en
Feedback
Ethiopian Customs Clearing Agents

Ethiopian Customs Clearing Agents

Open in Telegram

Great Interesting Stuff Here!!

Show more
Buy Ad
6 613
Subscribers
+424 hours
+427 days
+23430 days
Posts Archive
የመነሻ ዋጋ /Minimum Price/ በተመለከተ ጥር 23 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 4/0506/15 የተላለፈ ሠርኩላር ⚜Customs Valuation on Minimum Value ECVS-IP Circular Issued on January 31, 2023 ⚠N.B፡- 1. ከጉምሩክ ኮሚሽን ከዚህ በፊት የመነሻ ዋጋ /Minimum Price/ በተመለከተ የካቲት 11 ቀን 2014 በደብዳቤ ቁጥር 4/1167/14 የተላለፈ ሠርኩላር ለማግኘት 👉  (Customs Valuation on Minimum Value ECVS-IP Circular Issued on February 18, 2022) 👈 ይጫኑ 2. ከጉምሩክ ኮሚሽን ከዚህ በፊት የመነሻ ዋጋ /Minimum Price/ በተመለከተ ሐምሌ 06 ቀን 2014 በደብዳቤ ቁጥር 4/0005/15 የተላለፈ ሠርኩላር ለማግኘት 👉  (Customs Valuation on Minimum Value ECVS-IP Circular Issued on July 13, 2022) 👈 ይጫኑ

ማስታወቂያ የጉምሩክ ኮሚሽን ባሉት የጀማሪ ባለሙያ ክፍት የስራ መደቦችን በሰው ኃይል ለመሙላት ከየክልሎቹ መልምሎ በሁለት ዙር ፈተና መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ፈተናውን ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ሰልጣኞች በደቡብ ፖሊስ ኮሌጅ ተጨማሪ ስልጠናዎችን የምትወስዱ በመሆኑ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2015 ዓ.ም ይርጋለም ከተማ በሚገኘው የደቡብ ፖሊስ ኮሌጅ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ በተጨማሪም ስድስት ጉርድ ፎቶግራፍ እና ኦርጂናል የትምህርት ማስረጃ እንድትይዙ እየገለጽን ሌሎች ተጨማሪ መረጃዎችን እና ስም ዝርዝራችሁን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ የኢፌዲሪ ጉምሩክ ኮሚሽን #CustomsComission

In case you missed the news: አዲሱ የድሬደዋ ወደብና ተርሚናል በዛሬው ዕለት ይመረቃል፣ 🌼በከፍተኛ ወጪ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ጥራት የተገነባው የድሬዳዋ ወደብና ተርሚናል ከ
+3
In case you missed the news: አዲሱ የድሬደዋ ወደብና ተርሚናል በዛሬው ዕለት ይመረቃል፣  🌼በከፍተኛ ወጪ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ጥራት የተገነባው የድሬዳዋ ወደብና ተርሚናል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ በገቢ ወጪ ንግድ  የተሰማሩ ባለሃብቶች እንዲሁም ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ሀገር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ጥር 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ይመረቃል፡፡ 🌼በተጨማሪም ኢባትሎአድ አዲሱን የድርጅቱን ብራንድ (ስያሜ አርማ) ይፋ ያደርጋል፡፡

⚜የገንዘብ ሚኒስቴር ከዚህ በፊት በቁጥር ማኢ 30/07/9728  በቀን 20/04/2015 በተጻፈ ደብዳቤ የተደረገው የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ በተራ ቁጥር 3 ታሪፍ ቁጥር 2103.2000 ላይ የሚመደበውን እና የታሪፍ ምጣኔው ከ35 በመቶ ወደ 15 በመቶ ዝቅ ተደርጎ የነበረውን  የቲማቲም ድልህ እና ሌሎች የቲማቲም ሶስ (Tomato Ketchup and other Tomato Sauces) ይህንኑ ምርት የሚያመርቱ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ከለላ ለመስጠት ሲባል የታሪፍ ምጣኔ ማሻሻያው ወደ 35  በመቶ ከፍ እንዲደረግ በማለት የገንዘብ ሚኒስቴር በቁጥር ማኢ30/07/9824  በቀን 15/05/2015 በተጻፈ ደብዳቤ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ማሻሻያው ተግባራዊ እንዲደረግ ጥር 19 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 6.3/0100/15 ከጉምሩክ ኮሚሽን የተላለፈ ሠርኩላር 🏵🏵🏵 ⚠N.B፡- የገንዘብ ሚኒስቴር ከዚህ በፊት በቁጥር ማኢ 30/07/9728  በቀን 20/04/2015 በተጻፈ ደብዳቤ ያደረገውን የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማሻሻያ ሠርኩላር ለማግኘት ይህንን 👉  (MoF's Previous Customs Tariff Amendment) 👈 ይጫኑ

