Ethiopian Customs Clearing Agents
Open in Telegram
6 613
Subscribers
+424 hours
+427 days
+23430 days
Posts Archive
⚠አስቸኳይ
⚠Urgent
⚜ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሬ የማይፈቀድላቸው እቃዎች በተመለከተ ከጉምሩክ ኮሚሽን በዛሬው ዕለት ነሃሴ 26 ቀን 2015 ከጉምሩክ ኮሚሽን የተላለፈ እና ነሃሴ 11 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 4/0051/16 የተላለፈ ሠርኩላር ማሻሻያ
🏵የውጭ ምንዛሪ ክልከላ ውሳኔ ከመተላለፉ አስቀድሞ በተሰጠ የባንክ ፈቃድ እና የባንክ ፈቃድ ማራዘሚያ ተሸከርካሪዎች ወደ አገር እየገቡ በመሆኑ አስመጪዎች ዕቃቸውን አጠቃለው _ እንዲያስገቡ በቂ ጊዜ የተፈቀደ ቢሆንም በተፈቀደው ጊዜ አጠቃለው ባለማስገባታቸው ክልከላ የተደረገባቸው ተሸhርካሪዎች ወደ አገር እንዳይገቡ በቁጥር 4/0051/16 በቀን 11/12/2015 ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡
ሆኖም ውሳኔ ከመተላለፉ በፊት ወደ አገር ገብተው ትራንዚት አጠናቀው በተለያዩ ጉምሩክ ክሊራንስ ስነ-ስርዓት ሃደቶች ላይ የሚገኙ በተመላሽ ኢትዮጵያውያን ስም ተመዝግበው አገር ውስጥ የገቡ ፤ በመልቲ ሞዳል ስርዓት በመግባት ላይ እያሉ በመግቢያ በሮች የሚገኙ ተሸከርካሪዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ኤምባሲዎች፣ እና መንግስታዊ መ/ቤቶች በቀጣይነት ወደ አገር የሚያስገቧቸው ተሸከርካሪዎች በጉምሩክ በኩል የሚስተናገዱበት አግባብ በግልጽ መወሰን አስፈልጓል::
1. የውጭ ምንዛሪ ክልከላ ከመደረጉ በፊት በተሰጠ የባንክ ፈቃድ፤ በባንኮች በኩል በተሰጠ ህጋዊ የባንክ ፈቃድ መጠቀሚያ ጊዜ ማራዘሚያ እና ህጋዊ ስልጣን በተሰጠው አካል በተሰጠ ፈቃድ ወደ አገር ገብተው ትራንዚት ያጠናቀቁ እና በክሊራንስ ሃደት ላይ የሚገኙ ተሸከርካሪዎች በተመለከተ አስፈላጊው ቀረጥና ታክስ ተከፍሎ ወይም አግባብ ባለው አካል በተሰጠ የቀረጥና ታክስ ነጻ ፈቃድ የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ተፈፅሞባቸው እንዲስተናገዱ እንዲደረግ፤
2. በተመላሽ ኢትዮጵያዊ ስም አገር ውስጥ ገብተው በቅ/ጽ/ቤቶች የሚገኙ ተሸከርካሪዎች በተመለከተ በኮሚሽኑ በኩል በተደረገ ጥናት ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ቀረጥና ታክስ ከፍለው አንድ ተሸከርካሪ ወደ አገር የማስገባትን መብት በመጠቀም ህጋዊ መብት ለሌላቸው አካላት ተሽከርካሪን ወደ አገር እያስገቡ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ስለሆነም ይህ ድርጊት ህጋዊ አሰራሩን ያልተከተለ ስለሆነ በተመላሽ ኢትዮጵያዊያን ስም ተመዝግበው አገር ውስጥ የደረሱ ተሸከርካሪዎች በስማቸው የተመዘገቡ ተመላሽ ኢትዮጵያውያን በአካል እንዲቀርቡ እየተደረገ ዊዝሆልዲንግ ታክስን ጨምሮ የተሽከርካሪውን ሙሉ ቀረጥና ታክስ መክፈላቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨማሪነት የቀረጥና ታክሱን 10 በመቶ ቅጣት እንዲከፍሉ እየተደረገ እንዲስተናገዱ ተወስኗል
3. በመልቲ ሞዳል ስርዓት በመጓጓዝ ላይ ሆነው ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት በትራንዚት ሃደት ላይ ሆነው በመግቢያ በር በሚገኙ የጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች ቁጥጥር ስር የሚገኙ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ ወደ መዳረሻ ጣቢያ እንዲጓጓዙ ሆኖ እንደ አግባብነቱ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1 እና 2 በተወሰነው አግባብ እንዲስተናገዱ ተወስኗል፤
4. የዓለም አቀፍ ድርጅቶች፤ ኢምባሲዎች እና በልዩ ሁኔታ በኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ እና በጉምሩክ ኮሚሽን በህግ አግባብ በልዩ ሁኔታ ፈቃድ አግኝተው ወደ አገር ያልገቡ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ እገዳው የማይመለከታቸው መሆኑ ታውቆ ትራንዚት መፍቀድን ጨምሮ በቀጣይነት የጉምሩክ አገልግሎት እንዲያገኙ ተወስኗል፡
If Interested ......
ቀን 17/12/2015 ዓ.ም
ማስታወቂያ
በ4ኛ ዙር የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ለወሰዳችሁ፤
በ4ኛ ዙር የአዳዲስ የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ከወሰዳችሁ ሰልጣኞች ውስጥ ከዚህ በታች ስም ዝርዝራችሁ የተጠቀሳችሁ የተሰጣችሁን የምዘና ፈተና 75 በመቶና ከዚያ በላይ በማምጣት ያለፋችሁ በመሆኑ የሙያ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የተዘጋጀላችሁ ሲሆን
- ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ
- ውክልና ከሆነ በውልና ማስረጃ የተረጋገጠ ህጋዊ የውክልና ማስረጃ እንዲሁም
- ስም ዝርዝራችሁ ያለበትን ተራ ቁጥር በመያዝ
ከመስቀል አደባባይ ወደ ሳሪስ በሚወስደው መንገድ መሻለኪያ ድልድዩ ፊት ለፊት በሚገኘው የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት 8ኛ ፎቅ የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት በመምጣት ሰርተፍኬት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ስም ዝርዝራችሁ የሌለ ሰልጣኞች በዚሁ የቴሌግራም ገጽ የሚለቀቁ የተለያዩ ማስታወቂያዎችን እንድትከታተሉ እናሳስባለን፡፡
በተጨማሪም በ3ኛ ዙር የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ተሳተፋችሁ ድጋሚ ፈተና (Re-Exam) ወስዳችሁ የማፊያ ነጥብ ያስመዘገባችሁትን ሰልጣኞች ስም ዝርዝር በቅርብ በደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት የቴሌግራም ገጽ የምናሳውቅ መሆኑን አውቃችሁ ማስታወቂያ እንድትከታተሉ እናሳስባለን፡፡
በጉምሩክ ኮሚሽን
የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት
