en
Feedback
The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ የቴሌግራም ግሩፕ ነው። በእናንተ እገዛ ለ34 ዓመታት ለ5,000 በላይ ሕፃናት መድረስ ችለናል፣ አሁንም ግን ብዙ ሕፃናት ይጠብቁናል። #6710 ላይ OK ብለው SMS በመላክ በቀን 1 ብር ይለግሱ! 0977909090 / 0115513636 አድራሻዎቻችን 👉 https://linktr.ee/chfe

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 864
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Channel Posts
2
የራዲሰን ብሉ ሆቴል የምሳ ግብዣ በልብ ማዕከል! በተለያዩ መንገዶች የልብ ሕሙማንን በመደገፍ ከማዕከላችን ጎን የሆነው ራዲሰን ብሉ ሆቴል ባሳለፍነው ሳምንት በማዕከላችን ተገኝቶ በዕለቱ ለልብ ሕክምና ክትትል ለመጡ ታካሚዎች፣ ቤተሰቦቻቸው እና የማዕከሉ ሠራተኞች የምሳ ግብዣ አከናውኗል፡፡ ራዲሰን ብሉ ሆቴል ከዚህ ቀደም ከተለያዩ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የልብ ቀዶ ሕክምና ለሚያከናውኑ የሕክምና ቡድኖች የሆቴሉን ማረፊያ ክፍሎች በነፃ እና በቅናሽ በመፍቀድ የበርካታ ሕፃናት ሕይወት መዳን አስተዋፅዎ ማድረግ የቻለ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንትም የማዕከሉን እንቅስቃሴዎች በመጎብኘት እና የምሳ ግብዣ በማድረግ በርቱ ብሎናል፡፡ ራዲሰን ብሉ ሆቴል ማህበራዊ ኃላፊነቱ በመወጣት ምሳሌ መሆን የሚችል ተግባር በማከናወኑ እና የልብ ሕሙማን አጋር በመሆኑ በታካሚ ሕፃናቱ ስም ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ #ድጋፋችሁ_አይለየን #የተሰበሩ_ልቦችን_በጋራ_እንጠግን #6710_ok #አንድ_ብር_ለአንድ_ልብ
0
3
No text...
0
4
እንኳን ለ1444ኛው የረመዳን ፆም አደረሳችሁ! ካለን ላይ የምናካፍልበት ወር እንዲሆን እንመኛለን፡፡ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ #6710_ok #1ብርለ1ልብ
0
5
No text...
0
6
የምስራች! 6710 ከA/B/C/D ወደ “OK” ተቀይሯል! በኢትዮቴሌኮም ድጋፍ ለልብ ሕሙማንን የምንለግስበት 6710 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ከዚህ በፊት ከ 1 ብር እስከ 100 ብር ድጋፍ የሚደረግበት A/B/C/D አማራጭ በእናንተ በልባም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ወደ “OK” መቀየሩን ለማብሰር እንወዳለን፡፡ አሁን👇 አንድ ጊዜ ብቻ “OK” ብለው ወደ 6710 በመላክ እና በመመዝገብ በቀን አንድ ብር ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ፡፡ #6710_OK📨 #አንድ_ብር_ለአንድ_ልብ!💖 ይህንን መልዕክት በማጋራት ለብዙሃን እንድንደርስ ያግዙን፡፡ እናመሰግናለን🙏
0
7
ለ፡ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አዲስ አበባ ጉዳዩ፡ የልብ ሕሙማን ሕፃናትን ሕይወት ለመታደግ የሚያስችል ትብብርን ይመለከታል በቅድሚያ የማክበር ሠላምታችንን እያቀረብን ድርጅታችን በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ መንግስታዊ ያልሆነ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሆኖ ከተቋቋመበት 1981 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 34 ዓመታት የልብ ቀዶ ሕክምናን ለሕፃናት በነፃ በመስጠት፣ በርካታ ሕፃናትን ወደ ውጭ ሀገር በመላክ እና ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ አዲስ አበባ ውስጥ በሕብረተሰቡ እና በልባም ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ባስገነባው የልብ ማዕከል ውስጥ አገልግሎቱን በነፃ መስጠት የቻለ ድርጅት ነው፡ በአሁኑ ወቅት የልብ ማዕከል የጀመራቸውን ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎቶች በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን በአላቂ የሕክምና እቃዎች እጥረት እና በቋሚ ገቢ አለመኖር ምክንያቶች ግን ከሙሉ አቅሙ አንድ ሶስተኛውን ብቻ በመጠቀም በዓመት 500 የሚሆኑ ሕፃናትን ሕይወት ብቻ በመታደግ ላይ ይገኛል፡፡ ይህንን ዓመታዊ ቁጥር በመጨመር ወረፋ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ከ7,400 በላይ የሚጠጉ ታካሚዎችን ሕይወት ለማዳን አሁንም የተለያዩ አካላት ድጋፍ እና አጋርነትን በመጠየቅ ላይ ይገኛል፡፡
0
8
No text...
0
9
No text...
0
10
No text...
0
11
No text...
0
12
የረውማቲክ የልብ በሽታ እንዳይባባስ የሚረዳውን በመርፌ የሚሰጥ ህክምና (ቤንዛቲን ፔኒሲሊን) አስመልክቶ አጭር መረጃ እነሆ! ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ(link) በመጫን ያንብቡ ለሌላ ወዳጆም ያጋሩ፡፡ https://chfe.org.et/about-benzathine-penicillin/
0
13
𝐌𝐞𝐧𝐝 𝐚 𝐡𝐞𝐚𝐫𝐭, 𝐬𝐚𝐯𝐞 𝐚 𝐜𝐡𝐢𝐥𝐝! The Children's Heart Fund of Ethiopia is now accepting donations via GoFundMe. 💖Donate here 👉 https://gofund.me/ec75c6c4 #gofundmecampaign
0
14
#የቅን_መንገድ አባላት ለልብ ማዕከል የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ! በወ/ሮ ሂወት ታደሰ አስተባባሪነት የተሰባሰቡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፤ ማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸውን በመጠቀም ከዚህ ቀደም ካበረከቱት የ284 ሺህ ብር እገዛ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት የ500 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል። ወ/ሮ ሂወት ታደሰ እና የቅን መንገድ አባላት ቅን ልባችሁን ልብ ለሚሹ ሕፃናት በመስጠታችሁ ከልብ እናመሰግናለን! #CCE | #CHFE | #6710_A_B_C_D
0
15
https://youtu.be/8rjhn4Mvmuc ‹‹ሙከሚል ከማል ገና ከጥቁር ሆስፒፒል እንደወጣ ከአውቶቢስ ተራ ጳውሎስ ሆስፒታል ድረስ የደስታውን በእግሩ ነው የሄደው፡፡ድሮ ከታክሲ ወርዶ ትንሽ እንኳን መንቀሳቀስ አይችልም ነበር፡፡ያን ቀን ግን ወደ ቤትም አልገባንም፡፡ ትንሽ እርቀት እራሱ ተሸከመነው ነበር የምንጓዘው፡፡በጣም እናመሰግናለን!!!!!››ይለናል የሙከሚል ከማል ወንድም ከህክምናው በኋላ ስንጨዋወት ፡- በብዙ ቅን ልባም ኢትዮጵያውያን ድጋፍ የብዙ ወላጆች ሳቅ ተመልሷል፡፡ ለመጫወት፣ ለመማር፣ ለመቦረቅ ችለዋል፡፡ ለዚህም ደግሞ ትልቁ ምክንያት እናንተ ለልብ የደረሳችሁ ልባም ኢትዮጵያን ናችሁ፡፡ አሁንም ከሰባት ሺህ በላይ ሕፃናት ለመማር፣ እንደ እኩዮቻቸው ለመጫወት፣ እንደልባቸው ለመንቀሳቀስ ሳይችሉ ከሕመማቸው ጋር ሆነው ከዛሬ ነገ እንድናለን በማለት በተስፋ ወረፋ እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም እኚህን የነገ ተስፋ ለማዳን ስልካችንን አውጥተን 6710 ላይ A B C D ብለን የተሰበሩ ልቦችን እንጠግን 1 ብር ለ 1 ልብ፡፡ እናመሠግናለን!!!! #CCE #CHFE
0
16
No text...
0
17
No text...
0
18
No text...
0
19
ፈረስ ትራንስፖርት በዛሬው ዕለት የብር 365,974.45 የገንዘብ ድጋፍ ለልብ ሕሙማን አበርክቷል! የገንዘብ ድጋፉ የፈረስ ቤተሰቦች አገልግሎቱን በመጠቀም ያሰባሰቡትን የፈረስ ማይልስ ለአንድ ዓመት ያህል መተግበሪያውን በመጠቀም የለገሱት ሲሆን፣ ይህንንም ድጋፍ ፈረስ ትራንስፖርት በዛሬው ዕለት በራዲሰን ብሉ ሆቴል ባዘጋጀው የማስረከቢያ መርሀግብር ላይ የድርጅታችን የበጎ ፈቃድ አምባሳደር አርቲስት መሠረት መብራቴ እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት አበርክቷል። ፈረስ ከልብ ሕሙማን በተጨማሪ ለሌሎች የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ግለሰቦችም የገንዘብ ድጋፉን ያበረከተ ሲሆን በአጠቃላይ ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ተደርጓል። የፈረስ ትራንስፖርት መተግበሪያን በመጠቀም ይህንን ድጋፍ ላበረከታችሁ ልባም ኢትዮጵያውያን ብሎም ይህንን አማራጭ በማዘጋጀት የበጎ አድራጎቶች አጋር መሆኑን ያስመሰከረውን ፈረስ ትራንስፖርት በልብ ሕሙማን ሕፃናቱ ስም ከልብ እናመሰግናለን!
0