en
Feedback
Wcu main campus

Wcu main campus

Open in Telegram

Show more
Ethiopia7 023The category is not specified
3 383
Subscribers
-124 hours
+147 days
+830 days
Posts Archive
photo content

መልካም ዜና የመዉጫ ፈተና ያለፉም ያላላፉም ተመራቂ ተማሪዎች ሐሙስ 13/11/2015 ዓ.ም በሚደረገው የምርቃ መርሃ ግብር ለይ እንድሳተፉ የተወሰነ በመሆኑ ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ። Congratulations! የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

የመውጫ ፈተና ውጤት መታየት ጀመረ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን በ " ኦላን ላይን " ማየት መጀመራቸውን ማረጋገጥ ችሏል። ምንም እንኳን ትምህርት ሚኒስቴር ውጤት መታየት የሚጀምረው ከማታ ጀምሮ መሆኑን ቢገልጽም ከዚህ ሰዓት አንስቶ ተማሪዎችን የፈተናውን ውጤት እያዩ መሆኑን አረጋግጠናል። የመውጫ ፈተና ውጤት የሚታየው በ result.ethernet.edu.et ላይ Username እና Password በማስገባት ነው። ድረገፁ ተመራቂዎች ፈተናውን ማለፍ አለማለፋቸውን ካገኙት ውጤት ጋር Pass / fail እያለ ያሳውቃቸዋል።

ተማሪዎችየመዉጫ ፈተና ውጤታችሁን ከእሑድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣችሁን Username በመጠቀም በዚህ ሊንክ በ https://result.ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ።

photo content

Exam rule for Remedial Students
Exam rule for Remedial Students

Final Room Schedule for Model Exit Exam by MoE.pdf0.91 KB

Good Luck!
Good Luck!

#MoE 161 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጀመሪያ ዲግሪ ዕጩ ተመራቂዎቻቸው የመውጫ ፈተና ይሰጣሉ። በተጨማሪም 44 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ በትምህርት ሚኒስቴር
#MoE 161 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጀመሪያ ዲግሪ ዕጩ ተመራቂዎቻቸው የመውጫ ፈተና ይሰጣሉ። በተጨማሪም 44 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንደሚያስፈትኑ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ ኢዮብ አየነው (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል። በዚህም 95,755 ተማሪዎች ከግል እና 74,706 ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በድምሩ 170,461 ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ ብለዋል። ተማሪዎች ከተማሯቸው የትምህርት ዓይነቶች መካከል መሰረታዊ በሚባሉት ከ12 እስከ 17 የትምህርት ዓይነቶች ፈተናው መዘጋጀቱን ኃላፊው ጠቁመዋል። በመውጫ ፈተና አዘገጃጀት መመሪያ መሰረት ለ211 የትምህርት ፕሮግራሞች የፈተና ጥያቄዎች ዝግጁ መሆናቸውንም አመልክተዋል። ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቸ ዲግሪ እንደማይሰጣቸው እና በቀጣይ በድጋሜ እንደሚፈተኑ ገልጸዋል። #ኢዜአ

ለመላም የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 1444ው የዒድ አል-አድሀ(አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! መልካም የዒድ አል- አድሃ (አረፋ) በዓል ዒድ ሙባረክ
ለመላም የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 1444ው የዒድ አል-አድሀ(አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! መልካም የዒድ አል- አድሃ (አረፋ) በዓል ዒድ ሙባረክ

4_5787204578634108844.xls

የ2015 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ለመስጠት ማቀዱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። *********************************** በ
የ2015 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ለመስጠት ማቀዱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። *********************************** በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን እና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡ ተማሪዎች በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ብቻ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ሰጥቶ ለማጠናቀቅ መወሰኑን መስሪያ ቤቱ ያሳወቀ ሲሆን፤ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ስራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ እንዲሁም፤ በ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍልን አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ ብሎም ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም የትምህርት ተቋማት የትምህርት የጊዜ ሰሌዳቸውን (Academic Calendar) በዚህ ማዕቀፍ ያስተካክሉ ዘንድ ትምህርት ሚኔስቴር ትዕዛዝ አስተላልፏል። በመሆኑም ተማሪዎች በዚህ ፕሮግራም መሰረት ከወዲሁ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ እየጠየቅን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ መሆኑን እንገልፃለን። @EHEISUOfficialChannell

