በልዩ ሁኔታ እንዲታይ ጥያቄ አቅርበዋል። ኢሰመኮም ይህንን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ጉዳዩን ለመንግሥት አቅርቧል። ኮሚሽኑ እንደገለጸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉዳዩን በአዎንታ ተቀብለው፣ የሕግ የበላይነትን በጠበቀ መልኩ ለሰላም፣ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲ የሚያግዙ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ለሚመለከታቸው የመንግሥት መዋቅሮች አቅጣጫ ሰጥተዋል። በዚህ መሠረት በተቀመጠው የሕግና የይቅርታ ሂደት መሠረት፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተፈረደባቸው በይቅርታ እንዲፈቱ፣ በክስ ሂደት ላይ ያሉ ተከሳሾችም ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ ተወስኗል ሲል ኢሰመኮ ገልጿል። ኢሰመኮ ይህንን ውሳኔ ለሰላም፣ ለሀገራዊ መግባባትና ለዴሞክራሲ ግንባታ ጠቃሚ እርምጃ በማለት አድንቋል። በቀጣይም ተመሳሳይ የሰላም ግንባታ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቋል። ከእስር የተለቀቁት ዜጎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው በመመለስ በሕጋዊና ሰላማዊ መንገድ በሀገራዊ የሰላም ግንባታና ልማት ላይ እንዲሳተፉም ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ያሉ ችግሮች በትጥቅ ትግል ይፈታሉ ብለው የሚያምኑ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡ ኢሰመኮ አሳስቧል። ኮሚሽኑ በተጨማሪም በዛሬው ዕለት ከእስር የተለቀቁት ዜጎች ወደ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወደ መደበኛ ሕይወታቸው እንዲቀላቀሉ የሚደረገውን የማቋቋም ሥራ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ አካላት እንዲያግዙ ጠይቋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

"መንግስት ከፋኖ እግር ስር ወድቆም ቢሆን እርቅ ያውርድ!" — ጄኔራል ካሳዬ ጨመዳ በአገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲወርድ ከተፈለገ መንግስት እስከ መጨረሻው ዝቅ ብሎ ''ከፋኖ እግር ስር ወድቆም'' ቢሆን አስቸኳይ እርቅ ሊፈፅም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።  ሌላው ነገር ሁሉ ቀላልና ሁለተኛ ደረጃ ነው ሲሉ የቀድሞው ጀኔራል ካሳዬ ጨመዳ ተናግረዋል። በሻዕብያ እና በህወሓት መካከል የሚታየው ጊዜያዊ የፖለቲካ ፍቅር 15 ቀን እንኳ የሚዘልቅ አይደለም።  መሰረታዊውን የፋኖን ጥያቄና ሀይል ወደ ጎን ብሎ የሚደረግ ማንኛውም አይነት ስምምነትም ሆነ ህብረት የትም ሊደርስ አይችልም ብለዋል።'' ጄኔራል ካሳዬ ጨመዳ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ጥይት ስትተኩሱ ክርስቲያኖች በስመአም፣ መስሊሞች ቢስሚላህ እያላቸው ተኩሱ በሚለው ምክራቸው ይታወሳሉ።  @tikfahethiopia

የድሮን ጥቃት‼️ አዳሩን በሕንጣሎ ወረዳ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። በትግራይ ክልል ሕንጣሎ ወረዳ ጣብያ ፍረወይኒ «ማይ ሽመት» ልዩ ቦታ ላይ ሌሊት 8:30 ሰዓት ተደጋጋሚ የድሮን ደብደባ መፈፀሙ ታውቋል። የድሮን ጥቃቱ ኢላማ የህውሃት የጦር መሳሪያ ክምችት ላይ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ህውሃት በበኩሉ በጥቃቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሦስት ሰዎች (የአራት ዓመት ሕፃንን ጨምሮ) ሲሞቱ፣ የሟቾች እናት ደግሞ በጽኑ መቁሰላቸውንና በንብረት ላይም ከባድ ውድመት መድረሱ አሳውቋል። @Tikfahethiopia

