ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር አንድ መንበር አንድ ሲኖዶስ አንድ ፓትርያርክ
Open in Telegram
ይህ ገጽ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ስርዓት እና ደንብ የተከተለ ሃይማኖታዊ መልእክት እሚተላለፍበት ነው ሃይማኖት እንደ አባቶቻችን ቴክኖሎጂ እንደዘመናችን! ተጠቅመን የገዳማት ታሪክ ወቅታዊ የቤ/ክ መልዕክት እና መረጃ የምንለዋወጥበት ቃለ እግዚአብሔር የምንማር" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
1 833
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Channel Posts
እንኳን አደረሳችሁ ለብርሃነ ትንሳኤው!
"የረድዔት አምላክ" አዲሱን ዝማሬ ያድምጡ ይጽናኑበት
https://youtu.be/aOQYUgjpNY0
Subscribe Our Channel and stay updated! 🔔
ቻናላችንን ሰብስክራይብ ላይክ ኮሜንት ሼር በማድረግ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ዝማሬዎችን ይከታተሉ!!
| 2 | No text... | 0 |
| 3 | No text... | 0 |
| 4 | የቡንጉንጋማው ቄስ
በአንድረጅስት ዑፒትስ
የትኛውም አውሮፓዊ ስሟን አስተካክሎ ሊጠራት በማይችለው፤ እንግሊዞች ቡንጉንጋማ ብለው በሚጠሯት አነስተኛ መንደር ታላቅ ነውጥ ተፈጠረ።
በዚያ ዓመት ከመንደራቸው ከፍ ብሎ የሚኖረው ተንከባካቢ አምላካቸው በተለየ መልኩ ለራሱ እዝነቱን አሳይቷል። ከብቶቹ በሁለት ሰዎች ጣቶች በሚቆጠሩ ጊደሮች በዝተዋል። ቡንጉንጋማዎችን በተመለከተ ግን ሶስት ጭንቅላት ከብቶች አጥተዋል፤ አንዷን ላም ወንዙ ሲወስዳት ሁለቱን ደግሞ እባብ ነድፏቸው አልቀዋል።
በነዚህ ሁለት ታላላቅ ስህተቶች ምክንያት ቡንጉንጋማዎች በታላቅ ቁጣ ከወንዙ አጠገብ ከሚገኘው ዛፉ ላይ ተንጠልጥሎ የሚጠብቃቸውን አምላካቸውን ከአገልጋይ ቄሱ ጋ ወንዙ ውስጥ አስጥመዋቸው ነበር...ቄሱ፤ አምላካቸው በሁለት ቀናት ውስጥ የሚያሳያቸውን ተዓምር እንዲጠብቁ ባያግባባቸው ኖሮ።
.
.
.
የቡንጉንጋማው ቄስ በመጠን የጌታውን ሲሶ ከማከሉ ውጭ አንድ ነበሩ። እርሱም ትልቅ ጭንቅላት፤ ዱባ መሳይ ሆድ፤ አጫጭር እግሮች አሉት- አምላኩ በራሱ አምሳያ እንደፈጠረው ግልፅ ነው።...ቡንጉንጋማዎች ከትልቁ አሳማ ጋ ያለው ጥብቅ ተመሳስሎሽ ባይዛቸው ኖሮ፤ ይህን ትንሽ አሳማ አውጥተው ወደ ጫካ በወረወሩት ነበር። ቄሱን ሲያስቆጡ ይበቀለናል ብለው መፍራታቸው ትክክል ሳይሆን አይቀርም።
.
.
.
በመጨረሻም ቄሱ አፉን ሲከፍት መንደርተኞቹ እጅግ አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ሰምተውት የማያውቁትን የስድብ ናዳ አወረደባቸው። ሌሊቱን እንቅልፍ አጥቶ በማደሩ የተሰማውን ብስጭት እና ጥላቻውን በሙሉ ዘረገፈባቸው።
በአዞ ለመበላት የተገባችሁ የእባብ እንቁላሎች ናችሁ፤ አምላካቸውንና አገልጋዩን ለመዝረፍ የምትፈልጉ ንፉግ እፉኝቶች፤ በዘንባባ ዛፎች ስር ተጎልታችሁ የምትውሉ ዝፍዝፎች፣ ሚስቶቻችሁ የራሳችሁን ሆነ የቄሱን ትእዛዝ እንዲፈፅሙ የማትገርፉ ሰነፎች፤ ጎረቤቶቻችሁ የማያከብሯችሁ ሆነ የማይፈሯችሁ ፈሪዎች ናችሁ አላቸው።
ቡንጉንጋማዎች ይህ ትንሽ አሳማ ከአፉ የሚተፋቸው ቃላት በሙሉ ትክክል እንደሆኑ አውቀው አንገታቸውን ደፍተው ቀሩ።...
