E tech
Open in Telegram
Some tech | Innovating tech solutions to elevate your business. @WISEgeneration
Show more1 112
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-2930 days
Posts Archive
1 112
ነፃነት ከምን ፣ከማን ና እስከ ምን ¿
ሀሳብ ፫
አሁንም አስባለው ሰው ለምን ነፃነቱ ከሚመገበው፣ ከሚለብሰው እና ከሚጠለልበትም በላይ ያሳስበዋል ?
እሱን ለመጠበቅ እና ለማስመለስ ህይወቱን ሳይቀር ይሰዋል ድንገት ተነስቶ ለራሱ ለሰዎችም ይተርፋል ?
ነፃነት ማጣትስ በአፋኝ ሀይል መታፈን ወይስ በራስ ሀሳብ ትብታብ ተተብትቦ መውደቅ?
የታሰረ የተጨቆነስ ሕመሙ እሰከምን ነው ጥልቀቱ፣የተፈታስ እስከምን ነው ፍታቱ?
ተይቃለው እነማን ወስጣዊ ወይንም ውጫዊ ደንነታችንን ይቀሙናል?
መሀበረሰብ፣ አገዛዝ፣አመራር ልንለው እንችላለን ሀይማኖት ቤተሰብ ወይስ እራሳችን የየቱ ንፍገት ይከፋል ይበልጥ ያማል ይበልጥ ለመፈልቀቅ ያለፋ?
ደህንነት ለነፃነት ምን ያህል ግብሀቱ ይሆን? የኛ ልጅነትስ ምን ያህል ለነፃ መሆን ምሳሌ ነው?
የአእምሮ በሚገባው ልክ ከባርነት አስተሳሰብ የሚላቀቀው መቼ ነው ?
ለምን ተገዝተን ለምንስ ታስረናል?
ግን ነፃነት የባርነት ተቃራኒ ይሆን ይሆን እነዴ?
ለመሆኑ አርነት ነፃነት ነው ነፃ ለመውጣትስ ለምህ ያህል ግዜ ህሊና መታሰር አለበት ?ለመሆኑ ለህይወት ሎሌ ያልሆነ እርሱ ማነው በነገ ናፍቆት በትላን ትይኔት ያልታሰረስ ማነው???
ነፃ የወጡለትስ የትላንቱ መታሰር ካልተፋቀ ትላንት አያመንምን??
በነፃነት መታሰርስ
የሰው ልጅ በጣሙን ፈልጎ ያገኘው አጁ ላይ ሲደርስ እንደሚረክሰው ሁሉ በእጁም ሆኖ ካተፋው እና ነፃነቱ ዳግም ከገዛው ባሪያ ሆነ ማለት አይደለምን ?
ከነፃነት ባርነት ነፃ ለመውጣትስ ለምን ያህል ግዜ ነፃነቱን ይሻል ይታገላል ከራሱ ተጣልቶ ራሱን ይሰዋ ይሆን?
ነፃነት እራስን የለተፃራሪ መሆን ቢሆንስ ብዬ አሰብኩን እንደዛ ካልሆነማ ሁሉ ነፃነቱን እንዳሰሰ ይሆናላ ወደ ተቀባዩ ጨቋኙ አፈር ሚሄደው ....
እኛ ሰዎች ከነፃነታችን ይልቅ ለምን ለነፃነታችን ሳማ ለሆኑት እውቅና እንሰጣለን እንደዛስ ከሆነ በውለታቸው ታሰርን አይደለም ከዛስ በኋላ ነፃነታችን ታሰረ ማለት አይደለምን?
ሁላችን ነፃ የወጣን ግን ነፃነት ያሰረን፤ የሀርነት ባሪያ አይደለንምን??
ምን የሚቋጭ የተቋጨ ሀሳብ አይኖርም
በርግጥ ነገን ለማየት መቆም አማራጨ አይደለም እንራመድ እንራመድ ወይ እንፏቀቅ ግን አንቁም ታላቅን ጨለማ ትንሽ ብርሀን ታጠፋዋለት
ክብረት ይስጥልኝ 🙏🙏
ብሌን
Make Ethiopia Great Again
Rise and Shine
1 112
ሀሳብ፪
እራስን መውደድ እና የገዘፈ የራስ አምልኮ
ይሄ ሀሳብ በአብዛኛ ያለ ግን የማናስተውለው ወይም ልክ ካለፈ እራስ መዳድነት ጋር በተለዋዋጭ ደረጃ የምንጠቀው ቃል ይሆናል።
በርግጥ ስው እራሱ ይወዳል? እስከምን ድረስ....