⚠️ GRAPHIC CONTENT ይህ ቪድዮ አስደንጋጭና የሚረብሽ ይዘት ስላለው በጥንቃቄ ይመልከቱ። በአሜሪካ በመብረቅ ተመቶ በተአምር ከሞት የተረፈው ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል። በአሜሪካን፣ ኒውዮርክ ውስጥ " ስታተን አይላንድ " የተባለ አካባቢ ነዋሪ የሆነው ቶማስ ፋህሚ የተባለ ግለሰብ ከመኪናው 15 እስከ 20 ጫማ ርቀት ላይ ሳለ በድንገት በመብረቅ ተመቶ በተአምር ከሞት ተርፏል። ግለሰቡ ከመኪናው ወርዶ ብዙም ሳይሄድ ነው በከባድ መብረቅ ተመትቶ ከሞት አፋፍ የተረፈው። በአካባቢው በነበረው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ውስጥ የተከሰተው ይህ አስደንጋጭ አደጋ ፋህሚ ላይ ከፍተኛ የሆነ የአካል እና የስነ-ልቦና ስቃይ ፈጥሯል። በመብረቅ በተመታበት ወቅት በሁለቱም እግሮቹ ላይ ከባድ የመቃጠል ስሜት፣ የመደንዘዝ እና ከፍተኛ የህመም ስሜት እንደተሰማው ምስክርነቱን ሰጥቷል። አደጋው ከተከሰተ በኋላ " በሌላ መብረቅ እመታለሁ " የሚል ከፍተኛ ስጋትና ፍርሃት አድሮበት እንደነበር ተናግሯል። በአሁኑ ወቅት በህክምና ክትትል ከጉዳቱ በማገገም ላይ ያለው ቶማስ ፋህሚ፣ ይህ አስከፊ አደጋ በህይወት ላይ ያለውን አመለካከት ሙሉ በሙሉ እንደቀየረው ይናገራል። አደጋው ህይወትን ማድነቅ፣ ንጹህ አየርን መተንፈስ፣ ለዕለት ተዕለት ኑሮ ትልቅ ዋጋን መስጠት እንዳለበት አስተምሮታል። እንዲሁም ህይወትን በጭንቀት ውስጥ ማሳለፍ እንደማይገባ ግንዛቤ እንደጨበጠበት ገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከ 'ስካይ ኒውስ' ነው ያገኘው። ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም @tikfahethiopia

