en
Feedback
ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር አንድ መንበር አንድ ሲኖዶስ አንድ ፓትርያርክ

ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር አንድ መንበር አንድ ሲኖዶስ አንድ ፓትርያርክ

Open in Telegram

ይህ ገጽ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ስርዓት እና ደንብ የተከተለ ሃይማኖታዊ መልእክት እሚተላለፍበት ነው ሃይማኖት እንደ አባቶቻችን ቴክኖሎጂ እንደዘመናችን! ተጠቅመን የገዳማት ታሪክ ወቅታዊ የቤ/ክ መልዕክት እና መረጃ የምንለዋወጥበት ቃለ እግዚአብሔር የምንማር" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
1 833
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሰው_ለሰው ሰው ለሰው/2/ ቢፋቀር ምነው /2/ ለሰው ይመስለዋል ብዙ የሚቆይ ግን በድንገት ያልፋል ሁሉንም/2/ ሳያይ ሀብትን ያከማቻል ቀኑን ሳያውቀው በድንገት ሲጠራ/2/ ላይከተለው አዝ የሰው ልጅ በተራው መጠራቱ ላይቀር ምነው አንዱ ለአንዱ መቃብር/2/ ባይቆፍር አይጠቅምም መጨነቅ እንዲያው ለውበት ይረግፋል ይጠፋል ሁሉም/2/ ከመሬት አዝ ዋ! ቁንጅና ከንቱ ማማርም ብላሽ አፈር ትቢያ ሲሆን ሲጨለም/2/ ሲመሽ ደሀ ባለጸጋ አንድ ነው መንገዱ በጨርቅ ተገንዞ በሳጥን/2/ መሄዱ አዝ ሰው ዙሪያውን ቢያጥር መዝጊውን ቢሠራ በሕንፃ ላይ ሕንፃ ቢያስመስል ተራራ አይቀርም መሄዱ ሁሉም/2/ በየተራ ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ

ወዳጄ ሆይ ! "ልብ ብርሃን የምትሆነው በአራት ነገሮች ነው ። የመጀመሪያው የፍቅር ፊት ስታይ ፣ ሁለተኛ መልካም ወሬ ስትሰማ ፣ ሦስተኛ ስትጸልይ ፣ አራተኛ እግዚአብሔር አዋቂ ነው ብለህ ስታምን ነው ። ነፍስ ካልተረጋጋች ሥጋ ሲንቀጠቀጥ ይኖራል ። የቀኑን ትግል አንተ ትግል ትለዋለህ ፣ እግዚአብሔር ግን የጸሎት ርእስ ይለዋል ። እግዚአብሔር እንኳን በአፍህ በልብህ የተመካኸውንም ያፈርሳል ። ትምክሕት ሲሰማህ “ሁሉ ባንተ ነው ጌታዬ” በማለት ክብርን ለአምላክህ ስጥ ። በአፍህ ምስጋና ሲሞላ በልብህ ደስታ ይሞላል ። በእጅህ ስትጎርስ በልብህ አመስግን ፤ ያን ጊዜ ሆድህና መንፈስህ እኩል ይጠግባሉ።" የቴሌግራም ቻናላችን ተቀላቀሉ፦ https://t.me/tselott የፌስቡክ ፔጂ ተቀላቀሉ፦https://www.facebook.com/Tselott