ተፅዕኖው ከባድ ነበር። ቄሱ ምርኩዙን ዝቅ አድርጎ ተዝናና። አሁን ወቀሳውን በዝርዝር በማድረግ ሌሊቱን ለእነርሱ ሲል ከአምላኩ ቁጣ ጋ እንዴት ሲታገል እንዳደረ እና መጨረሻ ላይ እንዳግባባው መተረክ ጀመረ።
በመጀመሪያ በቀኝ እግሩ ጡብ ጡብ እያለ ለሶስት ጊዜ ያህል በቅዱሱ ዛፍ ሲዞር፣ በመቀጠል ይህንኑ ተግባር በግራ እግሩ ለሶስት ጊዜ ደገመ። ከዚያ ቂል እና ሃጢያተኞች በመሆናቸው ፈፅሞ ሊገባቸው ያልቻለውን፤ እርሱና አምላኩ ብቻ ለማወቅ የታደሉትን ያንን ተዓምረኛ ቃል ጮኽ እያለ ደጋገመ። እነዚህ የማይረቡ ዝፍዝፎች በህይወት እንዲቆዩ ሲል የታላቁ ትግል ምልክት የሆነውን በእጆቹ እና ጉልበቱ ወድቆ መሬት ለመሬት በሆዱ የመልመጥመጥ ተግባር ፈፀመ።
.
.
.
አምላክ ጦርነት እንዲከፍቱ አንዳዘዛቸው ነገራቸው።
.
.
.
አዎን፤ ትልቁ አሳማ ቡንጉንጋማዎች ጦርነት እንዲከፍቱ ይፈልጋል አላቸው። ንጋት ላይ ጦሮቻቸውን እየነቀነቁ፤ ዱላዎቻቸውን እየወዘወዙ፤ መጥረቢያዎቻቸውን ወልውለው፤ ደጋኖቻቸውን ወጥረው ወንዙን ተሻግረው፤ በዳርቻ እየሰከሰኩ፤ ፀሐይቷን ፊት ለፊት እያዩ፤ ሸለቆውን አቋርጠው ትልቁ አሳማ ሊሰጣቸው ያሰበውን የጎረቤታቸውን ግጦሽ እንዲወሩ ፈልጓል።
.
.
.
በዚያች ቀን በቡንጉንጋማ ምሽት እስኪወድቅ ድረስ ጫጫታ ነገሠ።... የዚህ ሁሉ ምክንያቱ ደግሞ ቡንጉንጋማዎች ፍፁም ጦርነት መጥላታቸው ነበር።
.
.
.
(ይህን እና ሌሎች ምርጥ አዝናኝ ተረኮች ከ"የስቅለቱ ቀን") መጽሐፍ ያገኙታል። | 0 |
| 5 | No text... | 0 |
| 6 | No text... | 0 |
| 7 | https://youtu.be/SDJfEDHjzf0 | 0 |
| 8 | በድጋሚ የተለጠፈ
#ልጅሽ_ደጅ_ላይ_ቆሟል
ከመስከረም 26 እስከ ሕዳር 6 ባሉ አንድ ቅዳሜ ማታ ከ3 ሰዓት በኋላ ማሕሌተ ጽጌን ለመቆም ወደ የካ ደብረ ሳሕል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እየሄድኩ ነው...መንገዱ ጭር ብሏል፤ አንድ ሱቅ ላይ ግን ደምበኛ (ገዢ) ቆሟል፤ እኔ መንገዴን እየቀጠልኩ ነው፡፡ ደንበኛው ቀጥ ብሎ ወደኔ መጣ እና ‹‹አባ ይበርኩኝ?›› አለኝ። ‹‹ካህን አይደለሁም›› አልኩት፣ በለበስኩት ነጠላ ጋቢና በእጄ የያዝኩት የጸሎት መጽሐፍ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደምሄድ አውቆ ነው፡፡ ‹‹አውቃለሁ›› አለኝ እና ‹‹ወደየትኛው ቤተ ክርስቲያን ነው የምትሄደው?›› ጠየቀ መለስኩለት፤ ‹‹እባክህን ልሸኝህ?›› አለኝ አዲስ ቪ 8 መኪና እያሳየኝ፣ ‹‹ብዙም ሩቅ ስላልሆነ በእግሬ ነው የምሄደው›› አልኩት....
ግለሰቡ የጠጣ ይመስላል፣ በእርግጥም የመጠጥ ሽታ ሸትቶኛል፤ በእጁ ፓኬት ሲጋራ ይዟል፣ ከሱቁ ሲመጣ ከፓኬቱ ውስጥ አንዱን አውጥቶ ከንፈሩ ላይ አድርጎ ነበር ሲቀርበኝ በጣቶቹ መሃል ያዘው፣ ምልከታዬን አስተውሎ ነው መሰለኝ የያዘውን ሲጋራ በሙሉ ጣለና በእግሩ ረጋገጠው፡፡ ‹‹አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ ልትል ነው አይደል?›› አለኝ
ከዚህ ንግግር በኋላ ስካሩ ሙሉ ለሙሉ ሲጠፋ በግልጽ ይታያል፡፡ ሁሉንም የመኪናውን በሮች ከፈተና ‹‹እንዲናፈስ ፈልጌ ነው...በሲጋራና በመጠጥ ሽታ የታጠነ መኪና ውስጥ እንዳትገባ›› አለኝ፤ በግርምት ቆምሁ፤
‹‹እባክህ አሁን እንሂድ?›› የጋቢናውን በር ብቻ ትቶ ሌሎቹን ዘጋጋና መኪናውን ለመንዳት ተዘጋጀ፤ በእምነት ገባሁና ተቀመጥኩ። መንገድ ስንጀምር በጣም ባዘነ ድምጸት
‹‹ሽሮ ሜዳ ነው ያደግሁት...ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን...ጽጌን በፍቅር ቆሜ ነው ያደግኩት...ለረጅም ዓመታት...አክሊለ ጽጌ ብዬ...ክበበ ጌራ ወርቅ ብዬ›› ዓይኖቼን ከመንገዱ ነቅዬ ወደርሱ ሳዞር መንታ መንታ ሆነው የሚወርዱ እንባዎቹን ይጠርጋል፤ ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም መስማት ብቻ
‹‹ዲግሪዬን ከያዝኩ በኋላ አንድ ዓለም አቀፍ ኤን ጂ ኦ ገባሁ...በከፍተኛ ደመወዝ በቃ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ተለያየሁ...አልሳለም፣ ኪዳን አላደርስ፣ አላስቀድስ፣ አላድር፣ አላነግስ ከሀገር ሀገር መዞር ከጓደኞቼ ጋር መጠጣት፣ ሲጋራ ማጨስ...ይኸውልህ ሚስትና ልጆች እያሉኝ ነው እዚህ ያገኘኸኝ፣ የመጠጥና የሲጋራ ጓደኞቼ በልጠውብኝ ነው ያገኘሁህ...ውስኪአቸውን ይዘው እየጠበቁኝ ነው ›› ያለቅሳል፣ እንባዎቹን ይጠርጋል፤ ግን በሥርዓት ረጋ ብሎ ይነዳል፤ መናገሩን ይቀጥላል
‹‹ተረጋግቼ ማሰብ አልፈልግም...ምክንያቱም ከተረጋጋሁ ልጅነቴን ማሰብ እጀምራለሁ...ልጅነቴን ማሰብ ከጀመርሁ ቤተ ክርስቲያንን ማሰብ እጀምራለሁ...ደጀ ሰላሟን ማሰብ እጀምራለሁ...መቅደሷን ማሰብ እጀምራለሁ፣...የዕጣኑን ሽታ ማሰብ እጀምራለሁ...ማልቀስ እጀምራለሁ...ፍቅሯን አስባለሁ....የጸናጽሉ፣ የከበሮው ድምጽ ይሰማኛል፣ በመሃል ሰይጣኔ ይመጣና እውነቴን ነው ስጠራው ነዋ የሚመጣው....ለጓደኞችህ ደውል ይለኛል....በመጠጥ ራስህን ደብቅ ይለኛል እታዘዘዋለሁ ልጆቼንና ሚስቴን ጥዬ እወጣለሁ››
አሁን ወደ ቤተክርስቲያን ታጥፈናል፤ ወደ ግቢው የሚያስገባ በር ጋር ስንደርስ ቆመ፣ ወደውስጥ ለመግባት በሮቹ የተከፈቱ ቢሆንም አልገባም፤
‹‹ወደ ውስጥ ገብተህ ትንሽ ቆይተህ አትሄድም?›› አልኩ ሀዘኑ ተጋብቶብኝ ‹‹አልገባም ግን ድሮ የሚወድሽ ልጅሽ ደጅ ቆሟል በላት›› አለና ሳግ ተናንቆት መሪውን ተደግፎ ድምጽ አሰምቶ አለቀሰ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ ለምን እንዳለቀሰ፣ እንዴት እንዳለቀሰ በዓይኔ ያየሁ መሰለኝ፤
‹‹እባክህን ግባና አልቅስ›› አልኩ፣ የቻለውን ያህል አልቅሶ እንዲወጣለት ፈለግሁ፣
