ምርጥ ምሳሌያዊ ንግግሮች
Open in Telegram
በቻናሉ አዝናኝ እና አስተማሪ ምሳሌያዊ ንግግሮች ከሁሉም የአለም ክፍል ተተርጉሞ ይቀርባል ለማንኛውም አስተያየት ሆነ ጥያቄ @mirtababaloch1bot ላይ ያገኙናል
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
3 283
Subscribers
+724 hours
+247 days
+10730 days
Posts Archive
3 283
ህይወቴን ሙሉ ሁሌም ከለመድኩት ውጭ ተጨማሪ ነገር እንዳለ እገምት ነበር፤
ከዛ አንቺን አገኘሁ ያኔ ልክ እንደነበርኩ አረጋገጥኩ... ልክ ነበርኩ!!
#Free_Guy(movie) @mirtababaloch
3 283
የረመዳን ወር በመጣ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮች ይዘጋሉ፤ ሸይጣኖችም ይታሰራሉ።
#ነብዩ_መሀመድ(ሰዐወ) #mirtababaloch
3 283
ወቅታዊ ምርቃት... አሜን በል !
—----------------------------
ግንባርህን ከቄሮ ዱላ
የኪራይ ቤትህን ከደላላ
ጆሮህን ከመግለጫ
አውቶብስህን ካዲሳባ መውጫ
ያትርፍልህ !
አንገትህን ከገጀራ
አገርህን ከመከራ
ነፍስህን ከባለጊዜ
መንግስትህን ከድንዛዜ
ንብረትህን ከመንጋ አጥፊ
‹ኢሜልህን› ከጠላፊ
ያድንልህ!
እንደተኛህ ‹ሳትከበብ›
ቀን በቁምህ ‹ ሳትመረዝ›
እድሜህ ይርዘም እንዳባይ ወንዝ !
አገርህን ከግብፅ ዛቻ
ወጣትህን ከዘመቻ
ሰላምህን ከዓይን አውጣ
አዝመራህን ከአንበጣ
ያትርፍልህ!
ከመቅደስህ ቅዳሴ እንጅ
የዋይታ እንባ ከቶ አይፍሰስ
በሱብሂ አዛን እንጅ
ጧት ለመርዶ አትቀስቀስ
ዱኒያ ተትረፍርፎልህ
ርዚቅ ቤትህ ይከመር
በከሰረ የደም ምድር
አንደብር ሬሳ አትቁጠር
ከነጋልህ ቀንህ ይመር
ከመሸብህ ሰላም እደር !!
#አሌክስ_አብረሃም @mirtababaloch
3 283
እኔ እወድሻለው
ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
ሚልዮን መሰለኝ
ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ ቀኑ ረዘመብኝ፡፡
እኔ እወድሻለው
የሠማይ መሬቱን
የባህር ስፋቱን
የዓለም ዳርቻ የርቀቱን ያህል
እንደ ጽጌረዳ
እንደ አደይ አበባ
እንደሎሚ ሽታ፡፡
እንደ ከርቤ ብርጉድ
እንደ እጣን ጢስ እንጨት
ውዴ እወድሻለው አበባ እንዳየ ንብ፡፡
እንደቢራቢሮ ጫካ እንደሚያስሰው
ፍቅርሽን በፍቅሬ
በፍቅርሽ ልቅመሰው፡፡
ማር ወለላዬ ነሽ ከረሜላ ስኳር
አማርኛ አይበቃ
ወይ ጉድ
ባለም ቋንቋ ሁሉ ቢወራ ቢነገር
እኔ እወድሻለው
እንደማታ ጀንበር
እንደጨረቃ ጌጥ
እንደ ተወራርዋሪ ኮከብ
እኔ እማልጠግብሽ
ስወድሽ ፤ስወድሽ፤ ስወድሽ ፤ስወድሽ ፡፡
ጡት እንዳየ ህጻን ወተት እንዳማረው
ጠጋ በይ ዘመዴ አፍሽ ህይወቴ ነው፡፡
ጣይ ላይ እንዳለ ቅቤ
ገላዬ ገላሽን ሲነካ የሚያልቀው
አፈር መሬት ትቢያ ውሃ እንደሚበላው
ፍቅሬ አንቺን ስወድሽ
ብዙ ሺህ ዘመናት
እልፍ አእላፍ ሌሊት
እኔ እወድሻለው
አይኖችሽን ባይኔ ደጋግሜ እያየው
ስወድሽ ሰወድሽ
ውዴ እወድሻለው፡፡
#ገብረክርስቶስ_ደስታ @mirtababaloch
3 283
➢➢ላ’ንዲት የገጠር ሴት➢➢
ስትፈጭ የኖረች ሴት፣
መጁ በመጠኗ፣ ወፍጮውም በልኳ፣
ጓያ ትፈጫለች
ጓያ ሽሮ ሲሆን ያበቃል ታሪኳ !!
አስባው አታውቅም…
ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደመጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ከና’ቷ ሆድ ወጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ለባሏ ተሰጠች……
ተዚያን ቀን ጀምራ፣
ተዚያን ቀን ጀምሮ፣
ድንግል ድንጋይ ወቅራ፣
ትፈጫለች ሽሮ……
አታውቅም፣
ማን እንደሚባሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣
አታውቅም፣
ሹማምንት በ’ሷ ስም፣ ምን እንደሚሠሩ፣
አነሳኹት ‘ንጂ፣ እኔም ለነገሩ፣
ፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ፣
ምን ይጠቅማትና ጓያዋን ለማድቀቅ
ከቶ ማንም የለ, አበባ ‘ሚሰጣት፣
ከቶ ማንም የለ፣ ከተማ ‘ሚያወጣት፣
ከቶ ማንም የለ ፣ በዳንኪራ መላ፣ ወገቧን የሚያቅፋት፣
ልፋቷም፣ ዕረፍቷም፣
ወደዚህ መጅ መሳብ
ወደዚያ መጅ መግፋት……
እንደ ዓባይ ፏፏቴ፣
ሽህ ዓመት ቢንጣለል፣
ቢጎርፍም ዱቄቱ፣
እንደ ሲኦል ወለል፣ ጫፍ የለውም ቋቱ!
ከዘመናት ባንዱ
መስተዋት ፊት ቆማ፣ በተወለወለው፣
ራሷን ለማየት፣
ከጸጉራ ላይ ያለው
ዱቄት ይኹን ሽበት ሲያቅታት መለየት፣
ያኔ ይገባታል
የተሰጣት ዕጣ፣
ከማድቀቅ ቀጥሎ፣ መድቀቅ እንዲመጣ…
የመጅ አጋፋፏ - አምሳለ ሲሲፈስ፣
ከቋት ሥስት እንጅ፣ ሢሳይ አይታፈስ፣
ትቢያ ‘ሚተነብይ ዱቄት በዙሪያዋ፣
ከባርኔጣ አይሰፋም፣ የኑሮ ጣሪያዋ፣
"ስትፈጭ የኖረች ሴት"
ይህ ነው መጠሪያዋ!
#በእውቀቱ_ስዩም @mirtababaloch
3 283
የኢትዮጽያን ችግር ጠጋ ብሎ ላስተዋለው
በሁለት ስንኞች የተገለፀ ነው፤
አንዱ: እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል
ሌላው: እኔ ካልጋገርኩት እርር ይበል
#ቴውድሮስ_ዳኜ @mirtababaloch