እራሳቸውን የሚጎዱ ስዎችስ እራሳቸውን ስለሚጠሉ ወይስ የውስጣቸውን ጮኸት ለመሸሽ ሲሮጡ?
እራስን መውደድ በልኩ በድርበቡ መልካም ቢሆንም ቅሉ ልክን ካለፈ ደግሞ shelfishness ለሚባል የራስ አምልኮ አና ስዎችን እንደ መሰላል መርገጥንም ያመጣል።
እራስን መውደድ ለራስ በቂ ግምት መስጠትን ፣እራስን መረዳት እና በቂ ክብር መስጠትን ይጨምራል።
የግድ ስለ ህልሞቻችን ስናወራ የግድ ለራስ የሚሰጥ ተመጣጣኝ ክብር እና መውደድ የነገን የብርሃን ልቀት መጠን ለመቋቋም በመከራም ለመፅናት መልካሙን የስኬት ማማ ለመቀዳጀት ከማይገቡን ውዳቂ ስፈራን ለቀን መራመድ አለብን።
እራስን ለመውደድ የሚቀለው እራስን በአግባቡ መረዳት የጠበቅብናል የእኛን አቅም ስንረዳ እራሳችንን እንቀበለዋለን ተቀብለን እንወደዋለን ከዛም እናከብረዋለን ስናከብረው ለከበረው ሰውነታችን የሚገባውን ቦታ እንመርጥለታለን በርግጥ ይሄ እራስን መውደድ እንጂ እራስን ማመለክ ነውን??
ይሄ ስጋን ከማዋደድ ጋር ታላቅ ልዩነት አለው በርግጥ የሰው ልጅ ነብስ የከበረች ናትና የግድ ለተፈቀደላት አለማ ኖራ ማለፍ አለባት።
ስለ እራስ አምልኮ(selfishness )
ይሄ ደግሞ ለራስ የሚሰጥ ከፍተኛ በእኔነት መታወር ነው። እርግጥ ነው ስው እራሱን ከጠላ ነብሱን ያረክሳታ ብሆንም ከሚገባው በላይ ቢወዳትም ሌሎችን በመጉዳት ያቆስላታል።
ስው ለምን እራሱን ያመልካል ይሄ ተፈጥሮዊ ወይስ አካባቢችን የጫነብን???
እራስን መውደድ ከፍርሃትስ ይመጣል ወይ የሰዎችን መንጠቅ ሱሰኝነት ይሆን??
ሰው እራሱን መውደዱ እና ነብሱን ማክበሩ እስከምን??
selfishness ለእራስ ማስበለጥ ወይስ እራስን የማስመለጫ መልካም ገፃታችንን መገንቢያችን ???
ምን አልባት አስተዳደግ እና የማህበረሰብ ተፅኖስ ይኖርበት ይችል ይሆን?
አለም የምንፈልገውን ሁሉ ይዛለች ወይስ የምንፈልገው ሁሉ በስግብግብነት ልምሻ ተይዟል?
የታሰረው እኛነታችን እራስን በመውደድ ወይሰ ከራስ ርቆ በመዝመት ይበልጥ ቀርበን እንወደዋለን ነው ርቀን እናመልከዋለን???
የመሮጥ እና የመሻገር ፍላጎታችንስ እራስ ጥሎ ወይስ ሳንሆን ነን ብለን በተቀበልነው እኛነት ተድበስብሶ ሳንወድ ሳንጠለው ይዘነው እንኑር?????
መልሱንም ጥያቄውንም ለእናተ ትቻለው
ሰናይ ይግጠመን 🙏
ብሌን
Make Ethiopia Great Again
1 112
ሀሳብ፩
ሰው አንድን ጥፋት በመድገም ምን ሊማር ይችላል ብዬ ማስብ ጀመርኩን?
በዚህ ውስጥ our mistakes are our lesson የሚሉን ሰዎች በተደጋጋሚ በአከባቢችን እንደ አሸን እየፈሉ ይገኛሉ።
ወይንም ደግሞ ጥፋትን እና ስህተትን በተሻለ ቃል አመቻምቾ ማቅረብን ቃላትን የአለአግባብ የሚሰኩ እና በተሻለ የሚያብራሩ የሰው ልጅ በእንቅፋቱ እንኳን ወደ ፊት ከወደቀ በስንት ጥፋቶቹ ነው የሚማረው ???