‹‹ማን....እኔ? አልገባም ግን ንገርልኝ አሁንም ይወድሻል በልልኝ....እዚህ በር ላይ ቆሟል በልልኝ›› አለኝ፣ እያለቀሰ ወረድሁ
ቅዱስ ዳዊት ‹‹በኃጥአን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ›› መዝ 84፣10 ያለው ለምን እንደሆነ ይበልጥ ገባኝ። ሳላውቀው የእኔም እንባ መንገዱን ጀምሯል፤ ‹‹ማን ስለሆንኩ ነው እንዲህ በፍቅርህ የተሸከምከኝ›› አልኩ አምላኬን፣ በላዔ ሰብዕ ትዝ አለኝ በልጅነቱ የሚያስታውሳትን የድንግልን ድንቅ ስሟን ሲሰማ ከክህደት እንደተመለሰና ለመዳን ምክንያት እንደሆነችው፡፡ እናም ‹‹በልጅነቱ ይወድሽ የነበረውን ልጅሽን አስቢው ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢለት›› አልኳት
(#ዲያቆን_አብርሃም_ይኄይስ እንደጻፈው)
╔✞═┉✽👐✥👐✽┉═✞╗
❀#መልካም_የበረከት_ቀን❀
╚✞═┉✽👐✥👐✽┉═✞╝ አላቲኖስ | 0 |
| 9 | 👍 | 0 |
| 10 | No text... | 0 |
| 11 | ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ሳሙኤል_ጻድቅ (ዘደብረ ወገግ)
ጥቅምት ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ አረፉ፡፡
ጻድቁ አቡነ ሳሙኤል እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡ የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል፡፡ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው "እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ" ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡ በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡
አቡነ ተክለሃይማኖትም በአባቱ እንድሪያስ በኩል የሥጋ ዘመዱ ሲሆኑ የመንፈስ ቅዱስም አባት ሆኑትና በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናውን "ሳሙኤል" አሉት፡፡ ትርጓሜውም "እግዚአብሔር ጸለቴን ሰማኝ" ማለት ነው፡፡ ከሕፃንነትም ጀምረው በምግባር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳድገው ለዲቁና አብቅተው በኋላም አመንኩሰውታል፡፡ "ደብረ ወገግ" የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ አስቦ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ አስቦን የብርሃን ውጋጋን ሲያጥለቀልቀው መላእክትም "ቦታውን ደብረ ወገግ" (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም "ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት" ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት እንዳረገ ድርሳነ ዑራኤል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡
በቦታው ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡
ንጉሥ ዓምደ ጽዮን በክፉዎች ምክር የአባቱን ሚስት እንጀራ እናቱን በማግባቱ ምክንያት አቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው ያወገዙትን የቅዱስ ተክለሃይማኖትን ወገኖች በየአውራጃው በተናቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስንም ደሙ በምድር ላይ እስከሚንጣለል ድረስ ገርፈው ወደነበረበት ቤቱ ወሰዱት፤ ፊሊጶስም በሚሄድበት ቦታ ላይ ሳይደርስ በመንገድ ሞተ፡፡ እንድርያስ፣ አኖሬዎስና ተክለ ጽዮን ሁላቸው ከተከታዮቻቸው ጋር በሰማዕትነት አርፈው እነስድስተይ በምትባል ምድር ተቀበሩ፡፡ ጳጳሱን አቡነ ያዕቆብንም ደሙ በምድር ላይ እንደውኃ እስኪወርድ ድረስ ገርፈው ወደ ሀገሩ እንዲሰደደ አደረጉት፡፡ ከዚያም በኋላ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ ንጉሥ ዳዊት በነገሠ ጊዜ አባታችን ሳሙኤል ዘወገግን አገኘውና ‹‹መማጸኛ እንዲሆነኝ በእንድርያስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ሥራልኝ›› ብሎ ለመነውና የሩፋኤልን ቤተ ክርስቲያን ሠራለት፡፡ የእንድርያስንም አጽም ከመቅደሱ ስር አኖረው፡፡ ንጉሡም በዚያ በእንደግብጦን አውራጃ ሁሉ ላይ ፓትርያርክ አድርጎ ሾመው፡፡ በእነስድስታይ አገር ላሉ ሰዎችም ሁሉ አባት ሆናቸውና የመንፈስ ቅዱስ ልጁንም ታዲዮስን መምህርና አባት አድርጎ ሾመላቸውና ጽላልሽ ሄዶ እናቱን ይዞ ጽጋጋ ምድረ ወገግ ወስዶ አመነኮሳት፡፡
አቡነ ሳሙኤል ወደ ምድረ ርስቱ ደብረ ወገግ እየሄደ በዚያ ያሉ ልጆቹን እያጽናና ወደ እንደግብጦን አውራጃም እየተመለሰ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ ጣዖት አምላኪዎችን ወደ ክርስትና እየቀየረ፣ አጋንንትንና መመለኪያ ቦታዎቻቸውን እያጠፋ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እያነጸ በብዙ ተጋድሎ ኖረ፡፡ በቅዱስ ገድሉ ውስጥ በጣም አስገራሚ በሆነ መልኩ እጅግ ብዙ ታሪኮች ተጠቅሰዋል፡፡ እነዚህም ታሪኮች ውስጥ አቡነ ሳሙኤል በሀገራችን በጣም ብዙ ጣዖታትንና መመለኪያ ቤቶቻቸውን እያጠፉ፣ በሰዎች (በጠንቋዮች) ላይ፣ በዛፍና በባሕር ውስጥ አድሮ ይመለኩ የነበሩ ሰይጣናት አጋንንትን በሚያመልኳቸው ሰዎች ፊት እያጋለጡና እያዋረዱ ሰዎቹን አስተምረው አጥምቀው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሷቸው ቤተክርስቲያንም በመሥራት ሐዋርያትን መሰሉ፡፡
ሰይጣን አድሮባቸው የነበሩ ጠንቋዮች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ዕቃዎችን ጻድቁ እየባረኩና እየቀደሱ ለቤተክርስቲያን መሥሪያና መጠቀሚያነት ያውሉት ነበር፡፡ ይህም ገና ሳይወለዱ በአቡነ ተክለሃይማኖት ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖት ‹‹ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ይሆናል›› ብሎው ትንቢት እንደተናገሩላቸው አቡነ ሳሙኤል በሰዎች፣ በባሕርና በዛፍ ላይ እያደሩ ይመለኩ የነበሩ በጣም ብዙ አጋንንትን አጠፏቸው፡፡ ጠንቋዮችንም በውስጣቸው ካደረባቸው ሰይጣን እያላቀቁ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያደርጓቸውና ያመነኩሷቸው ነበር፡፡