የ1 ሺህ 4 መቶ 44ኛው የኢድ-አል ፈጥር በዓል በማስመልከት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የእንኳን  አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ!! ለ1 ሺህ 4 መቶ 44ኛው የኢድ-አል ፈጥር በዓል በማስመልከት  የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ የእንኳን  አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንኳን በ2015 ዓ/ም የሚከበረውን  ለ1 ሺህ አራት መቶ 44ኛው ኢድ-አል ፈጥር በዓል አደረሳችሁ እያልኩ  በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ እንዲሆን እመኛለሁ። የሙስሊሙ ማህበረሰብ በፆም ወቅት  የአላህ ትዕዛዝ በማክበር ያሳየውን መልካም ተግባር በሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እንደሚያሳይ ይጠበቃል። በሀይማኖቱ አስተምሮ መሠረት ጾም የተራቡና የተቸገሩ ሰዎችን ሕይወት የሚካፈሉበትና ዓመቱን ሙሉ በችግርና በሰቆቃ የሚያሳልፉትን ድሆች ሁኔታ የሚያስታውሱበት የአምልኮ ዘርፍ   መሆኑን ታላቁ ቁርአን ይናገራል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ በፆም ወቅት በጋራ የአፍጥር ስነስርዓት ማካሄድ እና በአላህ ትዕዛዝ  መጓዝ የሚያስተምረው ትልቁ ምስክር ከአላህ በርከት መቀበልን፣ በጋራ መቆም እንዲሁም ለድሆች ማሰብን ያስተምራል ብዬ አስባለሁ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ አይነት ግጭቶችና አለመግባባትን በማስተናገድ ዜጎችን እጅግ አዋራጅ ከሆነው ድህነት ጋር እንድንኖር  እና አልፎ አልፎ የኃያላን ስውር እጆች እንድናይ እያደረገ ይገኛል። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ሁላችንም በጋራ በመቆም የእምነቱ  ተከታዮች በፆም ያገኛችሁትን ፅናት እና ለአላማ የመኖር ትርጉም ይዘን ለሀገራችን ብልፅግና እና ሰላም ዘብ  መቆም ይጠበቅብናል። በእስልምና ሃይማኖት መሠረት ፆሙ ከሚያስገኛቸው ትሩፋቶች መከከል በአላህ አምኖ፣ ትዕዛዙንም አክብሮ፣ በረመዳን ትሩፋት ዙሪያ የተላለፉ ጉዳዮችን እውነት ብሎ ተቀብሎ እንዲሁም አላህ ዘንድ የሚያገኘውን ምንዳ በመከጀል ረመዳንን የጾመ፣ ቀደም ሲል የሰራው ወንጀሉ ይማርለታል፡፡ ምስጥሩ ይቅር በመባባልና በይቅርታ ማመን ሲሆን ሀገራችንን በይቅርታ  መሻገር እና በዓሉን ለመክበር ያልቻሉ ወገኖቻችንን በማሰብ ልሆን ይገባል እያልኩ  ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያን፣የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብና ተማሪዎች እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ። መልካም የኢድ-አል ፈጥር ኢድ ሙባረክ! ዶ/ር ሀብታሙ አበበ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሚያዝያ 2015 ዓ.ም @wachemoo

photo content
+8

የትንሣኤ በዓል በማስመልከት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዓሉን በድምቀት አከበሩ ** የትንሣኤ በዓል በማስመልከት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ ተማሪዎች ጋር ፋሲካን በድምቀት አክብረዋል። ፕሬዝዳንቱ ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ በማለት ትንሳኤ የሚያስተምረው ይቅር መባባልን እና የአንድነት መንገድ ነው ብለዋል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለምንም ጥፋት ከቆሰለ በኃላ ያሰቃዩትን በሙሉ የሚያደርጉትን አያውቀውምና ይቅር በላቸው በማለት ያለውን የይቅርታ ጥግ በማሳየቱ ዛሬም እኛ በይቅርታ ትውልድን ማሸጋገር ያስፈልጋል ሲሉ ዶ/ር ሀብታሙ አበበ ተናግረዋል። በዓሉ ሲከበር ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረን ፍቅር፣ ትህትና እና መረዳዳት በመሆኑ ሁላችንም ይህንኑ ተግባራዊ በማድረግ ለሀገራችን ትንሳኤ በጋራ መስራት ይጠበቃል ብለዋል። የተማሪዎች መሠረታዊ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሳሙኤል ግርማ በበኩላቸው ተማሪዎች በዓሉን በጋራ እንዲያከብሩ በቂ ዝግጅት መደረጉን አንስተው ይህ እንዲሳካ የበኩላቸውን ድርሻ ለተወጡት አካላት ምስጋና አቅርበዋል። እንኳን ለበዓሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሳኤ ስናስብ እና ስናከብር የሁሉ ፈጣሪ የሆነ አምላክ ሰው ሆኖ በምድር ተገልጦ ቅንነትን፣አገልጋይነትን፣ ዝቅ ማለትን፣ ትህትናን፣ መሃሪነትን እና ይቅርታውን አስተምሮ ለእኛ የከፈለልንን መስዋዕትነት እና ለኛ ያለውን ጥልቅ ፍቅር በመረዳት የትንሳኤው ብርሃን በህይወታችን እንዲበራ በማድረግ መሆን ይገባል ሲል የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት እና የሰላም ፎረም መልዕክት አስተላልፏል። ሚያዝያ ቀን 8/2015 ዓ.ም ዘገባው የህዝብ ግንኙነት እና ዓለም ዓቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው። Let Your Light Shine in the Society! @wachemoo

photo content

photo content

photo content