መቼም አብዛኞቻችን ጥፋትን ላለመድገም ከራሳችን የታገልንባቸው ብዙ ዘመን እንዳሉ ገምታለው በዛ ሁሉ ውስጥስ ስለ ጥፋታችን ስንት ግዜ ሰርተን ለራሳችን ይቅርታ አድርገናል ?
ስንት ግዜ ስልችግሩ ሳይሆን ስለመፍትሄው አውርተናል??
ስንተስ ግዜ በጥፋት የድግግሞሽ አዙሪት በአከባቢያችን ያሉትነሰ ሰዎቾ ስናግዝ የችግሩን ወይም ጥፋት የመሰለንን ነገር መሰረት ተረድተን ቀርበናል?
ነግረን መክረን አስተምረን ተሳክቶልን ግን ሰውዬውን ከራሱ አስተርቀነውል?
ሰዎች ሁሌም ወደፊት ሲሮጥ ወደኋላ ከሚጎትታቸው የራሱ የተከላለሰ ሀሳብ ለማትረፍ ምን ሰርተናን?
ነው እኛ በገባን ልክ ብቻ ቃላትን ዘርግፈን ነው የተመለስነው?
ችግር መፍታት ማለትስ የችግሩን ምንጭ ማድረቅ ነው ለ ችግሩ የምንሰጠውን response ማስተካከል??
በጥፋተኛነት ውስጥ ያለፉ ሰዎች ጥሩ አቅጣጫ ጠቋሚ የሚሆኑትስ እንደም ነው???
እነርሱስ ስንቴ ይሆን በጥፋት እጣቢ የታጠቡት?
ሀገራችን የተማረ የነቃ ትውልድን ትሻለች ምክኒያቱ ደግሞ እያንዳዳችን የጨለማዋ ማሾ ስለሆንን አብርተን በርተን በርትተን እናሻግራታለን ግን ያሰው ስኬታማ ሙሉ ሰው ለመሆን ስንቴ መሳሳት ስንቴ ከራሱ ማጣላት ስንቴ ከራሱ መታረቅ አለበት ¿¿¿¿
መልሱንም ጥያቄውንም ለናንተ ትቻለው ሰናይ ቀን ይሁንለን
ክብረት ይስጥልኝ🙏
ብሌን
Make Ethiopia Great Again
1 112
በዛሬው ዕለት የሚደረገውን መርሀ-ግብር ለመወጣት አገራዊ ፍቅር ለማሳየት ይሄው ዛሬ የእውነት ተባርከናል ለአገር ክብር ለቆሙልን መከላከያዎች ክብር ብለን ሰዓቱን ጠብቀን ወደዬ ፈጣሪያችን እንፀልይ
ታዲያ በ5:30 ብቻ ብለን አንተው ሁለም ፀሎታችን ያስፈልጋቸዋል
እናመሰግናለን
እኔም ለአገሬ ጩኽት አለኝ!!!!!
መልካም ቆይታ
@cravingaction
@cravingaction
1 112
Abeny:
A call to participate in a research survey. A research project that is underway titled 'Social Entrepreneurship and Youth Empowerment: The Case of Addis Ababa, Ethiopia' is looking for participants to fill in its research questionnaire.
