en
Feedback
ምርጥ ምሳሌያዊ ንግግሮች

ምርጥ ምሳሌያዊ ንግግሮች

Open in Telegram

በቻናሉ አዝናኝ እና አስተማሪ ምሳሌያዊ ንግግሮች ከሁሉም የአለም ክፍል ተተርጉሞ ይቀርባል ለማንኛውም አስተያየት ሆነ ጥያቄ @mirtababaloch1bot ላይ ያገኙናል

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
3 283
Subscribers
+724 hours
+247 days
+10730 days
Posts Archive
ጨለማ ውስጥ ብርሀን፤ ውጥንቅጥ ውስጥ ውበት፤ ሞት ውስጥ ህይወት አለ #thefairytail @mirtababaloch

ህይወቴን ሙሉ ሁሌም ከለመድኩት ውጭ ተጨማሪ ነገር እንዳለ እገምት ነበር፤ ከዛ አንቺን አገኘሁ ያኔ ልክ እንደነበርኩ አረጋገጥኩ... ልክ ነበርኩ!! #Free_Guy(movie) @mirtababaloch

ሰላም ከፈለክ ለጦርነት ተዘጋጅ #ጣልያን @mirtababaloch

ሲለምኗት እንቢ ብላ ሲጎትቷት #ኢትዮጵያ @mirtababaloch

የረመዳን ወር በመጣ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮች ይዘጋሉ፤ ሸይጣኖችም ይታሰራሉ። #ነብዩ_መሀመድ(ሰዐወ) #mirtababaloch
የረመዳን ወር በመጣ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮች ይዘጋሉ፤ ሸይጣኖችም ይታሰራሉ። #ነብዩ_መሀመድ(ሰዐወ) #mirtababaloch

ወቅታዊ ምርቃት... አሜን በል ! —---------------------------- ግንባርህን ከቄሮ ዱላ የኪራይ ቤትህን ከደላላ ጆሮህን ከመግለጫ አውቶብስህን ካዲሳባ መውጫ ያትርፍልህ ! አንገትህን ከገጀራ አገርህን ከመከራ ነፍስህን ከባለጊዜ መንግስትህን ከድንዛዜ ንብረትህን ከመንጋ አጥፊ ‹ኢሜልህን› ከጠላፊ ያድንልህ! እንደተኛህ ‹ሳትከበብ› ቀን በቁምህ ‹ ሳትመረዝ› እድሜህ ይርዘም እንዳባይ ወንዝ ! አገርህን ከግብፅ ዛቻ ወጣትህን ከዘመቻ ሰላምህን ከዓይን አውጣ አዝመራህን ከአንበጣ ያትርፍልህ! ከመቅደስህ ቅዳሴ እንጅ የዋይታ እንባ ከቶ አይፍሰስ በሱብሂ አዛን እንጅ ጧት ለመርዶ አትቀስቀስ ዱኒያ ተትረፍርፎልህ ርዚቅ ቤትህ ይከመር በከሰረ የደም ምድር አንደብር ሬሳ አትቁጠር ከነጋልህ ቀንህ ይመር ከመሸብህ ሰላም እደር !! #አሌክስ_አብረሃም @mirtababaloch

አሁን አሁን እየገባኝ የመጣው ነገር ዘረኝነትን ሲያወግዝ ከሚውለው ሰው በላይ ዘረኛ የለም #ዘውድአለም @mirtababaloch

ታካሚ ከሞተ ዶክተሩ ገደለው ከዳነ ፀሎታችን ሰመረ #ጣልያን #mirtababaloch

እርሟን ብታፈላ ጀበና ሙሉ አተላ #ኢትዮጵያ @mirtababaloch

ፀሎት ካበዛ የሆነ ነገር ፈርቶዋል ማለት ነው #አርጀንቲና @mirtababaloch

እኔ እወድሻለው ብዙ ሺህ ዘመናት እልፍ አእላፍ ሌሊት ሚልዮን መሰለኝ ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ፡፡ እኔ እወድሻለው የሠማይ መሬቱን የባህር ስፋቱን የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል እንደ ጽጌረዳ እንደ አደይ አበባ እንደሎሚ ሽታ፡፡ እንደ ከርቤ ብርጉድ እንደ እጣን ጢስ እንጨት ውዴ እወድሻለው አበባ እንዳየ ንብ፡፡ እንደቢራቢሮ ጫካ እንደሚያስሰው ፍቅርሽን በፍቅሬ በፍቅርሽ ልቅመሰው፡፡ ማር ወለላዬ ነሽ ከረሜላ ስኳር አማርኛ አይበቃ ወይ ጉድ ባለም ቋንቋ ሁሉ ቢወራ ቢነገር እኔ እወድሻለው እንደማታ ጀንበር እንደጨረቃ ጌጥ እንደ ተወራርዋሪ ኮከብ እኔ እማልጠግብሽ ስወድሽ ፤ስወድሽ፤ ስወድሽ ፤ስወድሽ ፡፡ ጡት እንዳየ ህጻን ወተት እንዳማረው ጠጋ በይ ዘመዴ አፍሽ ህይወቴ ነው፡፡ ጣይ ላይ እንዳለ ቅቤ ገላዬ ገላሽን ሲነካ የሚያልቀው አፈር መሬት ትቢያ ውሃ እንደሚበላው ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ ብዙ ሺህ ዘመናት እልፍ አእላፍ ሌሊት እኔ እወድሻለው አይኖችሽን ባይኔ ደጋግሜ እያየው ስወድሽ ሰወድሽ ውዴ እወድሻለው፡፡ #ገብረክርስቶስ_ደስታ @mirtababaloch