In case you missed the news: የኤክሳይስ ታክስ ረቂቅ አዋጅ ፓርላማው ያፀደቀውን አዋጅ የሚጥሱ ድንጋጌዎችን በማካተቱ እንዳይፀድቅ ተጠየቀ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የኤክሳይስ ታክስ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ፣ የማኅብረሰብን ጤና ለመጠበቅ ተብሎ ምክር ቤቱ ያፀደቀውን የምግብና መድኃኒት አስተዳደር አዋጅ የሚጥስ በመሆኑ፣ ማሻሻያ ሳይደረግበት እንዳይፀድቅ ተጠየቀ። ቅሬታ አዘል ጥያቄውን በግልጽ ወጥቶ ያቀረበው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ባለሥልጣን ቢሆንም፣ የጤና ሚኒስቴርን ጨምሮ በማኅበረሰብ ጤና ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትም ረቂቁ የኤክሳይስ ታክስ ማሻሻያ አዋጅ አሁን ያለውን ይዘት እንደያዘ እንዳይፀድቅ እየተንቀሳቀሱ ነው። ለተቋማቱ ቅሬታ ምክንያት የሆነው ከአራት ዓመት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የምግብና መድኃኒት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1112 ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን የሚሽር ሆኖ በመገኘቱ ነው። ይህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ኤሌክትሮኒክስ ሲጋራ፣ ሺሻና የሺሻ መጠቀሚያ ፒፓዎች ላይ የኤክሳይስ ታክስ የሚጣል መሆኑ ተዘርዝሮ መቅረቡን የገለጹት ወ/ሮ ሔራን {የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት አስተዳደርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር} ፣ እነዚህ የትምባሆ ምርት ዓይነቶች ወደ አገር እንዳይገቡ በአዋጅ ቁጥር 1112 ላይ መደንገጉን ገልጸዋል። ‹‹ረቂቅ አዋጁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት በቀረበበት ወቅት የኤክሳይስ ታክስ ክፍያ ምጣኔ ማሻሻያ የተደረገባቸው ምርቶች ዝርዝር ከረቂቅ ሰነዱ ጋር ተያይዞ አለመቅረቡን ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀረበው ሰነድ ላይ የምርቶች ዝርዝር አለመያያዙን ተረድቻለሁ፤›› የሚሉት ዳይሬክተሯ፣ ‹‹ይህ ለምን ሊሆን ቻለ ብሎ ፓርላማው መጠየቅ አለበት፤›› ብለዋል። Source: ኢትዮጵያ ኢንሳይደር Read more 👉 https://www.ethiopianreporter.com/115534/

አዲሱ የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅNew Draft _ Excise Tax Amendment Proclamation ⚠ማሳሰቢያ፡- ይህ ከዚህ በላይ የተያያዘው ረቂቅ ሠነድ ጥር 6 ቀን 2015 የሚኒስትሮች ምክር ቤት 16ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ተወያይቶ ግብዓት በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ከወሰነበት እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ጥር 16 ቀን 2015 የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅን ለማሻሻል የተዘጋጀውን ረቂቅ ሠነድ ተመልክቶ ለዝርዝር ዕይታ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲተላለፍ ከተደረገው የመጨረሻው ሠነድ ጋር ለውጥም ሆነ ማስተካከያ ሊኖር እንደሚችል ግምት ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል፡፡ መልካም ንባብ!

የጉምሩክ አስተላላፊነት የብቃት ማረጋገጫ አመታዊ እድሳት በተመለከተ ጥር 15 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 7.2/0289/15 ከጉምሩክ ኮሚሽን የተላለፈ ሠርኩላር

⚜የገንዘብ ሚኒስቴር በቁጥር ማኢ 30/07/9822 በቀን 12/05/2015 በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የሚቀርብ የቀረጥና ታክስ ነጻ ጥያቄዎችን የሚስተናገዱበት ሁኔታ በተመለከተ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ጥር 15 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 7.2/0289/15 ከጉምሩክ ኮሚሽን የተላለፈ ሠርኩላር

⚜የ ፓወር ኬብል ▶POWER CABLE WITH EXTRUDED INSULATION AND THEIR ACCESSORIES FOR RATED VOLTAGES FROM 1 KV (UM = 1,2 KV) UP TO 30 KV (UM = 36 KV) –PART 1CABLES FOR RATED VOLTAGES OF 1 KV ((UM = 1,2 KV) AND 3 KV (UM = 3,6 KV)◀ አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ መስፈርትን በተመለተ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጥር 12/2015 በደብዳቤ ቁጥር 011.34/11167  የተላለፈ  ሠርኩላር