If you are a Social Enterprise owner or Entrepreneur, click here: https://bit.ly/3igz8rI
If you are employed in or work with (Full time or part time) a Social Enterprise: https://bit.ly/3jgcG3p
@megaygra
1 112
ጊዜህን አታባክን
በሁለት ነገሮች ላይ ጊዜህን አታባክን፡-
ለመለወጥ ፈቃደኝነት የሌለው ሰው
ባለፈው ዓመት ብዙ የታገልክለትንና የተጣጣርክለትን ሰው አስበውና አንድ ጥያቄ ጠይቅ፡- ይህ ሰው ምን ያህል ለመለወጥ ፈቃደኛ ነው? ብትመክረው፣ ብትረዳው፣ ገንዘብህን ብታፈስበትና ስሜትህ ላይ ጫና እስኪያስከትል ድረስ ብትሸከመው ለመለወጥ ፈቃደኝነት የሌለው ሰው ላይ ጊዜህን ማሳለፍ ማለት እጅግ አክሳሪ ጉዳይ ነው፡፡
ሰዎች ለመለወጥ ፈቃደኛ እስከሆኑና የቻሉትን እያደረጉ ከሆነ ምንም ነገርህን አስተባበርህ ብትደግፋቸው በጣም መልካም ነገር ነው፡፡ የመለወጥ ፈቃደኝነቱ ከሌላቸው ግን ጊዜህን እያባከንክ ነው፡፡
ልትለውጠው የማትችለው ነገር
ባለፈው ዓመት ብዙ የታገልክለትንና የተጣጣርክለትን ሁኔታ አስበውና አንድ ጥያቄ ጠይቅ፡- ይህ ሁኔታ እኔ በመታገሌና በመጨነቄ ልለውጠው የምችለው ነገር ነው? ልንለውጣቸው የሚገቡንና የምንችላቸው ነገሮች ላይ ያለ የሌለንን ነገር አስተባብረን ለመለወጥ መሞከር የሚበረታታ ጉብዝናና ቆራጥነት ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜያችንን የሚያባክኑብን ሁኔታዎች በፍጹም ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡
ለመለወጥ ፈቃደኛ በሆነውና ባልሆነው ሰው መካከል የመለየትና እንዲሁም ታግለን ልንለውጣቸው በምንችላቸውና በማንችላቸው ሁኔታዎች መካከል የመለየቱ የቤት ስራ ግን የአንተው መሆኑን አትዘንጋ፡፡
Make Ethiopia great again
@megaygra
1 112
New opportunities
DAAD Leadership for Africa Scholarship Programme 2021/2022 for African Masters Students (Fully Funded to Germany 🇩🇪
🔥Application Deadline:16 October, 2020.
✍🏾Link:
https://www.daad.de/en/the-daad/what-we-do/sustainable-development/funding-programmes/funding-programmes-for-students-a-z/leadership-for-africa/
The DAAD has launched its new scholarship programme "Leadership for Africa" with funding from the German Foreign Office. The programme supports 55 master's degrees at German universities, with the exception of the subjects of human, veterinary and dental medicine, as well as law, art, music and architecture.
Leadership for Africa offers scholarships for studies in Germany to qualified applicants in all fields of study with the exception of medicine, veterinary medicine, dentistry, law, the arts and architecture. Public health is open for application in the field of medical studies.
Benefits
If necessary: Language course (2, 4 or 6 months) in Germany before the start of the study programme including the coverage of the test fees for a German language certificate. Participation in the language course is mandatory.
Accompanying study programme
Monthly scholarship rate payments of 861 EURO
Adequate health, accident and private/personal liability insurance in Germany.
Travel allowance.
One-off study allowance.
@megaygra
1 112
ያገዘፍከውና ያሳነስከው
የዛሬዋ ሕይወት በትናንትናውና በነገው መካከል እንደ ሳንዱዊች የተጣበቀች ሂደት ነች፡፡ እነዚህ ሁለቱ የሕይወት ገጽታዎች በዛሬው የሕይወትህ ሂደት ላይ ትልቅ ድርሻ አላቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከእነዚህ ሁለት ገጽታዎች መካከል ያገዘፈው ህይወትህን የማንቀሳቀስ አቅም አለው፡፡
የትናንትናውን ስታገዝፈው፣ የነገው ይደበዝዛል፤ የነገውን ስታገዝፈው ደግሞ የትናንትናው ይደበዝዛል፡፡ በእነዚህ ሁለት ምርጫዎች መካከል የመወሰን መብቱም አቅሙም አለህ፡፡ ብዙ የተሳካላቸው ሰዎች የትናንትናውን ልምምዳቸው “መልካምም” ሆነ “መጥፎ” ያንን ሳይክዱና ፈጽመው ሳይጥሉት ነገር ግን ከትናንትናው ይልቅ የነጋቸውን በማግዘፍ እንደሚያምኑ ይናገራሉ፡፡
የትናንትናውን በማግዘፍና የነገውን በማግዘፍ መካከል መምረጥ ማለት በመቃብር ውስጥ ባለውና በመሕጸን ውስጥ ባለው መካከል እንደመምረጥ ነው፡፡ የትናንትናህ መቃብር ውስጥ ነው - ሞቷል! በተቃራኒው፣ የነገህ ደግሞ በማህጸን ውስጥ ነው - ሊወለድ ተዘጋጅቷል! የትኛውን ትመርጣለህ? ለየጥኛው ትኖራለህ? የትናውን ስታሰላስል ታሳልፋለህ? ወደየትኛው አቅጣጫ መሄድ ትፈልጋለህ?