ሲሮጥ ካላየኸው እንደሚበር ጠርጥር #ቺሊ @mirtababaloch

የተናቀ አስረገዘ #ኢትዮጵያ @mirtababaloch

እንኳን አደረሳቹ
እንኳን አደረሳቹ

​​➢➢ላ’ንዲት የገጠር ሴት➢➢ ስትፈጭ የኖረች ሴት፣ መጁ በመጠኗ፣ ወፍጮውም በልኳ፣ ጓያ ትፈጫለች ጓያ ሽሮ ሲሆን ያበቃል ታሪኳ !! አስባው አታውቅም… ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደመጣች፣ ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ከና’ቷ ሆድ ወጣች፣ ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች፣ ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ለባሏ ተሰጠች…… ተዚያን ቀን ጀምራ፣ ተዚያን ቀን ጀምሮ፣ ድንግል ድንጋይ ወቅራ፣ ትፈጫለች ሽሮ…… አታውቅም፣ ማን እንደሚባሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አታውቅም፣ ሹማምንት በ’ሷ ስም፣ ምን እንደሚሠሩ፣ አነሳኹት ‘ንጂ፣ እኔም ለነገሩ፣ ፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ፣ ምን ይጠቅማትና ጓያዋን ለማድቀቅ ከቶ ማንም የለ, አበባ ‘ሚሰጣት፣ ከቶ ማንም የለ፣ ከተማ ‘ሚያወጣት፣ ከቶ ማንም የለ ፣ በዳንኪራ መላ፣ ወገቧን የሚያቅፋት፣ ልፋቷም፣ ዕረፍቷም፣ ወደዚህ መጅ መሳብ ወደዚያ መጅ መግፋት…… እንደ ዓባይ ፏፏቴ፣ ሽህ ዓመት ቢንጣለል፣ ቢጎርፍም ዱቄቱ፣ እንደ ሲኦል ወለል፣ ጫፍ የለውም ቋቱ! ከዘመናት ባንዱ መስተዋት ፊት ቆማ፣ በተወለወለው፣ ራሷን ለማየት፣ ከጸጉራ ላይ ያለው ዱቄት ይኹን ሽበት ሲያቅታት መለየት፣ ያኔ ይገባታል የተሰጣት ዕጣ፣ ከማድቀቅ ቀጥሎ፣ መድቀቅ እንዲመጣ… የመጅ አጋፋፏ - አምሳለ ሲሲፈስ፣ ከቋት ሥስት እንጅ፣ ሢሳይ አይታፈስ፣ ትቢያ ‘ሚተነብይ ዱቄት በዙሪያዋ፣ ከባርኔጣ አይሰፋም፣ የኑሮ ጣሪያዋ፣ "ስትፈጭ የኖረች ሴት" ይህ ነው መጠሪያዋ! #በእውቀቱ_ስዩም @mirtababaloch

ምርጥ ሰው ብሎ ማለት የራሱን ጥፋቶች በመፈለግ ተወጥሮ የሌላውን ጥፋት የሚያይበት ጊዜ ያጣ ሰው ነው #ነቢዩ_ሙሃመድ(ሰዐወ) @mirtababaloch

ብቸኛ ነኝ ብሎ፣ ይሄ ምስኪን ልብህ ሳግ ሲተናነቀው ፀሀይን ተመልከት፣ ብቻውን ሆኖ ነው ሚያንፀባርቀው! #እዮብ @mirtababaloch

አዲስ አመት አዲስ ተስፋ 🌻🌻🌻 2012 🌻🌻🌻
አዲስ አመት አዲስ ተስፋ 🌻🌻🌻 2012 🌻🌻🌻

አዝለኸው የለመደ ውረድ እና ልረፍ ብትለው ምቀኛ የሆንክበት ይመስለዋል #እኔ @mirtababaloch

የኢትዮጽያን ችግር ጠጋ ብሎ ላስተዋለው በሁለት ስንኞች የተገለፀ ነው፤ አንዱ: እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ሌላው: እኔ ካልጋገርኩት እርር ይበል #ቴውድሮስ_ዳኜ @mirtababaloch