#TeleBirr #ብድር በዘንድሮው በጀት ዓመት ኢትዮ ቴሌኮም 35.04 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት ለመስጠት አቅዷል። ኢትዮ ቴሌኮም በ2019 በጀት ዓመት በቴሌብር አማካኝነት ለቴሌብር ደንበኞች እስከ 35.04 ቢሊዮን ብር የአነስተኛ ብድር አገልግሎት ለመስጠት ማቀዱን ገልጿል። እንዲሁም 26.42 ቢሊዮን ብር የቁጠባ መጠን ለማድረስ ግብ አስቀምጧል። የቴሌብር ደንበኞቹን ቁጥር 7.1 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች በመጨመር 67.69 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዷል። በበጀት አመቱ አጠቃላይ የግብይት ብዛት 4.99 ቢሊዮን ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም 7.4 ትሪሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ፍሰት በዲጂታል ሥርዓቱ ውስጥ እንዲንቀሳቀስ ያደርጋል። #EthioTelecom @tikfahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ህፃናት ልዩ ትኩረት ይሻሉ፤ ...ወላጆች ልጆቻችሁ የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል ይገባል " - ፖሊስ 👉 " ሰራተኛ ስትቀጥሩ ጥንቃቄ አድርጉ ! " ህፃን ፊዮና ሰለሞን ነሐሴ
+4
" ህፃናት ልዩ ትኩረት ይሻሉ፤ ...ወላጆች ልጆቻችሁ የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል ይገባል " - ፖሊስ 👉 " ሰራተኛ ስትቀጥሩ ጥንቃቄ አድርጉ ! " ህፃን ፊዮና ሰለሞን ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡30 ሠዓት አካባቢ ከቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ በቤት ሰራተኛቸው የእገታ ወንጀል ተፈጽሞባት 3 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀባት በኋላ አጋቿ ሰራተኛ ተይዛ ህጻኗ ወደ ቤተሰቦቿ እንድትመለስ ተደርጓል። መቅደስ ሞገድ የተባለችው ተጠርጣሪ አቶ ሰለሞን ፈንታሁንና ወ/ሮ ሄለን ኃይለሚካሄል ቤት በቤት ሰራተኝነት ለሶስት ወራት ከሰራች በኋላ " ቤተሰብ ልጠይቅ " ብላ ፈቃድ ጠይቃ ከሄደች በኋላ ሳትመለስ ትቀራለች። ከሁለት ወራት በኋላ ግን ከአንድ ግብረ አበሯ ጋር ወደ ቀድሞ አሰሪዎቿ አካባቢ በመመለስ ህፃን ፊዮና ሰለሞንን ከምትጫወትበት ቦታ ይዛ ትሰወራለች። ከዚያም ግብረ አበሯ ለህፃኗ ቤተሰቦች በስልክ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ይዝታል፤ ቤተሰቡ ዛቻውን በመፍራት 370 ሺህ ብር በባንክ ገቢ ያደርጋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ በመታገዝ ባደረገው ክትትል፣ ተጠርጣሪዋ ህፃኗን ይዛ ወደ አማራ ክልል መሄዷን ለይቷል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመተባበር ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዋን ከጎንደር ከተማ ማራኪ ክ/ከተማ ዩኒቨርሲቲ ጫካ ውስጥ በጥቆማና ክትትል በቁጥጥር ስር ሊያውል ችሏል። ታጋችዋ ህፃን ፊዮና ሰለሞን ትላንት ምሽት ላይ ከባህር ዳር አዲስ አበባ ገብታለች። የአዲስ አበባ ፖሊስ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ፣ ህፃናት ልዩ ትኩረት ከሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ቀዳሚ በመሆናቸው መጠበቅ፣ መንከባከብና ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል። ወላጆች ልጆቻቸው የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል የሚገባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የህፃን ፊዮና እናት ወ/ሮ ሄለን ኃ/ሚካኤል፥ ተጠርጣሪዋ መቅደስ ሞገስ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ የቆየች በመሆኑ ህጻኗ ስለምታውቃት አጋጣሚ ተጠቅማ የእገታ ወንጀሉን በመፈፀሟ ማዘናቸውን ገልጸዋል። በወቅቱ የልጃችንን መጥፋት ለአዲስ አበባ ፖሊስ ካመለከትን ጀምሮ ፖሊስ ቀን ከሌሊት ፍለጋውን በማድረግ ልጃችንን በእጃችን በማስገባቱ ወደር የሌለው ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል። " በስራው ለተሳተፉ በሙሉ ክብር ይገባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል። " ማንኛውም ዓይነት ወንጀል ፈፃሚዎች ለጊዜውም ቢሆን ከሰው ዓይንና ጆሮ ቢሰወሩም ከህግ ማምለጥ አይችሉም " ያለው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በስራው ተሳታፊ ለነበሩ የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እና የጎንደር ከተማ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ላደረጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኞችን ሲቀጥር ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እንዲሁም በአካባቢው ላይ የሚያያቸውን ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ለአቅራቢያ ፖሊስ መረጃ በመስጠት የህግ የበላይነትን ሊያረጋግጥ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ #AddisAbabaPolice ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

