609
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1030 days
Posts Archive
ማስታወቂያ
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
መስከረም 2017
#AASTU #ASTU
በ2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ ጥሪ ቀርቧል።
ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በቀጥታ (online) በመስጠት ነው የሚቀበሉት።
የትምህርት መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?
/ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /
#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሮ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፣ ማይኒንግ ኢንጂነሪንግ ፣ ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ
#አፕላይድሳይንስ ፦ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፉድ ሳይንስ፣ አፕላይድ ኒውትሪሽን ፣ ጂኦሎጂ፣ ባዮቴክኖሎጂ
/ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /
#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ኢንጂነሪንግ፣ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ
#አፕላይድሳይንስ ፦ አፕላይድ ቦዮሎጂ፣ አፕላይድ ኬሚስትሪ፣ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፋርማሲ፣ አፕላይድ ፊዚክስ ፣ አፕላይስ ጂኦሎጂ፣ አፕላይድ ማቲማቲክስ
የምዝገባ ጊዜ፡- ከመስከረም 06 እስከ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሆነ ተገልጿል።
ምዝገባው የሚጠናቀቀው መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ ነው።
የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et ድረገጽን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በድህረ ገጽ የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ ይደረጋል።
ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ፤ በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡
NB. ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቅ ሲሆን የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ፍላጎቱ ያላቸው አመልካቾች ይህን አውቀው ቅድሚያ እንዲመዘገቡ ተብሏል።
@tikvahethiopia
Repost from Harari Broadcasting Network
ለትምህርታቸው ሙሉ ትኩረት በመስጠት አመቱን ሙሉ ማጥናታቸው እና የመመህራን ዕገዛ በ12ኛ ክፍል ፈተና ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የረዳቸው መሆኑን ከሀረሪ ክልል በፈተናው ጥሩ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ገለጹ።
***
የ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
እንደ ሀገር በተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የሐረሪ ክልል ከአዲስ አበባ መስተዳድር በመቀጠል ለፈተናው ከተቀመጡ ተማሪዎች ውጤት አንፃር በማሳለፍ ምጣኔ እንደ ሀገር ሁለተኛ ደረጃ ላይ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ በሐረሪ ክልል ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል የሀረር ኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር ተማሪ ሱራፌል በትረ ፣ መርቱ ዮሀንስ እና ቤትሔል ማስረሻ ከሀረሪ ብዙሐን መገናኛ ኤጀንሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ተማሪዎቹ በውጤቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ለጥሩ ውጤት የበቁበትም ምክንያት ትምህርት ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ አመቱን ሙሉ ማጥናት፣ ሙሉ ትኩረት መስጠት፣ ለፈተና በቂ ዝግጅት ማድረግና የመምህራኖች ዕገዛ ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ ገልፀዋል።
ተማሪዎቹ አክለውም በጋራ ማጥናትና መመካከር እንዲሁም መምህራኖቻቸው የሚሰጧቸውን የክፍልና ከክፍል ውጪ የትምህርት ተግባራት በአግባቡ መከታተልም የተሻለ ውጤት ለማምጣት ያግዛል ያሉት ተማሪዎቹ በቀጣይም በዩኒቨርሲቲ ህይወታቸው የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ራሳቸውንና ክልሉን ለማስጠራት መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።
የተማሪዎቹ ወላጆች በበኩላቸው ልጆቻቸው ባስመዘገቡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ለዚህ ሁሉ ውጤት መምህራኖቻቸውን ጨምሮ የትምህርት ቤቱን ማህበረሰብ አመስግነዋል።
አክለውም እንደ ሀገር የተማሪ ውጤት በቀነሰበት በዚህ ወቅት የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ እንደ ክልል የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ እያደረገ ላለው ስራ አመስግነው በዚሁ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የሀረር ኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዘንድሮው የ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች ከ97% በመቶ በላይ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸውን የትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር አቶ ተሾመ ደምለው ገልጸዋል።
በትምህርት ዘርፉ በቅንጅትና በትኩረት ከተሰራ ከዚህ የበለጠ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻልም ጠቁመዋል።
የተመዘገበው ውጤት በአንድ ጀምበር የተሰራ ሳይሆን የረዥም አመታት ልፋት ነው ያሉት ዳይሬክተሩ የክልሉን ትምህርት ቢሮ ጨምሮ ለዚህ ውጤት መሳካት አስተዋፅኦ ላደረጉ መምህራን እና የትምህርቱ ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
እንደ ሀገር 674ሺ823 ተማሪዎች መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ሲሆን 36ሺ409ኙ አልያም 5.4% በመቶ ተማሪ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሐረሪ ክልልም በ2015 የትምህርት ዘመን 7.1 በመቶ ተማሪዎች ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን በ2016 የትምህርት ዘመን ደግሞ 13.3 በመቶ ተማሪዎችን ማሳለፍ መቻሉን ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ይህም ውጤት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ 6.2 በመቶ መሻሻል ያሳያል።
ዘጋቢ ሲሳይ ዘርይሁን ።
03 / 01 / 2017
ለሁሉም የሐረር ኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር ት/ቤት ተማሪዎች፣ ወላጆች እንዲሁም ሰራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን ሁሉንም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በከፍተኛ ውጤት ማሳለፍ መቻላችንን እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ከዚህ በፊት ያልተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን በኩራት እንገልፃለን ።
ኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር ት/ቤት
እጅግ በርካታ ድንቅ ተማሪዎችን ያወጣ ወደፊትም በከፍታ የሚቀጥል ድንቅ ት/ቤት
🎉🎉🎉Congratulations !!! 🎆🎆🎆 .
🎆🎆🎆Congratulations 🎉🎉🎉
To all the school community on the remarkable result scored in the entrance examinations!
All natural science students scored above 50%.
95% of social science students scored above 50%.
Our extraordinary student, Surafel Betre scored 536/ 600.
This accomplishment is a true testament to the hard work, dedication, and support provided by all parties involved.
Your hard work and dedication have truly paid off.
Well done! 🎉👏📚