✌️ይህ እድል የእርሶ ሊሆን ይችላል በፍጹም በቸልታ አይለፉት🤞🤞 6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በሰላም በመጠናቀቁና በትግራይ ክልል አንፃራዊ ሰላም በመስፈኑ እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የቴሌብር አገልግሎት መጀመራችንን ምክንያት በማድረግ ባንካችን ያዘጋጀው የሽልማት እድል ላይ ይሳተፉ🇪🇹 የአቢሲንያ ባንክ የያጋሩ ይሸለሙ መልዕክት👇 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች! ቃል በገባነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች ለመሸለም ተዘጋጅተናል! 🇪🇹1ኛ ለ100 እድለኞች 50ሺ ብር እና 44inch LG ቴሌቪዥን፤ 🇪🇹 2ኛ ለ 150 እድለኞች 25ሺ ብር እና የSamsung 10+ የሞባይል ቀፎ፤ 🇪🇹3ኛ ለ 250 ባለ እድሎች ከ5ሺ እስከ10ሺ ብር ያስተውሉ ዕጩ ለመሆን መጀመርያ በጥንቃቄ ያንብቡ ለመሸለም ይህንን መንገድ ተከተሉ 1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/BankofAbyssinia1 https://t.me/BankofAbyssinia1 2. በመቀጠል ለ 50 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልዕክት በፍጥነት ሼር ( Forward) ያድርጉ፤ ወይም ወደ አቢሲኒያ ባንክ የመወያያ ግሩፕ ከ100 በላይ ወዳጆችዎን Add ያድርጉ። ( @BankofAbyssinia01 ) 3.እስከ ሐምሌ 10 ድረስ የሽልማቱ አሸናፊ ይሁኑ ! መልካም እድል! አሸናፊዎቹ በአቢሲንያ ባንክ የቴሌግራም ቻናላችን ላይ የምንገልፅ ይሆናል ይቀላቀሉን 👇 https://t.me/BankofAbyssinia1 #መልካም_ዕድል አቢሲኒያ ባንክ

+++ ማርታም ታገለግል ነበር+++ ማርያምና ማርታ እኅትማማቾች ናቸው፡፡ ‹ኢየሱስም ማርታንና እኅትዋን ፣ አልዓዛርንም ይወድ ነበር› (ዮሐ. 11፡5) ስለዚህም በቢታንያ በሚገኘው ቤታቸው እንግዳ ሆኖ ተገኘ፡፡ እጅግ ለሚወዱት ጌታ ፍቅራቸውን ለመግለጽ እኅትማማቾቹ ይሻላል ብለው ያሰቡትን ሁለት የተለያየ ዓይነት አቀባበል አድርገውለት ነበር፡፡ ማርታ ለምትወደው እንግዳዋ ምግብ ለማቅረብ ብዙ ተጨንቃ በጓዳ ሥራ ላይ ተወጠረች፡፡ ‹ለታላቁ ጌታ ምን ላቅርብለት ይሆን?› ብላ ተጠበበች፡፡ መቼም የምናከብረው ሰው እንግዳ ሆኖ ሲመጣ ሙያውም ሊጠፋብን ይችላል፡፡ ማርታም የገጠማት ይኼው ነው  ፣ ምኑን ከምኑ አድርጋ እንደምታቀርብ ግራ ገባት ፤ ጌታችን እንዳለው ‹በብዙ ነገር ተጨነቀች ታወከች›፡፡ እኅትዋ ማርያም ግን ሃሳቧን ጥላ ቃሉን ልትሰማ ከጌታ እግር ሥር ቁጭ አለች፡፡ ማርያምን በማርታ ዓይን ሆነን ስናያት እንግዳ ሲመጣ ሥራ ላለመሥራት ከእንግዳ ጋር ከሚቀመጡ ሥራ ጠል እኅቶች አንድዋን ትመስለናለች፡፡ እኅትዋ ከጭስ ጋር ስትታገል ፣ ምን ልሥራ ብላ ስትርበተበት እስዋ በቤትዋ እንደ እንግዳ መቀመጥዋን ስናይ ‹ምን ዓይነቷ ግፍ የማትፈራ ናት› ብለን መታዘባችን አይቀርም፡፡ ማርታ ግን ታዝባ ዝም አላለችም፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው። ጌታችንም ኢየሱስም መልሶ፦ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።