ቀን 25/12/2018 📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣 አስቸኳይ ክፍት የስራ ማስታወቂያ 09 03 01 00 06/09 57 97 40 82 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ:# NGO በሁሉም ዘርፍ 🍇የት/ደረጃ /ዲፕሎማ / ድግሪ 🍇የስራ ልምድ ፡- 0አመት 🍇ደሞዝ:- 25000_50000 🍇ፆታ:-   ወ/ሴ 🍇የሰራ ቦታ  አአ/ክልል 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው  መደብ =- የሰው ሀይል አስተዳደር 🍇የትምርት ደረጃ / ድግሪ 🍇ጾታ ወ/ሴ 🍇የስራ ልምድ 0-3 🍇ደሞዝ 10000+27000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ =- ሆስተስ 🍇የትምርት ደረጃ 10 + 🍇ጾታ ሴት 🍇የስራ ልምድ 0 አመት 🍇ደሞዝ 15000 / 25000+ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ =-ኢንጅነሪንግ 🍇የትምርት ደረጃ/ ድግሪ 🍇የስራ ልምድ 0/2 🍇ጾታ ወንድ /ሴት 🍇ደሞዝ 18000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ /ሆቴል ሱፐርባይዘር 🍇የስራ ልምድ ፡- 1/3 አመት 🍇ደሞዝ:-  13000/25000 🍇ፆታ:-   ወ/ሴ 🍇የሰራ ቦታ  አአ/ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ ስልክ ኦፕሬተር  🍇የት ደረጃ ፡ 10/12/ዲፕ 🍇ጾታ ሴ/ወ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0 -አመት  🍇ደሞዝ ፡ 16000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ:-ሹፌር ደ/1/2ህ/1/2ሞተረኛ 🍇የሰራ ልምድ :- 2-10አመት 🍇የት/ት ደረጃ :- 8/10/12 🍇ደሞዝ:- 7000_19000 🍇ፆታ :- ወንድ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ:- ትኬተር/ኦፊስላይ 🍇የሰራ ልምድ :- 0አመት 🍇የት/ት ደረጃ :- 10/12/ዲፕሎማ 🍇ደሞወዝ   :- 9000~14,000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ፦ሽያጭ /ለፈርኒቸር 🍇የት/ደረጃ፦10/12/diploma/ 🍇ደሞዝ:-8000_20000+ 🍇የስራ ልምድ: 0አመት 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ :markting 🍇የት ደረጃ ፡- degree  🍇የስራ ልምድ ፡- 0~3አመት 🍇ደሞዝ :-13000+ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ Accountant 🍇የት ደረጃ ፡ Degree/"Dip 🍇ፆታ: ሴ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0 - 8አመት 🍇ደሞዝ ፡  8,000-35,000  🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ IT 🍇የት/ደረጃ ፡-  degree /dip 🍇የስራ ልምድ ፡- 0 -2አመት 🍇ፆታ:- ሴ/ወ 🍇ደሞዝ:- 8000-15000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ፦ካሸር 🍇የት/ደረጃ፦10 + 🍇የሰራ ልምድ 0~3 አመት 🍇ደሞዝ:- 7000-14000 🍇ፆታ፦ሴ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ፦/መምህር በሁሉም 🍇የት/ደረጃ፦ዲፕልማ / ዲግሪ 🍇የስራ ልምድ: 0~2አመት 🍇ደሞዝ:- 10000+20000 🍇ፆታ፦ሴት/ወንድ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ ቡቲክ ሴልስ 🍇የት ደረጃ ፡ 8 🍇ፆታ: ሴ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0-1 🍇ደሞዝ :8000-20,000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ =- የጥፍር እና አይላሽ 🍇የትምርት ደረጃ 8+ 🍇የስራ ልምድ 0 -1 አመት 🍇ደሞዝ 20000+ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ=- ፀሀፊ 🍇የትምርት ደረጃ ዲፕሎም 🍇የስራ ልምድ ያላት 🍇ፆታ ሴት 🍇ደሞዝ 8000/25000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው አይነት =- ዱቄት ፋብሪካ ሁለገብ 🍇የትምርት ደረጃ 8/10/12 🍇የስራ ልድ 0 አመት 🍇ፆታ ሴት/ወንድ 🍇ደሞዝ 17000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራው መደብ =- ከስተመር ሰርቢስ 🍇የትምርት ደረጃ 8/10/12 🍇የስራ ልምድ 0 አመት 🍇ጾታ ሴት 🍇ደሞዝ 10000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ፦ሼፍ ዋና / እረዳት 🍇የት/ደረጃ፦ ሰርተፍኬት/ 🍇ደሞዝ:-9000-40000 🍇ፆታ፦ወንድ/ሴት 🍇የስራ ልምድ ፡ 0_5አመት 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ ሶፍት ፋብሪካ እሸጋ 🍇የት ደረጃ ፡ 8+ 🍇ጾታ ሴ/ወ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0 🍇ደሞዝ ፡  16000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ ሞባይል ቤት ሴልስ 🍇የ/ት ደረጃ ፡-8 🍇ጾታ ሴት 🍇የስራ ልምድ ፡- 0 /2አመት 🍇ደሞወዝ :- 10000+ኮምሽን 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ reception 🍇የት ደረጃ ፡ 10/12 🍇የስራ ልምድ ፡ 0-2 🍇ደሞዝ 8000/15000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ፦ ፍተሻ ፅዳት ለባንክ 🍇የት/ደረጃ፦8/12 🍇 የሰራ ልምድ 0 አመት 🍇ደሞዝ:- 5000 🍇የስራ ቦታ: በሰፈር አቅራብያ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇የስራ መደብ ፡ ጉዳይ አስፈፃሚ ፖስተኛ 🍇የት ደረጃ ፡ 10/12/"Dip 🍇ፆታ: ሴ/ወ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0-2አመት 🍇ደሞዝ ፡  15000 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 🍇ሀውስ ኪፒግ 🍇የት ደረጃ ፡ 8+ 🍇የስራ ልምድ ፡ 0-1አመት 🍇ደሞዝ ፡ 7000+ 🍇🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢🪢 ለበለጠ መረጃ 👇👇👇👇 አድራሻ:-  መገናኛ መተባበር ህንጻ 4 ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ B421 👇👇👇👇👇          ☎️ 09 57 97 40 82          ☎️ 09 03 01 00 06                09 97 47 03 84 https://t.me/familyWorke

