en
Feedback
Customs Transit, ESW service/የትራንዚትና የኤሌክትሮኒክ አንድ መስኮት አግልግሎት

Customs Transit, ESW service/የትራንዚትና የኤሌክትሮኒክ አንድ መስኮት አግልግሎት

Open in Telegram

በኢትዮጵያ ከኤሌክትሮኒክ ንግድ(E-commerce)፣ ኤሌክትሮኒክ ፊርማ፣የኤሌክትሮኒክ አንድ መስኮት አገልግሎት(ESW System)፣የኤሌክትሮኒክ ጉሙሩክ አስተዳደር ስርዓት(ECMS)፣ ሌሎች መ/ቤቶች በኤሌክትሮኒክ ስርዓት ስለሚሰጡት አገልግሎት መረጃ በጽሁፍ፣በድምጽና በምስል ይቀርብበታል፣ ውይይት ይደረግበታል፡፡ የተቀላጠፈና ጥራትን የጠበቀ የጉምሩክ ትራንዚት አገልግሎት እንሰጣለን፡፡

Show more
Ethiopia22 328The category is not specified
463
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ውድ የዚህ ቻናል ተከታታዮች ልምድ እና ዕውቀት ባላቸው ባለሙያዎች የተቋቋመው ሞና ትራንዚት አገልግሎት ጥራትን እና ቅልጥፍናን መሠረት ያደረገ የጉምሩክ ትራንዚት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን እናበስራለን፡፡ ይደውሉ ያግኙን፡፡

በክልሎች ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪዎች የንግድ አገልግሎት ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ፌዴራል ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መዞሩ ተገለጸ:: ==================================== አዲስ አበባ 03/11/ ከ2015 ዓ.ም (ንቀትሚ) በክልሎች ይሰጥ የነበረው የአስመጪዎችና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል አገልግሎቱ እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፈቃድ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት በክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በኩል ይሰጥ የነበረው የአስመጪና ላኪ የንግድ አገልግሎት አስተዳዳራዊ ክፍተቶች የታዩበት፣ የኮንትሮባንድ ንግድ የተበራከተበት በመሆኑና በወቅቱ አገልግሎቱ ያልወረደላቸው ክልሎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በማንሳታቸው ሚኒስትር መስራ ቤቱ ይህን ችግር ለመፍታት የአስመጪና ላኪዎች ንግድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በፌዴራል ተግባራዊ እንዲሆን መወሰኑን ሚኒስትር መስራ ቤቱ አስታውቋል፡፡ የኦንላይን ንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎት ከሃምሌ 1/2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ማንኛውም አስመጪና ላኪ ነጋዴ የትም ማሄድ ሳይጠበቅበት ሲስተሙን በመጠቀም ባለበት ቦታ ሆኖ አገልግሎት ማግኘት የሚችል ሲሆን በአገልግሎቱ ላይ ግልጽ ያልሆኑ ጥያቄዎች ካሉ በ 965 የጥሪ መዕከል ደውሎ መረጃ ማግኘት የሚችል መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

Ethio_South_Sudan_Border_Trade_implementation_Draft_Directive_2.docx0.46 KB

Ethio_Djibouti_Border_Trade_implementation_Draft_Directive_2_Amharic.docx0.50 KB

ማስታወቂያ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ እና ከደቡብ ሱዳን ጋር ቀደም ሲል በተፈራረመችው የጠረፍ ንግድ ስምምነቶች( border trade protocols) መሰረት የድንበር አካባቢ ማህበረሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጠረፍ ንግድ ማስፈጸሚያ ረቂቅ መመሪያዎች በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እየተዘጋጁ ይገኛል፡፡ እነዚህን የጠረፍ ንግድ ማስፈጸምያ ረቂቅ መመሪዎች አስመልክቶ ማንኛውም በዘርፉ ላይ ፍላጎት ያለው ግለሰብም ሆነ ተቋም፣ በተለይም በጠረፍ አካባቢ በሚገኙ በጋምቤላ፣ በሱማሌ  እና በአፋር ክልሎች የምትገኙ የአስተዳደር ዘርፍ ሀላፊዎችን ጨምሮ ማንኛውም በረቂቅ የጠረፍ ንግድ ማስፈጸሚ መመሪዎች ላይ  አስተያየት ያላችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 የስራ ቀናት ውስጥ አስተያየታችሁን ከታች በተቀመጡት አማራጮች እድትልኩልን እየጠየቅን የጠረፍ ንግድ ማስፈጸምያ ረቂቅ መመሪውን ሙሉውን ሰነድ በቴሌግራም ገጻችን  :https://t.me/motri_gov_et ላይ ማግኝት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ፡፡ አስተያየቶቻችሁን፡- • በኢሜል ፡-  sisaykebede47@gmail.com •  በፖስታ ሳጥን ቁጥር፡  704

እቃ ወደ አገር ውስጥ ሲገባ ስለሚከፈል ቀረጥ አጭር መረጃ

updated_የባህር_ትራንስፖርት_ማጓጓዣ_ዋጋ_መረጃ.pdf4.83 MB

935_የንግድ_ምዝገባ፣_ፈቃድ_እና_ድኅረ_ፈቃድ_ኢንስፔክሽን_መመሪያ_ቁጥር_935_2015_1.pdf9.72 KB

የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ላይ ማሻሻያ ተደረገ የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 ከየካቲት 5/2012 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለ ሲሆን ይህ አዋጅ የታክሱን መሰረት በማስፋት እና የታክሱን አስተዳደር ስርዓት በመቀየር ከፍተኛ ጠቀሜታን አስገኝቷል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባኤው በአዋጁ ላይ የቀረቡ ማሻሻያዎችን ታሳቢ በማድረግ የአዋጁ ማሻሻያ ተደርጓል፡፡ የአዋጁ ማሻሻያ ታሰቢ ያደረገው ተደራራቢ የኤክሳይዝ ታክስ የተጣለባቸው ምርቶች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ፣ በቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ላይ የኤክሳይዝ ታክስ እንዲከፈል ለማድረግ፣ የኤክሳይዝ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩት አንዳንድ ምርቶች ላይ ታክሱን ለማንሳት፣ እንዲሁም በአስተዳር ምክንያት የተደረጉ ማስተካከያዎችን እና የማሻሻያውን ዋና ዋና ምክንያቶችን ከመረመረ በኋላ የኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1287/2015 እንዲጸድቅ አድርጓል፡፡ አዋጁ ከጸደቀበት ከሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ ውሏል፡፡

Dear all, esw team trying to fix the problem. just for temporary solution, try to fill all information fastly and save it repeatedly.

+1
Dec_2022_የታሪፍ ማሻሻያ ሠርኩላር.pdf2.95 MB