›› ሉቃ. 10፡38-42 በእኛ ግምገማ ማርታ የበለጠ ለጌታ ፍቅር ያላት ቢመስለንም ጌታችን ግን የማርታን በፍቅር ለሥራ መድከም ሳይነቅፍባት የማርያም ምርጫ ግን ‹የማይቀማ በጎ ዕድል› መሆኑን ተናገረ፡፡ እንዴት ሊሆን ይችላል? በእኅትማማቾቹ ቤት የተገኘው ሌላ እንግዳ ቢሆን ኖሮ ማርያም ያደረገችው የሚያስወቅስ ይሆን ነበር፡፡ በእነርሱ ቤት የተገኘው ግን የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱ ደግሞ የሚቀበሉት እንጂ የሚሠጡት እንግዳ አይደለም፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ እንዳለው ‹‹ማርታ ጌታ ራሱ የፈጠረውን ምግብ በገበታ ልታቀርብለት›› ተጨነቀች፡፡(Martha gave him to eat: viands which He had created she placed before Him) @deaqonhanok የዋኋ ማርታ ያላወቀችው ነገር እርሱ ደስ ብሎት የሚበላው ምግብ እርስዋ የምትሠራው ዓይነት ምግብ እንዳልሆነ ነው፡፡ እንደ ሐዋርያቱ ቀርባ ብትጠይቀው ኖሮ ፡- ‹‹አንቺ  የማታውቂው የምበላው መብል ለእኔ አለኝ›› ይላት ነበር፡፡ (ዮሐ. 4፡32) ምን ትጠጣለህ? ብትለው ለሙሴ እንደነገረው ‹ኃጢአተኛ ሲጸጸት ዕንባውን እጠጣለሁ› (ኃጥእ አመ ይኔስሕ ዕንባሁ እሰቲ) ብሎ ይመልስላት ነበር፡፡ አልጠየቀችውም እንጂ መራራ ሐሞት እስኪጠጣ ድረስ በሰው ልጅ ፍቅር ስለተጠማው ጕሮሮው ይነግራት ነበር፡፡ (‹ሰላም ለጕርዔከ በጽምአ ፍቅረ ሰብእ ሐማሚ፡፡ እስከ ስቴ ሐሞት ጥዕመ ወዘወይነ ትፍስሕት ከራሚ› እንዲል) የእርሱ ምግብና መጠጥ የሰው ልጅ ልቡን ሠጥቶ ወደ እርሱ መመለሱ ነው፡፡ ማርያም ግን የማይቀሟትን በጎ ዕድል መረጠች፡፡ ከራሱ ከጌታችን እግር ሥር ቁጭ ብሎ ከመማር በላይ ምን ዕድል አለ? ፈጣሪ ሲናገር መስማትስ እንዴት መታደል ነው? እርሱ የሚናገረው ቃል እኮ መለኮታዊ ቃል ነው! ከጌታ የሚወጣው ቃል የሚሠራና ሕያው የሆነው የራሱ የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ ‹ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል› (ዕብ. 4፡12) እርሱ የሚናገረው ቃል ሙቱን አፈፍ አድርጎ ያስነሣል ፣ ለምጻሙን ያነጻል፡፡   አስረው እንዲያመጡት ከአይሁድ የተላኩት የሮም ወታደሮች እንኳን ከትምህርቱ ጣዕም የተነሣ   ተደንቀው ‹‹እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም›› ብለው ባዶ እጃቸውን ተመልሰዋል፡፡ (ዮሐ.7፡46) የኤማሁስ መንገደኞችም ‹በመንገድ ሲናገረን ልባችን ይቃጠል አልነበረምን?