ይህ ቪድዮ የሚረብሽ እና ስሜትን የሚነካ በመሆኑ በጥንቃቄ ይመልከቱ። በህንድ ሀገር በአንድ የግል ትምህርት ቤት የ6 ዓመት ህፃን በመምህሩ በጥፊ ከተመታ በኋላ ህይወቱ አልፏል። ክስተቱ በትምህርት ቤቱ የክፍል ውስጥ የደኅንነት ካሜራ ተቀርጾ ወጥቷል። መምህርቷ ህጻኑን " የቤት ስራ አልሰራህም " በማለት በጥፊ እንደመታችው ተገልጿል። በደህንነት ካሜራው ላይ እንደታየው ህፃኑ በመምህሩ በጥፊ ከመመታቱ በፊት ፣ በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ሆኖ ሲንቀጠቀጥና መምህሩን ሲለምን ነበር። በኋላ በጥፊ ከተመታ በኋላ ተዝለፍልፎ መምህርቷ ላይ ወድቋል። በሰዓቱ ርብርብ ተደርጎ ወደ ጤና ተቋም ቢወሰድም ህይወቱ ግን ሊተርፍ አልቻለም። የህጻኑ ሞት ትክክለኛ ምክንያትና በመምህሩ ድርጊት እና በህፃኑ ሞት መካከል ያለው ቀጥተኛ ግንኙነት በምርመራ እየተጣራ መኑን የህንድ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ክስተቱ በትምህርት ቤቶች ህፃናትን ከአካላዊ ቅጣት መጠበቅና የተማሪዎችን ደኅንነት ማረጋገጥ ላይ ጥያቄ ያስነሳና ዓለም አቀፋዊ መነጋገሪያ የሆነ ነው። @Tikfahethiopia

