en
Feedback
The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ የቴሌግራም ግሩፕ ነው። በእናንተ እገዛ ለ34 ዓመታት ለ5,000 በላይ ሕፃናት መድረስ ችለናል፣ አሁንም ግን ብዙ ሕፃናት ይጠብቁናል። #6710 ላይ OK ብለው SMS በመላክ በቀን 1 ብር ይለግሱ! 0977909090 / 0115513636 አድራሻዎቻችን 👉 https://linktr.ee/chfe

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 864
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
https://youtu.be/8rjhn4Mvmuc ‹‹ሙከሚል ከማል ገና ከጥቁር ሆስፒታል እንደወጣ ከአውቶቢስ ተራ ጳውሎስ ሆስፒታል ድረስ የደስታውን በእግሩ ነው የሄደው፡፡ ድሮ ከታክሲ ወርዶ ትንሽ እንኳን መንቀሳቀስ አይችልም ነበር፡፡ያን ቀን ግን ወደ ቤትም አልገባንም፡፡ ትንሽ እርቀት እራሱ ተሸከመነው ነበር የምንጓዘው፡፡በጣም እናመሰግናለን!!!!!››ይለናል የሙከሚል ከማል ወንድም ከህክምናው በኋላ ስንጨዋወት ፡- በብዙ ቅን ልባም ኢትዮጵያውያን ድጋፍ የብዙ ወላጆች ሳቅ ተመልሷል፡፡ ለመጫወት፣ ለመማር፣ ለመቦረቅ ችለዋል፡፡ ለዚህም ደግሞ ትልቁ ምክንያት እናንተ ለልብ የደረሳችሁ ልባም ኢትዮጵያን ናችሁ፡፡ አሁንም ከሰባት ሺህ በላይ ሕፃናት ለመማር፣ እንደ እኩዮቻቸው ለመጫወት፣ እንደልባቸው ለመንቀሳቀስ ሳይችሉ ከሕመማቸው ጋር ሆነው ከዛሬ ነገ እንድናለን በማለት በተስፋ ወረፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም እኚህን የነገ ተስፋ ለማዳን ስልካችንን አውጥተን 6710 ላይ A B C D ብለን የተሰበሩ ልቦችን እንጠግን 1 ብር ለ 1 ልብ፡፡ እናመሠግናለን!!!! #CCE #CHFE

What a delight it was for all of us here at Cardiac Center Ethiopia to have her excellency Vera Songwe, Executive Secretary of UNECA, and staff representatives of the Economic Commission for Africa. Thank you for your generous donation of 800,000 ETB to mend broken hearts. #UNECA #Cardiac_Center_Ethiopia #6710_A_B_C_D

የምስራች! የልብ ሕሙማን ሕፃናትን የሚደግፉበት አዲስ አማራጭ በgofundme! በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ከሀገር ውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ማድረግ የሚችሉበት አዲስ አማራጭ የሆነውን #የgofundme የድጋፍ ማሰባሰቢያ በድርጅቱ ስም የከፈተ ሲሆን፤ ከኢትዮጵያ ውጪ ያላችሁ ልባም ኢትዮጵያውያን ከዚህ በታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመከተል ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በታካሚ ሕፃናቱ ስም በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ 👉https://gofund.me/2e33c5c4 👉ለብዙሃን እንዲደርስ #Share በማድረግ ይተባበሩን! 💖የተሰበሩ ልቦችን በጋራ እንጠግን

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የዒድ አል አድሃ በዓል አደረሳችሁ! #eiduladha

እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያልን  ዘመኑ የሰላም፣ የጤና እና የስኬት እንዲሆንላችሁ  እንመኛል። መልካም አዲስ አመት!!!