› ብለዋል፡፡(ሉቃ. 24፡32) ይህ የጌታችን ድንቅ ትምህርት ማርታ ማድቤት ሆና አመለጣት፡፡ ‹ብዙ ነቢያት ሊሰሙት ወድደው ያልሰሙትን› ቃል የመስማት ዕድል ቤቷ ድረስ መጥቶላት እርስዋ ግን ሥራ ላይ ነበረች፡፡ እንደ ሙሴ ወደ ተራራ ሳትወጣ ፣ በደመና ሳትከበብ ቤቷ ድረስ እግዚአብሔር መጥቶ ሊያናግራት ሲል እስዋ ግን ምግብ እየሠራለች ነው፡፡ ‹ማርታ ግን አገልግሎት ስለበዛባት ባከነች› ይላል፡፡ ይህ ቃል በእግዚአብሔር ቤት ለምናገለግል ፣ የማርታ ችግር ላለብን ሰዎች ምንኛ ከባድ ቃል ነው? ለመቅደሱ ቀርበን ከፈጣሪ ለራቅን ፣ ጠዋት ማታ በሥራ ፣ በዕቅድ ፣ በስብሰባ ተወጥረን እንደ ማርታ ብዙ ድስት ለጣድን ለእኛ ምንኛ ከባድ ቃል ይሆን? አቡነ ሺኖዳ ‹‹እስከ ዛሬ የእግዚአብሔርን ቤት አገለገልሁ ፤ የቤቱን ጌታ የማገለግለው መቼ ይሆን?›› ብለው ነበር፡፡ ቤቱን እያገለገልን የቤቱን ጌታ ማገልገል ያቃተን ፣ በአገልግሎት ተወጥረን ከጸሎት ፣ ከንስሓ ፣ ከሥጋ ወደሙና ቃሉን ለራስ ብሎ ከመስማት ለተለየን ሰዎች እጅግ ከባድ ቃል ነው፡፡ እያገለገሉ ከፈጣሪ መራቅ እጅግ ከባድ ነው፡፡ እንደ ማርታ ፈጣሪ ባለበት ቤት እየኖሩ ከፈጣሪ መለየትም እጅግ የከፋ ነው፡፡ ማርያም የምትማርበትን ክፍል አጽድተን ፣ በኋላም ገበታውን አቅራቢ ሆነን የምንወደውን ፈጣሪ ሳንሰማው መቅረት እንዴት ያሳዝናል? ለሰብአ ሰገል ወደ ቤተልሔም ሔደው እንዲሰግዱ የጠቆሟቸው አይሁድ ነበሩ ፤ እነርሱ ግን ሔደው አልሰገዱለትም፡፡ ቅዱስ አምብሮስ እንዳለው ኖኅ መርከብ ሲሠራ የረዱት የቀን ሠራተኞች ነበሩ ፤ እነርሱ ግን ከጥፋት ውኃ አልዳኑም፡፡ ለፍቶ ደክሞ አገልግሎ ፣ ሌላውን አስተምሮ ፣ ቤተ እግዚአብሔርን ሠርቶ መኮነን እንዴት ያሳዝናል? እንደ መርፌ የሌላውን ቀዳዳ እየሠፋን የራሳችንን መስፋት ያቃተን ፣ እንደ መቋሚያ ለሌላው ድጋፍ እየሆንን ራሳችንን ማቆም ያቃተን ‹አገልግሎት ስለበዛብን የባከንን› ብዙዎች ነን፡፡ ማርታ ከቃሉ በመራቋ ምክንያት አገልግሎትዋን እንኳን በጸጥታ ማገልገል አልቻለችም፡፡ ብቻዋን መሥራትዋም አስቆጫት፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው።›› ይህ ንግግርዋ  ብዙ ጉድለት እንዳለባት ያሳያል፡፡ እኅትዋ እስከሆነች ድረስ ቀስ ብላ ጠርታ ‹ምን ማድረግሽ ነው? ነይና አግዢኝ እንጂ› ልትላት ትችል ነበር፡፡ አልዓዛር በሞተ ጊዜ በለቅሶ ቤት ‹ማርያምን በስውር ጠርታ፦ መምህሩ መጥቶአል ይጠራሽማል› ብላ እንደተናገረችው አሁንም በስውር ጠርታ ልትወቅሳት ትችል ነበር፡፡ (ዮሐ. 11፡28)  እርስዋ ግን በቀጥታ ለእኅትዋ ከመናገር ይልቅ እኅትዋን በጌታ ፊት አሳጣቻት ፣ ከእኅትዋ ይልቅ እርስዋ ለጌታ የበለጠ ፍቅር ያላት እንደሆነች የሚያሳይ ንግግር ተናረች፡፡ ሰው ቃለ እግዚአብሔር ሲጎድለው ጠበኛ ይሆናል፡፡ እርሱ እየሠራ የሌሎች አለመሥራት ያበሳጨዋል ፣ በቀጥታ ሔዶ ለሰው ችግሩን ከመናገር ይልቅ በተዘዋዋሪ መናገር ይቀልለዋል፡፡ የዋኋ ማርታ ለአገልግሎት ስትባክን የገጠማት ፈተናም ይኼው ነው፡፡