#USA 🇺🇸 #VISA የትራምፕ አስተዳደር 200 ሺህ የሚጠጉ የB1/B2 ቪዛዎችን ሊሰርዝ እና የH-1B ቪዛ ክፍያን ከ103 ሺህ ዶላር በላይ ለማድረስ ሀሳብ አቅርቧል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶና
+1
#USA 🇺🇸 #VISA የትራምፕ አስተዳደር 200 ሺህ የሚጠጉ የB1/B2 ቪዛዎችን ሊሰርዝ እና የH-1B ቪዛ ክፍያን ከ103 ሺህ ዶላር በላይ ለማድረስ ሀሳብ አቅርቧል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ወደ አሜሪካ በአጭር ጊዜ ጉብኝት (ቱሪስት) ወይም ቢዝነስ በB1 እና B2 ቪዛ ገብተው በኋላ የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ የውጭ ዜጎችን ቪዛ ለመሰረዝ እየሰራ መሆኑን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አስታውቋል። የመሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት፣ ቪዛን በመጠቀም የጥገኝነት ጥያቄ ማቅረብ የቪዛ ዓላማን መጣስ ሊሆን ስለሚችል የቪዛ መሰረዣ ምክንያት እንደሚሆን ገልጸዋል። ከ2016 እስከ 2026 ድረስ የተሰጡ B1 እና B2 ቪዛዎች ያላቸው የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ ወይም በሂደት ላይ ያሉ ሰዎች በእርምጃው ሊካተቱ እንደሚችሉ የመንግሥት ሰነዶችን በመጥቀስ የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ የቪዛ ስረዛው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በተከታታይ እንደሚከናወን ገልጿል። ከትራምፕ የሥልጣን ዘመን መጀመሪያ አንስቶ ከ175 ሺህ በላይ የውጭ ዜጎች ቪዛ በተለያዩ ምክንያቶች መሰረዙ ተነግሯል። በተያያዘ መረጃ፥ የአሜሪካ የሆምላንድ ሴኩሪቲ መሥሪያ ቤት (DHS) ለH-1B ቪዛ አመልካቾች 103,265 ዶላር የሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ሀሳብ አቅርቧል። H-1B ቪዛ የአሜሪካ ኩባንያዎች ከፍተኛ ሙያ ያላቸውን የውጭ ዜጎች ለመቅጠር የሚጠቀሙበት የሥራ ቪዛ ሲሆን በተለይም በቴክኖሎጂና በጤና ዘርፎች በስፋት ይጠቀሙበታል። የ103,265 ዶላር ክፍያው እስካሁን የጸደቀ ሕግ ሳይሆን የቀረበ ሀሳብ ነው። ተግባራዊ ከሆነም በዓመት 85,000 የH-1B የኮታ ማመልከቻዎች ላይ ተመስርቶ ወደ 8.8 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል መ/ቤቱ ገምቷል። ክፍያውን የሚከፍለው የውጭ ሠራተኛው ሳይሆን የH-1B ማመልከቻውን የሚያቀርበው አሠሪ ነው። ሆኖም ሀሳቡ ከኮታ ነፃ በሆኑ የH-1B ማመልከቻዎች፣ በአንዳንድ የምርምር ተቋማትና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚቀርቡ ማመልከቻዎች እንደማይተገበር ተገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

#JalalGirma👏 የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ በ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 591. 6 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደ
+1
#JalalGirma👏 የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ በ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 591. 6 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል። #ODA_SPECIAL_BOARDING_SCHOOL @tikvahethiopia

ዉጤት እንዲታይላቹ admision number እና የመጀመርያ ስም ፊደል ሳይሳሳት ላኩ

ዉጤት ለማየት network ያስቸገራቹ comment ላይ ፃፉልን

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል። ውጤት ለማየት ፦ 👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et 👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram 👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም @tikfahethiopia

" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች  ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል። ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም @tikfahethiopia

ተጨማሪ የድሮን ጥቃት በትግራይ በትግራይ ክልል አጽቢ ወረዳ ሌሊት 7:30 የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ተሰምቷል። በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት በሁለት ዞኖች ላይ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል። ባለፉት ተከታታይ
ተጨማሪ የድሮን ጥቃት በትግራይ በትግራይ ክልል አጽቢ ወረዳ ሌሊት 7:30 የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ተሰምቷል። በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት በሁለት ዞኖች ላይ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል። ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት በፌዴራል መንግስት በኩል ሕወሓት ላይ የአየር ጥቃቶች እየተፈጸሙ ቢሆንም፤ መንግሥት ግን እስካሁን ስለ ጥቃቶቹ ያለው ነገር የለም። @tikfahethiopia

የገዱ አንዳርጋቸው ንጹህ እንጀራ ። ከመሸ ፌስቡክ ላይ የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዝደንት ኋላ ላይም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ፡ በሀገረ አሜሪካን የፓ
የገዱ አንዳርጋቸው ንጹህ እንጀራ ። ከመሸ ፌስቡክ ላይ የቀድሞው የአማራ ክልል ፕሬዝደንት ኋላ ላይም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ፡ በሀገረ አሜሪካን የፓርኪንግ ስራ ሲሰሩ የሚያሳይ ቪዲዮ አየሁ ። ........ አደለም የአንድ ክልል ፕሬዝደንት ፡ አደለም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበረ ሰው ይቅርና ፡ ተራ የገቢዎችና ጉምሩክ ሰራተኛ እንዲሁም በተለያየ የመንግስት ቢሮዎች ያሉ ሃላፊዎች ዱባይ ውስጥ ቪላ በሚገዙበት ዘመን ። ተራ ባለስልጣን በዘመድ አዝማዱ ስም ሚሊዮኖችን በባንክ በሚያስቀምጥበት ጊዜ ፡ የሀገርን ሀብት በውጭ ባንኮች የሚያስቀምጡ እልፍ ባለስልጣኖች ባየንበት ዘመን ፡ ልጆቻቸውን በአውሮፓና አሜሪካ የሚያስተምሩ ሙሰኞች በሞሉበት ጊዜ ፡ ደጉ አንዳርጋቸው የሚባል ሰው ፓርኪንግ እየሰራ ይገኛል ሲባል የማይገረም ማን ይኖራል ? ..... አቶ ገዱ ስለሚያራምደው ፓለቲካዊ አመለካከትም ሆነ ሌላ ነገር ግድ የለኝም ። በስልጣን በነበረበት ጊዜ ከዚች ድሀ ሀገር ሳይዘርፍ በመኖሩ ግን በአክብሮት እጅ ለመንሳት እገደዳለሁ ። ማንም ሰው ይህን አለማድነቅ አይችልም ። አቶ ገዱ ቢፈልግኮ ይህኔ በአሜሪካን ባንኮች መቶ ሚሊዮኖችን ማስቀመጥ ይችል ነበር ። ሆኖም አላደረገውምና ዛሬ ላይ ፓርኪንግ ተቀጥሮ እየሰራ የሰላም እንቅልፍ ተኝቶ ያድራል ። .... የገዱ ንፁህ እንጀራ ያስቀናል ፡ በሙስና ያልቆሸሸ ፡ ከድሃ ሀገር ከተዘረፈ ገንዘብ ጋር ያልተነካካ ንፁህ እንጀራ ። @tikfahethiopia