ያለፈው ታሪክ አስፈላጊነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ካለፈው ታሪክ ይልቅ የነገው ራእይህ ሲገዝፍ ሕይወት ወደፊት ትሄዳለች፡፡ ከመጣህበት ይልቅ የምትሄድበት ሲገዝፍ! ካለፈው ስቃይ ይልቅ ከዚያ በመማር የያዝከው የመለወጥ ሂደት ሲልቅ! ካለፈው ስኬት ይልቅ የነገው የላቀ ደረጃ ሲተልቅ! አስገራሚ ሕይወት!!! አስገራሚ የወደፊት!!!
Make Ethiopia great again
@megaygra
1 112
የቅርብና የሩቅ ጸጸቶች
ሕሊና እንዳለው ሰው በብዙ አይነት ነገር እንጸጸታለን፡፡ ለምሳሌ …
• አንድን ውሳኔ በመወሰናችን ወይም ባለመወሰናችን ምክንያት ያመለጠንን እድል በማሰብ እንጸጸታለን፡፡ “ምነው በቶሎ በወሰንኩኝ ኖሮ … ምነው ከውሳኔ በዘገየሁ ኖሮ” …
• የማይሆን የፍቅር ሕይወት ውስጥ በመግባታችን ምክንያት በደረሰብን ጉዳት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው ከዚህ ሰው ጓደኝነት ባልጀመርኩኝ ኖሮ … ምነው ምርጫዬን ባስተካከልኩ ኖሮ” …
• ሰውን አምነን ከእጃችን ገንዘብ በማውጣታችን ምክንያት በደረሰብን የክህደት ሁኔታ እንጸጸታለን፡፡ “ምነው እምቢ ባልኩኝ ኖሮ … ምነው ባላመንኩት ኖሮ” …
• በማይረባ ምክንያት ከወዳጆቻችን ጋር በመጣላታችን ምክንያት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው በታገስኩት ኖሮ … ምነው ነገሩን ቀለል አድርጌ በያዝኩት ኖሮ” …
• በሰዎች የግል ውሳኔ ገብተንና ሰዎቹን ለአንድ ተግባር ገፋፍተናቸው በሰዎቹ ላይ በደረሰው አስከፊ ሁኔታ ምክንያት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው አርፌ በተቀመትኩኝ ኖሮ … ምነው ሰውየው የራሱን ውሳኔ እንዲወስን በተውኩት ኖሮ” …
አሁን ደግሞ ትክክለኛውን ውሳኔ ካልወሰንን ከመጸጸት እንዳናመልጥ መንገዱን የዘጋብን ሁኔታ ጋር ተፋጥጠናል፡፡ በቅርቡ በተከሰተብን አለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደ ደቡብ ኮሪያ ያሉ አንድ አንድ ሃገሮች አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ ከብዙ ጸጸት ራሳቸውን ሲጠብቁ ሌሎቹ እንደ አሜሪካ ያሉ ሃገሮች ደግሞ ምላሽ ለመስጠት በመዘግየታቸው ምክንያት የጸጸትን ውይይት ሲያደርጉ ይደመጣሉ፡፡
አንዳንድ ጥናቶች በጊዜ ርቀትና በጸጸት መካከል ያለውን ግንኙነት ይጠቁሙናል፡፡ በቅርብ ርቀት ውስጥ ሰዎች በአብዛኛው የሚጸጸቱት ስላደረጉት ተግባር፣ ስለሰሩት ስህተትና ስለወሰዱት እርምጃ ነው፡፡ የረጅም ርቀት ጸጸቶች የሚከሰቱት በአብዛኛው ሰዎች ስላላደረጉት ነገር ነው ይሉናል፣ አዋቂዎቹ፡፡
እኛም ብንሆን ማድረግ የማይገባንን በማድረግ ለቅርብ ርቀት ጸጸት ራሳችንን እና ጋልጣለን፡፡ ማድረግ ያለብንን ነገር ባለማድረጋችን ደግሞ ቀስ ብሎ ለሚከተለን የወደፊት ጸጸት እንጋለጣለን፡፡
እናስተውል!
Make Ethiopia great again
@megaygra
1 112
“Solid character will reflect itself in consistent behavior, while poor character will seek to hide behind deceptive words and actions.”
- Dr Myles Munroe