ዜና ዕረፍት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቀድሞው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ በዛሬው እለት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። (አቡቀለምሲስ) በረከታቸው ይደርብን

ጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች የቤት ባለቤት ለማድረግ የተዘጋጀ ሮስካ የተባለ የክፍያ አማራጭ አምጥቶላችኋል፡፡ በቅድሚያ ሀምሳ አምስት ሺህ ብር በመክፈል አባል ይሆናሉ በየወሩ ደግሞ ሁለት ሺህ ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተ ዝግ አካውንት ይቆጥባሉ፡፡ እጣው በየ ሶስት ወሩ የሚወጣ ሲሆን የዕጣው ባለዕድል ሲሆኑ ማህበሩን በመቀላቀል በአንድ አመት ተኩል ቤትዎን በጋራ ገንብተው የቤት ባለቤት ይሆናሉ፡፡ ሮስካ የቤት ባለቤት የሚያደርግዎ የመጨረሻ ቀላል አማራጭ፡፡ ሀያሁለት ማዞሪያ፣ ወርቁ ህንፃ ሶስተኛ ፎቅ ጂማርክ ትሬዲንግ ዋና ቢሮ ብቅ ይበሉ፣ ይመዝገቡ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በእነዚህ ስልክ ቁጥሮች በስራ ሰአት ደውለው ሊያገኙን ይችላሉ፡፡ 0948 059608 0948 059610 0948 059611 0948 059612 0948 059613 0948 059614 0948 059617 0948 059618

የመልአኩን ምክንያት ራሱ መልአኩ ቢናገረው ሳይሻል አይቀርም ፤ መልአኩ አትስገድልኝ ካለ በኋላ ያቀረበው የመጀመሪያ ምክንያት ‹‹ከአንተ ጋር የኢየሱስ ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ›› የሚል ነበር፡፡ ሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ትንሽ ሰፋ አድርጎ ‹‹ከአንተ ጋር ከወንድሞችህ ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ›› የሚል ነበር፡፡ ይህም በቀላሉ ሲብራራ ‹‹አንተ እንዴት ለእኔ ትሰግዳለህ? እኔ እና አንተ እኮ በክብር እኩል ነን ፤ ከእኔ ብትበልጥ እንጂ በምን ታንሣለህ? ከአንተ ጋር ብቻ ሳይሆን ከወንድሞችህ ከሐዋርያት ፣ ከነቢያትና የዚህን መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ሰዎች ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ›› የሚል ነው፡፡ በሥልጣንና ክብር ከእኛ እኩል የሆነ ሰው ሲያጎነብስልን ‹ኸረ ተው› ብለን እንከላከላለን ፤ ከእኛ የሚበልጥ ሰው ካጎነበሰ ደግሞ ‹‹ኸረ ግፍ እንዳታደርግብኝ ፤ በፍጹም አይገባም›› ብለን በድንጋጤ እንከላከላለን፡፡ መልአኩ በክህነቱ ከእርሱ የሚበልጠውን ፣ በንጽሕና ሕይወቱና ለሰማያዊ ምሥጢር ባለው ቅርበት ከእርሱ የማያንሰው ታላቁ ወንጌላዊ ሲሰግድለት ያደረገውም ይህንን የትሕትና ምላሽ ነው፡፡ በዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው አንድ ሰው መላእክት ‹አትስገድልኝ› ሊሉት እንኳን የሚችሉት ወይ እንደ ዮሐንስ ፣ ወይ እንደነቢያትና ሐዋርያት መሆን ከቻለ ወይም የመጽሐፉን ቃል መጠበቅ ከቻለ ብቻ ነው፡፡ ዮሐንስ ተው እያለውም ለመልአኩ ደግሞ የሰገደው የመልአኩን የትሕትና ንግግር ‹ለመላእክት ስግደት ፈጽሞ አይገባም› ማለት እንደልሆነ ስለተረዳ ነው፡፡ ሰዎች በአክብሮት ስንነሣላቸው ‹ኸረ አይገባም› ቢሉን ‹አሃ አክብሮ መነሣት አይገባም ማለት ነው ፤ እንደዚያ ከሆነማ ሁለተኛ አልነሣም› እንደማንለው ዮሐንስም መልአኩ እየነገረውም ደግሞ ሰግዶለታል፡፡ የዮሐንስ ራእይ በምዕራፍ ሃያ ሁለት ላይ ተጠናቀቀ እንጂ ሃያ ሦስተኛ ምዕራፍ ኖሮት ቢሆንና ዮሐንስ ለሦስተኛ ጊዜ መልአክ አጋጥሞት ቢሆን ኖሮ ለሦስተኛ ጊዜ በሰገደ ነበር፡፡ በአጭሩ ለቅዱሳን የምንሰግደው ‹እግዚአብሔር እንደወደዳቸው አውቀን› ነው፡፡ ቅዱሳኑን እግዚአብሔር እንደወደዳቸው የማያውቁ ሰዎች ሐሰተኞችና የሰይጣን ማኅበርተኞች ናቸው፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳዊያን ለቅዱሳኑ ያለ ምንም ግዴታ በፍቅር እንሰግድላቸዋለን፡፡ የሰይጣን ማኅበርተኞችን ግን እግዚአብሔር በጊዜው ለቅዱሳኑ እንዲገዙ ያደርጋቸዋል ፤ እርሱ እንደወደዳቸው እንዲያውቁና እንዲሰግዱ ያስገድዳቸዋል፡፡ እንዲህ ሲል ራሱ እግዚአብሔር ለፊልድልፍያ ላለው የቤተ ክርስቲያን አባት ቃል እንደገባለት ‹‹እነሆ አይሁድ ሳይሆኑ አይሁድ ነን ከሚሉ ነገር ግን ከሚዋሹ ከሰይጣን ማኅበርተኞች አንዳንዶቹን እሠጥሃለሁ፡፡ እነሆ መጥተው በእግሮችህ ፊት ይሰግዱ ዘንድ እኔም እንደወደድሁህ ያውቁ ዘንድ አደርጋቸዋለሁ›› (ራእ. 3፡9) አንዳንድ ሰው ስግደት ‹የአምልኮ ፣ የጸጋ› ተብሎ ይሰገዳል ተብሎ ሲነገረው ስግደቱ አንድ ዓይነት ከሆነ እንዴት የአምልኮውን ከጸጋ ለይቼ መስገድ እችላለሁ? ብሎ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ዓይነቱ አስተሳሰብ ከሄድን መሰገድ የሚኖርበት በሰገድን ቁጥር በፈጣሪ ፊት ስንቆም ‹በማስከተል የምሰግደው የአምልኮ ነው› በቅዱሳን ፊት ስንቆም ደግሞ ‹በማስከተል የምሰግደው የጸጋ ነው› እያልን ማሳሰቢያ እንድንናገር የሚጠብቅ ይመስላል፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ጥያቄ በረከታቸው ይደርብንና በቅርቡ ያረፉት የቤተ ክርስቲያናችን ብርቅዬ መምህር ንቡረ ዕድ ክፍለ ዮሐንስ የሠጡትን መልስ የዚህ ጽሑፍ ማሳረጊያ እናድርገው፡፡ አንድ ወጣት ወደ ንቡረ ዕድ ሔዶ ‹በቅዱሳንና በእግዚአብሔር ፊት ስሰግድ እንዴት የአምልኮና የጸጋ የሚለውን ለይቼ መስገድ እችላለሁ?›› አላቸው፡፡ ንቡረ ዕድ ብዙም ሳይቸገሩ እንዲህ አሉት ፡- ‹‹አንተ ዝም ብለህ ስገድ ፤ እነርሱ የየድርሻቸውን ይወስዳሉ›› ሰኔ 2010 ዓም አዲስ አበባ