ጻድቁ አባታችን አባ ሳሙኤል ወንጌልን ዞረው በማስተማር ሐዋርያትን መሰሉ፣ ከዓላውያን ጋር ለመዋጋት ሰውነታቸውን ለሞት በመስጠት ሰማዕታትን መሰሉ፣ በጾም በጸሎት በስግደት በተጋድሎ ቅዱሳን ጻድቃንን መሰሉ፣ ይህን ኃላፊና ጠፊ ዓለም ንቀው በመተው ባሕታውያንን መሰሉ፣ በደልንና ኃጢአትን በማስተሠረይ ካህናትን መሰሉ፣ በጽሕናና በቅድስና መላእክትን መሰሉ እንደዚሁም ሌሎች ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ በትእምርተ መስቀል አድርገው እንደሙሴ ባሕርን ለሁለት ከፍለዋል፣ እንደ ኢያሱ በጸሎታቸው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ተጋድሎአቸውን ፈጽመው ከጌታችን ታላቅ ቃኪዳን ተቀብለው በዚህች ዕለት በሰላም ዐርፈዋል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ | 0 |
| 12 | #አምላካችን_ናና
አምላካችን ናና በአምደ ደመና
አማኑኤል ናና ብርሀን ነህ እና/2
ታቦር አርሞንያም ሆ
የታዳለች መካን ሆ
የተገለጠባት ሆ
የመለኮት ብርሀን ሆ
አዝ
አብም መሰከረ ሆ
በደመና ሳለ ሆ
የምወደው ልጄ ሆ
ይሄነው እያለ ሆ
እሱን ስሙት ብሎ ሆ
ቃልን ተናገረ ሆ
አዝ
ከሞቱት ሙሴ ሆ
ኤሊያስ ከህያዋን ሆ
ቆመው መሰከሩ ሆ
በቀኝ በግራ ሆ
ጴጥሮስ ዮሐንስም ሆ
የቆመላቸው ሆ
አምላክ ጌትነቱን ሆ
ገልጦ ያሳያቸው ሆ
የከበሩ ናቸው ሆ
ያዩት አይኖቻቸው ሆ
አዝ
ታቦር አርሞንያም ሆ
የታደለች መካን ሆ
የተገለጠባት ሆ
የመለኮት ብርሀን ሆ
አዝ
እኔም እመኛለው ሆ
የጴጥሮስን ምኞት ሆ
አምኖ ለመኖር ሆ
በሰማይህም ቤት ሆ
ደግሞ ለመመገብ ሆ
የቃሉን ወተት ሆ
ዓመት ዓውዳመት ድገምና ዓመት ድገምና
ፀጋ በረከት ድገምና ዓመት ሰቶናል በእውነት ድገምና ዓመት
በብርሃኑ ፀዳል ድገምና ዓመት
ህይወታችን በራ ድገምና ዓመት
ሁሉም በዘመኑ ድገምና ዓመት
ታሪክ እየሰራ ድገምና ዓመት
በቤተ-ክርስቲያን ድገምና ዓመት
ይኖራል ሲዘከር ድገምና ዓመት
የጌታችን ስራ ድገምና ዓመት
ድንቅ የተደረገው ድገምና ዓመት
በታቦር ተራራ ድገምና ዓመት
ለዓመቱ ያድርሰን ድገምና ዓመት
ሁላችን በደህና ድገምና ዓመት
ሰላም ያገናኘን ድገምና ዓመት
ጌታችን በጤና ድገምና ዓመት
ዓመት ዓውዳ አመት ድገምና ዓመት
https://t.me/fenotz | 0 |
| 13 | https://youtu.be/o3F_uEMLXyw | 0 |
| 14 | No text... | 0 |
| 15 | No text... | 0 |
| 16 | No text... | 0 |
| 17 | No text... | 0 |
| 18 | No text... | 0 |
| 19 | No text... | 0 |
| 20 | ‘’ንግግርህ ምንም ያህል እውነተኛ ቢሆን በቁጣ ከተናገርክ ሁሉንም ነገር ታጠፋዋለህ"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
የተለያዩ ቅዱሳን ያሉትን ለመማወቅ የዚህን ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ 👇
ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek | 0 |