ለፓርላማ የቀረበው የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ ምን ይዟል? ⚠የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ ከሰዓት በሚያደርገው መደበኛ ስብሰባ፤ የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅን መርምሮ ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ለመምራት አጀንዳ ይዟል። ▶ በኤክሳይዝ ታክስ አዋጁ ላይ ለውጥ የተደረገባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች እንደሚከተለው ቀርበዋል:- ⤵ 🌼 ከዚህ ቀደም ከኤክሳይዝ ታክስ ነጻ የነበሩት የቴሌኮሚዩኒኬሽን አገልግሎቶች አሁን 5 በመቶ እንዲጣልባቸው ያደርጋል። 🌼 ቴሌቪዥን እና የቪድዮ ካሜራዎች ሙሉ ለሙሉ ከኤክሳይዝ ታክስ ነጻ እንዲሆኑ ማሻሻያው ላይ ቀርቧል። አሁን ባለው አሰራር ሁለቱ ምርቶች እያንዳንዳቸው 10 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ይከፈልባቸዋል። 🌼 ከቀረጥ እና ታክስ ነጻ ሆነው እቃዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ኢንቨስተሮች፣ አካል ጉዳቶኞች እና በጉምሩክ ታሪፍ ሁለተኛ መደብ የተዘረዘሩ ተቋማት የኤክሳይዝ ታክስ እንዲጣልባቸው ያደርጋል። 🌼 60 በመቶ የኤክሳይዝ ታክስ ተጥሎበት የነበረው የማይጠጣ ንጹህ አልኮል አሁን ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል በረቂቅ ህጉ ላይ ቀርቧል። በማይጠጣ ንጹህ አልኮል ላይ ተጥሎ የነበረው ታክስ፤ የኮቪድ ወረርሽኝ በተባባሰበት ወቅት ለ“ሳኒታይዘር” መስሪያ ግብዓት መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ሙሉ ለሙሉ ተነስቶ እንደነበር ይታወሳል።  🌼 ረቂቅ አዋጁ አሁን በስራ ላይ ካለው በተለየ፤ ተሽከርካሪዎችን በአራት የሚከፍልበት አዲስ አመዳደብ ይዟል። በአዲሱ ምድብ አብዛኛዎቹ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚጣለው የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ ቀንሷል። 🌼 በ2012 በወጣው አዋጅ ላይ ከ1300 ሲሲ በታች የሆኑ አዲስ ተሽከርካሪዎች በተለያዩ ምድቦች 5 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ይጣልባቸዋል። አዲሱ የአዋጅ ረቂቅ በአንጻሩ “ከ1500 ሲሲ በታች” የሚካተቱ ተሽከርካሪዎችን አዲስ ምድብ ሰጥቷቸዋል። በዚህ ምድብ ስር ባሉ ተሽከርካሪዎች ላይ 10 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ የሚጥል ድንጋጌ በአዲሱ የአዋጅ ረቂቅ ላይ ሰፍሯል። 🌼 አሁን በስራ ላይ ባለው ምደባ ከ1500 ሲሲ በልጠው፣ ከ3000 ሲሲ ግን የማይበልጡ አዲስ ተሽከርካሪዎች፤ 60 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ተጥሎባቸዋል። የአዋጅ ረቂቁ “ከ1501 እስከ 2500 ሲሲ” የሚል አዲስ ምድብ ያካተተ ሲሆን፤ በዚህ ውስጥ የሚካተቱ ተሽከርካሪዎች ላይ 20 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ይጥላል። 🌼 በአዲሱ ምድብ ከ2501 እስከ 3000 ሲሲ የሆኑ ተሽከርካሪዎች፤ 30 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ እንዲጣልባቸው በረቂቁ ላይ ቀርቧል። አሁን በስራ ላይ ያለው ምድብ ከ1800 ሲሲ በላይ የሆኑ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚጥለው የኤክሳይዝ ታክስ መቶ በመቶ (100%) ነው። 🌼 በስራ ላይ ያለው አዋጅ  ከ3000 ሲሲ በላይ የሆኑት አዲስ ተሸከርካሪዎች መቶ በመቶ (100%) ኤክሳይዝ ታክስ እንዲጥልባቸው የሚያደርግ ሲሆን ረቂቅ አዋጁ ይህንን የታክስ ምጣኔ ወደ 60 በመቶ ቀንሶታል። 🌼 እንደ ከረሜላ ያሉ ስኳር የታከለባቸውን ምርቶች የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች፤ ለምርቶቻቸው የሚከፍሉት 20 በመቶ ኤክሳይዝ ታክስ ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጎ በአዋጅ ረቂቁ ላይ ቀርቧል። 🌼 የአዋጅ ረቂቁ እስካሁን ተግባራዊ ሳይደረግ የቆየው፤ ለምግብነት በተዘጋጀ ከ100 ግራም ውስጥ 40 ግራም ወይም የበለጠ “ሳቹሬትድ ስብ” የያዘ የአትክልት እና የእንስሳት ዘይት ላይ የተጣለው ታክስ “ለጊዜው” ቀሪ እንዲሆን አድርጓል። Source: ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

⚜የገንዘብ ሚኒስቴር በቁጥር ማኢ 30/07/9728  በቀን 20/04/2015 የጉምሩክ ታሪፍ ምጣኔ  ማሻሻያ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ማሻሻያው ከታህሳስ 25 ቀን 2015 ጀምሮ ተቀባይነት በሚያገኙ ሰነዶች ላይ ተግባራዊ እንዲደረግ በዛሬው ዕለት ታህሣስ 27 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 4/0480/15 ከጉምሩክ ኮሚሽን የተላለፈ ሠርኩላር