መግደላዊት ማርያም በዘኪዮስ ቤት ሽቶ የቀባችውን እግሩንም በዕንባዋ ያጠበችውን በራሶ ፀጉር የጠረገችውን ሴት ብዙ ሀጥያቶን ይቅር አላት ብዙ ወዳዋለችና የቴሌግራም ቻናላችን join ያድርጉ :https://t.me/tselott

++ ግጥም ዘአበው ! ( ርዕስ - እኔስ ሰው አማረኝ ) እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ የምንኩስና ግብር ምን ነበር ምሥጢሩ የክርስትና ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ መቃብሩን ክፈቱና አበው ይመስክሩ፡፡ እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ፡፡ ነብያት በመጋዝ የተሰነጠቁት ሐዋርያት ቁልቁል የተዘቀዘቁት ሰማዕታት በእሳት የተለበለቡት ቅዱሳን በገዳም ደርቀው የተገኙት ምሥጢሩ ምን ነበር? አበው ይናገሩት፡፡ ይናገር ዝቋላ ግሸን ላሊበላ የቅዱሳንን ዐፅም ለምን እንዳልበላ፡፡ ዋልድባ ይናገር ዜጋመልም ሳይቀር እንባቸው መፍሰሱ ለምን እንደነበር፡፡ ነበር ወይ ፈልገው ሹመት ሽልማት? ወይስ ሀብት ንብረት የተሟላ ቤት? ወይስ አምሯቸው ነው ፈልገው መሞት? እናንተ ገዳማት ምሥጢሩን አውሩት፡፡ ጐበዝ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና ምግባር ሃይማኖቱ በእጅጉ የቀና፡፡ እንጦንስ የወለደው በምግባር በእምነት ተምሮ ያደገ ከተክለሃይማኖት፡፡ የጊዮርጊስ ወገን የት ነው የማገኘው? በመሀል ከተማ በአራዳ ውስጥ ነው? ወይስ በዝቋላ በደብረ ሊባኖስ በደብረ ዳሞ ነው? ወገን ሰው ናፈቀኝ ዐይኔን ሰው አማረው የሃይማኖት ጀግና የትነው የማገኘው? ልግባ ወይ ዋልድባ ጫካ ካለበት ማኅበረ ሥላሴ ከቅዱሳን ቤት? አክሱም ግሸን ማርያም ከቃል ኪዳን ቦታ ይገኛል ወይ ጀግና ጠላት የሚረታ? ፈሪሐ እግዚአብሔር በልቡ ያደረ ቤተ ክርስቲያንን ያልተደፋፈረ፡፡ የት ነው የማገኘው ለሃይማኖቱ ሟች ለተዋሕዶ እምነት ጠበቃ ተሟጋች፡፡ የወገን መመኪያ የከሀዲ መቅሰፍት ማነው እሱ ጀግና ተኝቶ እንደሆነ ይነሣ ቀስቅሱት፡፡ እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ የምንኩስና ግብ ምን ነበር ምሥጢሩ? የክርስቲያን ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ? መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ፡፡ ወገን ሰው ናፈቀኝ ዐይኔን ጀግና አማረው በእምነቱ የፀና የትነው የማገኘው? ብቅ ይበል እንየው እሱ ማነው ጀግና? በጐችን ከተኩላ ነቅቶ የሚጠብቅ መከራ ቢከበው ከቶ የማይሰቀቅ የሃይማኖት ጀግና ቆራጥ ሰው ገበሬ እንደዚያ እንደ ጥንቱ ይገኛል ወይ ዛሬ? የወገን የዘመድ ጥቅም