The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ
Open in Telegram
ይህ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ የቴሌግራም ግሩፕ ነው። በእናንተ እገዛ ለ34 ዓመታት ለ5,000 በላይ ሕፃናት መድረስ ችለናል፣ አሁንም ግን ብዙ ሕፃናት ይጠብቁናል። #6710 ላይ OK ብለው SMS በመላክ በቀን 1 ብር ይለግሱ! 0977909090 / 0115513636 አድራሻዎቻችን 👉 https://linktr.ee/chfe
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 864
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሙሉ ገቢው ለልብ ሕሙማን የሚውለው “#ቃል” የግጥም መድብል በገበያ ላይ ውሏል!
ኑሮውን በውጭ ሃገር ያደረገው ገጣሚ #አብዱልአዚዝ_ዩሱፍ “ቃል” ብሎ የሰየመውን የመጀመሪያ የግጥም መድብሉን አሳትሞ ለሽያጭ በማቅረብ ሙሉ ገቢውን ለልብ ሕሙማን ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ድጋፍ ለማድረግ አበርክቶልናል፡፡
የሞያ አስተዋፅዎ በማድረግ የሕፃናትን ሕይወት ማዳን እንደሚቻል በማመን ለጀመራቸው እንቅስቃሴዎች በታካሚ ሕፃናቱ ስም ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን የግጥም መድብሉን ፒያሳ ሴካ የገበያ ማዕከል፣ ስድስተኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 003 ወይም በ0953909577/0932174470 ስልክ ቁጥሮች ላይ በመደወል ማግኘት ስለምትችሉ ገዝታችሁ እንድታነቡት በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡
#CHFE | #CCE | #KAL
እንኳን አደረሳችሁ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ እህትና ወንድሞቻችን መልካም የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ #ከልብ እንመኛለን።
We wish all our Muslim brothers and sisters a happy, healthy and safe #EidAlAdha. May you all enjoy celebrations and prayers.
#EidMubarak
#EidAlAdha
#CardiacCenterEthiopia
#6710_A_B_C_D
የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃን ለማገዝ የትኛውን አማራጭ ይመርጣሉ?
እንኳን ለታላቁ የረመዳን የፆም ወቅት አደረሳችሁ!
የተሰበሩ የሕፃናት ልቦችን በዚህ የፆም ወቅት እንድታስቧቸው ጥሪ እናቀርባለን።
ረመዳን ሙባረክ!
#ramadan2022 | #CHFE | #CCE
አንድ ብር ለአንድ ልብ!
ወዳጅ ዘመድዎ ወደ 6710 OK ብለው እንዲልኩ በመጋበዝ ሕይወት ይታደጉ፡፡
ኢትዮ ቴሌኮምን እናመሰግናለን፡፡
#6710_ok
#አንድ_ብር_ለአንድ_ልብ
#የተሰበሩ_ልቦችን_በጋራ_እንጠግን
ስለ ሕፃናት የልብ ሕመም ከዶ/ር ያየህይራድ መኮንን ጋር #EBC ጤናዎ በቤትዎ
https://youtu.be/YfzorVYLmR0
በትላንትናው እለት በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ እና People To People በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በበይነመረብ ላይ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ (Virtual Meeting) የPeople To People መስራች ፕ/ር እናውጋው መሀሪ እና ሌሎች አባላት፣ ክቡር አምባሳደር ፍፁም አረጋ፣ ፕ/ር አፈወርቅ ካሱ ከሌሎች የልብ ሕሙማን ህፃናት መርጃ ተወካዮች ጋር እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፎ አድርገዋል።
ውይይቱ ወቅታዊ የልብ ማዕከል እንቅስቃሴን በመቃኘት የተጀመረ ሲሆን #ዘላቂ_የሆነ_ፋይናንሺያል_አቅም_መፍጠርን፣ #የምርምር_እና_ትምህርት_ግንኙነቶች_ማዘጋጀትን፣ #የገቢ_ማሰባሰቢያ_ዝግጅቶች_ማቀድን፣ #በቂ_የአላቂ_እቃ_አቅርቦት_ማግኘት_የሚቻልባቸው_እንቅስቃሴዎች_ማድረግ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱ ሁሉም ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን አቅርበው እና መጀመር ስላለባቸው እንቅስቃሴዎች ስምምነት ላይ ተደርሶ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
ይህ ግንኙነት ለድርጅታችን ትልቅ ተስፋ ሰጪ ጅምር ነውና ዕቅዶችን ወደ ተግባር በመቀየር የበርካታ የኢትዮጵያ ሕፃናትን ህይወት መታደግ እንደምንችል ባለሙሉ ተስፋ እና ቁርጠኛ መሆናችንን እየገለፅን ለPeople To People እና በውይይቱ ተሳታፊ ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
#peopletopeople | #CHFE | #cardiaccenterethiopia
የምስራቹን ያጋሩ!
በውጭ ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን PayPal በመጠቀም የልብ ሕሙማን ሕፃናትን መደገፍ የሚችሉበት አማራጭ ተፈጥሯል፡፡
ከስር የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጫን በቀጥታ ወደ ልብ ሕሙማን የPayPal ሒሳብ ድጋፍ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን ለማብስር እንወዳለን፡፡
https://www.paypal.com/donate/?hosted_button_id=NC357U2ATL4BW
መልዕክቱ ለብዙሃን እንዲደርስ ያጋሩት!
#PayPal | #donation
