en
Feedback
The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ የቴሌግራም ግሩፕ ነው። በእናንተ እገዛ ለ34 ዓመታት ለ5,000 በላይ ሕፃናት መድረስ ችለናል፣ አሁንም ግን ብዙ ሕፃናት ይጠብቁናል። #6710 ላይ OK ብለው SMS በመላክ በቀን 1 ብር ይለግሱ! 0977909090 / 0115513636 አድራሻዎቻችን 👉 https://linktr.ee/chfe

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 864
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"የእምዬ ማዕድ ለልጆቻችን" በመባል የሚታወቀው የፌስቡክ ግሩፕ አባላት የልብ ሕሙማን ሕፃናትን ለመርዳት ቀጠሮ ይዘዋል! ከአንድ መቶ ሺህ በላይ አባላት ያሉት ይህ ግሩፕ እናቶች ለልጆች ጠቃሚ የሆኑ ማዕዶችን እና ተያያዥ ምክሮችን የሚለግሱበት እና የሚጠይቁበት ሲሆን በግሩፑ ውስጥ በሚደረጉ የመረጃ ልውውጦችም ብዙሃን እናቶች በርካታ ጥቅሞችን እንዳገኙ ይመሰክራሉ፡፡ በአሁኑ ወቅትም የግሩፑ አባላት ስብስባቸውን ለበጎ አላማ ለማዋል እና የልብ ሕሙማንን ለመርዳት የሚያስችል ገንዘብ በማሰባሰብ በመጪው እሁድ ሐምሌ 17 ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በልብ ማዕከል በመገኘት ድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ በዕለቱም ማዕከሉን የመጎብኘት፣ የበጎ ፍቃድ የደም ልገሳ እና የልብ እና ተያያዥ በሽታዎች ቅድመ ምርመራ መርሃ ግብሮች የሚካሄዱ ይሆናል፡፡ የግሩፑ አባላት ይህንን መርሃ ግብር በማዘጋጀታቸው በታካሚ ሕፃናቱ ስም እያመሰገንን፤ የሚዲያ አካላት አባላቱ የማህበራዊ ትስስር ገፅን በመጠቀም በመሰረተቱት ስብስብ የሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚያደርጉትን በጎ ተግባር በአካል በመገኘት ለህዝብ እንድታደርሱልን በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ

ጥንዶቹ 250 ሺህ ብር ለግሰዋል! ባሳለፍነው ሳምንት የጋብቻ ስነ ስርዓታቸውን የፈፀሙት አቶ ሳሙኤል ግርማ እና ወ/ሮ ፌቨን ዓሊ ከሠርጋቸው ወጪዎች ላይ በመቀነስ፣ የሚዜ ወጪዎችን በማስቀረት እና ለጋብቻቸው ከወዳች ዘመድ የሚበረከትላቸውን ስጦታዎች ለልብ ሕሙማን ድጋፍ ይውል ዘንድ በማሰባሰብ በዛሬው ዕለት ብር #250_ሺህ የገንዘብ ድጋፍ አበርክተውልናል፡፡ ይህን የበጎ ምግባር ተምሳሌት የሚሆን ሃሳብ ተግባር ላይ በማዋል የሕፃናትን ሕይወት ለማዳን ላደረጋችሁት ድጋፍ ከልብ እያመሰገንን ለዚህ ድጋፍ አስተዋፅዎ ያበረከታሁ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ ዕጩ ሚዜዎች እና ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ በታካሚ ሕፃናቱ ስም ምስጋና እና አክብሮታችን ይድረሳችሁ፡፡ ትዳራችሁ የአብርሃም እና የሳራ ይሁን! #እናመሰግናለን | #thankyou #wedding #donation

በዛሬው ዕለት የRotary Club of A.A. East አባላት የ55,000 ብር እንዲሁም MC Bauchemie Manufacturing PLC የ100,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ ለማዕከላችን አበርክተዋል፡፡ በበጎ ፍቃድ ተግባሮቹ እና በበጎ አድራጎት እንቅስቃሴዎቹ የሚታወቀው Rotary፣ በልብ ሕመም የሚሰቃዩ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን ከልብ ሕሙማን ጋር በጋራ ለመስራት ያለውን ፍላጎት እና ተነሳሽነት ስለገለፃችሁልን እና ይህንን ድጋፍ በጋራ ስላበረከታችሁ በታካሚ ሕፃናቱ ስም ከልብ እናመሰግናለን፡፡ #ROTARY_ETHIOPIA | #CHFE

ለወላጆች የሚጠቅም የቴሌግራም ቻናል እንጠቁማችሁ፡፡ በልብ ማዕከል ከሚገኙ አንጋፋ የሕፃናት የልብ ኃኪሞች መካከል አንዱ በሆነው ዶ/ር አዘነ ደሴ እየተዘጋጁ የሚቀርቡ፤ በሕፃናት ጤና፣ አስፈላጊ ጥንቃቄ እና ሕክምናዎች ላይ የሚያተኩሩ መረጃዎች የሚቀርቡበት “ጤናማ ሕፃን ለብርቱ ዜጋ” የተሰኘ የቴሌግራም ቻናል ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠርያ በመጫን እንድትቀላቀሉ እንጋብዛለን፡፡ https://t.me/child_health

ጋዜጠኛ ነጋሽ መሐመድ ለልብ ማዕከል የገንዘብ ድጋፍ አደረገ! የጀርመኑ ዓለምአቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ዶይቼ ቬለ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ምክትል ኃላፊ የሆነው አንጋፋው ጋዜጠኛ ነጋሽ መሐመድ በዚህ ሳምንት በማዕከላችን ተገኝቶ ጉብኝት ያደረገ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ራድዮ ዓለም አቀፍ የራድዮ ቀንን ባከበረበት እና በሕይወት ዘመን የራድዮ ጋዜጠኝነት ሆኖ በተሸለመበት ወቅት የተበረከተለትን የ50 ሺህ ብር ሽልማት ለልብ ሕሙማን ይውል ዘንድ አበርክቷል፡፡ ስለ ልብ ሕመም በቅርበት እንደሚያውቅ ያጫወተን ጋዜጠኛ ነጋሽ በሚኖርበት የጀርመን ሃገር ድጋፎችን በማሰባሰብ እና አስፈላጊ ትብብሮችን በማድረግ የልብ ሕሙማንን እንደሚያግዝም ቃል ገብቶልናል፡፡ ጋዜጠኛ ነጋሽ መሐመድ ላበረከተው የገንዘብ ድጋፍ እና ገንቢ አስተያየቶቹ በታካሚ ሕፃናቱ ስም ከልብ እናመሰግናለን፡፡

ለልብ ከልባቸው የሚተጉት ሃኪሞቻችን! ዛሬም ግንቦት 15 ቀን ዓም ከጠዋት ጀምሮ እንደ ሁልጊዜውም የተሰበሩ ልቦችን በመጠገን ላይ ይገኛሉ። እርሶም  ከ 7500 በላይ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ያሉትን ሕፃናትን ልብ  መጠገን ይችላሉ። በቀላሉ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ወደ 6710 'OK'  በለው በመላክ እንዲሁም በቴሌብር ወደ 0977909090 ድጋፍ በማድረግ የሕፃናቱን ህይወት ለማዳን በሚደረገው ርብርብ ላይ የራስዎን አስተዋፃኦ ያብርክቱ። #1ብር1ልብ   #እናመሰግናለን #የተሰበሩልቦችንበጋራእንጠግን

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1441ኛው የረመዳን ፆም አደረሳችሁ መልካም የፆም ወቅት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

እንኳን ለ126ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ። መልካም የድል ቀን! #CHFE | #CCE | #ADWA

📢የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ሕፃናት መርጃ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን አዋጅ ቁጥር 1113/2011 መሠረት በመዝገብ ቁጥር 0518 ዳግም ተመዝግቦ ህጋዊ ሰውነት የተሰጠው የበጎ አድራጎት ድርጅት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በአዋጁ መሠረት በየዓመቱ የጠቅላላ ጉባኤ መደበኛ ጉባኤ መደረግ ያልበት በመሆኑ የ2021 ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን #ቅዳሜ #መጋቢት_17 ቀን 2014 ዓ.ም. ያደርጋል፡፡ በዚሁ መሠረት የጠቅላላ ጉባኤው አባላት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው የልብ ማዕከል ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ጥሪውን ያቀርባል፡፡ #በኢትዮጵያ_የልብ_ሕሙማን_ሕፃናት_መርጃ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! #6710_ok