ያላወረው የመናፍቆች እጅ ኪሱን ያልዳበሰው የዓለም አሸክላ ልቡን ያልማረከው የክርስቶስ ወዳጅ እሱ ጀግና ማነው? ምሥጢርን ከምሥጢሩ አንድ አድርጐ ቀምሮ ወልድ ዋሕድ ብሎ ሃይማኖት መስክሮ እንጦንስን መቃርስን በልቡ ያኖረ ከአትናቴዎስ ከቄርሎስ ጥበብ የተማረ፡፡ ድንግል እመቤቴ ብሎ የሚመሰክር መሆኗን የሚያምን ማኅደረ እግዚአብሔር ቋቅ እንትፍ ብሎ የጠላ ክህደትን ትንታግ ምላስም ጭንግፍግፉን ልሳነ ጤዛ መናፍቅን ወልደ አርዮስ ዲቃላውን፡፡ በሰይፈ ሥላሴ የሚቀላ ጀግና ማነው ዝቅ ይበላ፡፡ ነበር ወይ ያን ጊዜ ለሹመት መጓጓት እስኪ ጎርጎርዮሰ ይምጣና ጠይቁት ፍቅርንም ይጠየቅ አባ ሕርያቆስ ምሥጢርን ጠባቂ ወይም አባ መቃርስ፡፡ የክርስቶስ ባርያ የአጋንንት መቅሰፍት ወንጌል አስተማሪ የሃይማኖት አባት ይህንን ጉድ እንዲያይ ይምጣ ተክለሃይማኖት የጸሎት ገበሬ ገብረ መንፈስ ቅዱስንም ይነሣ ቀስቅሱት ይነሣ ጊዮርጊስ ይመስክር ምሥጢር የሃይማኖት ፍቅር ምን እንደነበር፡፡ ከእናቶቻችንም አሉ ለፍጥረት ያዘኑ ዲያብሎስ እንዲማር ጌታን የለመኑ፡፡ ስንቱን ልዘርዝረው የአባቶችን ሙያ መር ብለው የወጡት ከሥጋ ገበያ ጾም ጸሎት ነበረ የሃይማኖት ጋሻ መልከስከስ ምንድነው እንደ አበደ ውሻ፡፡ እንደ መስኖ ውሃ ከነዱት መነዳት ዓላማው ምንድነው የዘመኑ ወጣት፡፡ እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና ዐይኔን ሰው አማረው ጀግና ሰው ገበሬ ሃይማኖት መስካሪ እንደ ጥንቱ ዛሬ፡፡ “ሐዋርያት በሰበሰቡአት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን” (ጸሎተ ሃይማኖት)       

በቅዱስ ላሊበላ የሚከበረውን ልዩ በዓል ምክንያት በማድረግ ከሰኔ 9-15 የገዳማት ጉብኝት ጣና ሃይቅ ላይ የተወሰኑትን ገዳማት ሌሎቹንም ጨምሮ በዙር የሚጎበኙትን ልዩ ጉዞ ይሳተፉ ባጭር ግዜ ብዙ ገዳማትን ይጎብኙ 0911646037/0945445414 የጉዞ መነሻ እና መመዝገቢያ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ( መርካቶ ) በባንክ ከፍሎ ቦታ ማስያዝ ይቻላል ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር ። https://t.me/fenotz

Share Share Share ሁሉም መገናኛ ብዙኃን እና የጥበብ ቤተሰቦች መጽሐፍ ምረቃ "ቤተ እስራኤል" ከትናንት እስከ ዛሬ የደራሲ አምሳሉ መሐሪ 16ኛው መጽሐፍ 👉ዶ/ር ወዳጄነህ ማህረነ 👉መምህር ታዬ ቦጋለ 👉አርቲስት ሥዩም ተፈራ 👉ዶ/ር አበራ ሃብቴ 👉አቶ አየለ አዴቶ 👉አቶ መስፍን አሰፋ ትንታጎቹገጣሚያን 👉ተዋናይ ተስፋሁን ከበደ( ፍራሽ አዳሽ 👉ኤፊ ማክ 👉ኤልያስ ሽታሁን 👉አስታውሰኝ ረጋሳ ማክሰኞ ሚያዚያ 11 ቀን 2014 ዓ.ም በራስ ሆቴል ከ11:00 ሰዓት ጀምሮ መግቢያ በነጻ( ከቻሉ መጽሐፉን መግዛት ሰም እና ወርቅ 0911 125788