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አልተደረገም። የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት መለቀቁን በመግለጽ ተማሪዎችና ወላጀችን የሚያደናግር ሀሰተኛ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ። እስካሁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ የፈተናው ውጤት ይፋ ስለመደረጉ በይፋ አላሳወቀም። ትክክለኛ የተረጋገጡ መረጃዎች ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ የሚገኙ በመሆኑ ተማሪዎች እና ወላጆች ሀሰተኛ መረጃዎችን ከሚያሰራጩ የተለያዩ አካላትና ገጾች ትጠነቀቁ ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት ያስተላልፋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የፈተናው ውጤት ሰኞ ወይም እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል። ውጤት ሰኞ ዕለት ይፋ ያልተደረገ ሲሆን እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። የፈተናው ውጤት ይፋ ሲደረግ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ በይፋ የሚያሳውቅ ሲሆን እንዴት ማየት እንደሚቻልም ተቋሙ ገለጻ ያወጣል። እኛም ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ #TikvahEthiopiaFamily @tikfahethiopia

በኦሮሚያ ክልል የደገም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በታጣቂዎች ተገደሉ! የደገም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ተፈራ ደሴየፎቶው ባለመብት,Paartii Badhaadhinaa Damee Dagam በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደገም ወረዳ ታጣቂዎች ትናንት እሁድ ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም. በፈጸሙት ጥቃት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ተፈራ ደሴ መገደላቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ። በጥቃቱ በወረዳው የምትገኘው አኖ ቀሬ ቀበሌ ሊቀ መንበር አስፋወሰን ኃይሌን ጨምሮ ሌሎች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል። የዞኑ የፀጥታ መዋቅር ምንጮች ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ እንደተናገሩት፣ ዋና አስተዳዳሪው የተገደሉት እሁድ ከሰዓት በኋላ ሲሆን ጥቃት የተፈጸመው በደገም ወረዳ አኖ ቀሬ ቀበሌ ውስጥ ነው። በዕለቱ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እና በታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር ምንጮቹ አስረድተዋል። የቀበሌ ሊቀ መንበሩን ጨምሮ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና እያገኙ መሆኑንም ጠቅሰዋል። ቢቢሲ ያነጋገራቸው ምንጮች፣ በመንግሥት ባለሥልጣናቱ ላይ ለተከፈተው ጥቃት ተጠያቂ ያደረጉት በክልሉ የሚንቀሳቀሱትን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ታጣቂዎችን ነው። ታጣቂ ቡድኑ እስካሁን ስለ ጥቃቱ መረጃ ያለው ነገር የለም። የደገም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የአቶ ተፈራን መገደል በተመለከተ ከክልሉ መንግሥትም ይሁን ከሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር የተሰጠ አስተያየት የለም። ቢቢሲ ከዞኑ ዋና አስተዳደሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም። በክልሉ በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ባለልጣናትን ዒላማ ያደረገ ጥቃት ሲፈጸም ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በየካቲት 2017 ዓ.ም. ሱሉልታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አበበ ወርቁ በታጣቂዎች መገደላቸው ይታወሳል። መንግሥት በሽብር ቡድንነት የፈረጀው እና 'ሸኔ' ብሎ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በወቅቱ በወጣው መግለጫው ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። በዚያው ዓመት ታኅሣሥ ላይ ደግሞ የዞኑ የውሃ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ስዩም አበራ፣ የዞኑ አደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን እጄታ እና የዞኑ የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ግዛው ተገድለዋል። ጥቅምት ላይ በተመሳሳይ የወጫሌ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት ንጉሤ ኮሩን ጨምሮ ከ45 በላይ ሰዎች የሚሆኑ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግረው ነበር። Via BBC @Tikfahethiopia

ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikfahethiopia

ከፍተኛ ውጤት ! በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 576.2 ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ት/ቤት ተመዝግቧል። በሴት 569.1 ከቦሌ ሱፐር ሆሊሴቪየር ት/ቤት ተመዝግቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
ከፍተኛ ውጤት ! በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 576.2 ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ት/ቤት ተመዝግቧል። በሴት 569.1 ከቦሌ ሱፐር ሆሊሴቪየር ት/ቤት ተመዝግቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikfahethiopia