880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
ቀን 03/03/2016ዓም
ለተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ:-
የ2016ዓም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው ሴሚስተር የመጀመሪያ ወርሃዊ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት አድርገን እንደነበር በተለያዬ መልኩ ሰምታችሗል።
በዚህም መሠረት የመጀመሪያ ዙር ሙከራ የሚሰጠው ሐሙሰ እና ዓርብ መሆኑን እየገለፅን ፈተና የሚፈተኑትም ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ብቻ ናቸው። የKG ተማሪዎች በራሳቸው ፕሮግራም የሚመሩ ይሆናል።
Repost from Andu personal Edu. Consultant and Trainer
አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ዝውውር መመሪያ (ረቂቅ) ምን ይላል?
ትምህርት ሚኒስቴር በአጠቃላይ ትምህርት በየክፍል ደረጃው እና በየትምህርት እርከኑ በሚሰጡ የትምህርት አይነቶች ተማሪዎች የጨበጡትን እውቀት ወጥ በሆነ መንገድ በመመዘን ተማሪዎችን ከክፍል ወደ ክፍል ዝውውር ለማከናወን እንዲቻል መመሪያ (ረቂቅ) አዘጋጅቷል።
ይህ መመሪያ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ክልሎች ወጥነት ያልነበረው የክፍል ክፍል ሽግግርን የሚተካ አሰራርለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ከረቂቁ ተመልክተናል።
በዚህ መመሪያ መሰረትም፦
- ከ1ኛ - 3ኛ ክፍል ላሉ ተከታታይ ምዘና ከ70% ወስደው የማጠቃለያ ምዘና (ፈተና) ከ30 % እንዲወስዱ ያዛል። ያላለፉ ተማሪዎች በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ድጋፍ አግኝተው የሚዘጋጀውን ፈተና ተፈትነው እንዲገቡ ይደረጋል።
- ከ4ኛ - 5ኛ ላሉ ደግሞ ተከታታይ ምዘና ከ60% ወስደው የማጠቃለያ ምዘና (ፈተና) ከ40 % እንዲወስዱ ያስቀምጣል። በእነዚህ ክፍሎች ተማሪዎች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማግኘት አለባቸው።
- ከ7ኛ ወደ 8ኛ እንዲሁም ከ8ኛ ወደ 9ኛ ለሚሸጋገሩ ደግሞ 40% ተከታታይ ምዘና 60% ደግሞ የማጠቃለያ ምዘና እንደሚወስዱ ያስቀምጣል። ለማለፍም 50 ከመቶ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው።
- ከ9-11ኛ ክፍል ሂሳብ (Maths) እና እንግሊዘኛ (English) ትምህርት ከ50% በታች ያመጣ ተማሪ እንዲሁም 1-7ኛ ክፍል 6ኛን ሳይጨምር Maths እና የማስተማሪያ ቋንቋውን ከ50% በታች ካመጣ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር የማይችል እንደሆነ ተጠቅሷል።
- በመመሪያው አንኳር የትምህርት ዓይነት ተብለው የተለዩ የትምህርት አይነቶች ሲቀመጡ ለአንደኛ እና ለመካከለኛ ደረጃ የትምህርት እርከኖች ትምህርቱ የሚሰጥበት ቋንቋ እና የሒሳብ ትምህርት ዓይነቶች እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና የሒሳብ ትምህርት አንኳር ዓይነቶች ሆነው ተለይተዋል።
- በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍሎች ላይ በሚሰጡ ፈተናዎች የማለፊያ ነጥብ ካላገኘ ለአንድ ጊዜ በትምህርት ቤቱ በመደበኛነት ትምህርት እንዲከታተል ይደረጋል። ነገር ግን ከ9ኛ_11ኛ ክፍል ተማሪ በአንድ ክፍል ከ2 ጊዜ በላይ ከደገመ ወይም በተከታታይ ክፍሎች ከደገመ ከትምህርት ዓለም ይሰናበታል።
- በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና በላይ ያገኘ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛዋወራል፡፡
- የአንደኛ ደረጃ ከ1-5 እና 6ኛ የክፍል ክፍል ዝውውር የራሱ የዝውውር አፈፃፀም እንደሚኖረው ሲጠቀስ በተመሳሳይ ፥ የመሀከለኛ ደረጃ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል የተማሪዎች ምዘና እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር አተገባበር የየራሳቸው ዝርዝር መመሪያ ወጥቶላቸዋል።
- አስራ አራት አመት የሚወስደውን አጠቃላይ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች በአንድ የሥራና የተግባር ትምህርት መስክ ጥናት ማጠናቀቃቸውንና በዚያም መስክ መመረቃቸውን ለማረጋገጥ የሚካሄድ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ይኖራል።
- መመሪያው ተግባራዊ የሚደረገው ከቅድመ አንደኛ ደረጃ አስከ 12ኛ ክፍል በመደበኛ እንዲሁም በማታውና በርቀት መርሃ ግብሮች ትምህርት በሚሰጡ ተቋማት ሲሆን ከዓለም አቀፍና ከውጭ ማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች በስተቀር በመንግስትና በሌሎች በሁሉም አይነት ትምህርት ቤቶች/ተቋማት/ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
እስኪፀድቅ መዘጋጀት ይበጃል
ቀን 30/02/2016
ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆችን በሙሉ ባለፈው ዕሁድ ተገናኝተን ውይይት ማድረጋችን ይታወቃል።
በዕለቱ ያልተገኙ ወላጆች ለነገ ጠርተን የነበረውን በተለያዩ ምክንያት የቀረ መሆኑን በታላቅ ይቅርታ እንገልፃለን።
ባስቸኳይ ይነበብ !
=============
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ለመላው ህብረተሰብ,
ከ ዶ/ር ሊያ ታደሰ
ካነበባችሁ በሇላ ለሁሉም እንዲደርስ Share ያድርጉ
ሞባይል ስልክ የሚያመጣብን ጣጣ
የአይን ማኩላር እርጅና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እድሜአቸው በገፋ ሰዎች ላይ ብቻ
ነበር የሚታየው።አሁን ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከ30 እስከ 40 አመት የሆኑ ወጣቶች
ሁሉ ‘ማኩላር ዲጀኔሬሽን’ የተባለና ወደ አይነ ስውርነት የሚያደርስ ሕመም
እየተጠናወታቸው መጥተዋል።
ይሄም የሆነበት ማክንያት ብዙ ሰዎች ማታ መብራት ካጠፉ በኋላ ተንቀሳቃሽ ስልክ
እየከፈቱ ያያሉ።በጭለማ ውስጥ ወይም ጨለም ባለ አካባቢ የሞባይል ስልክን ለ30
ደቂቃ እንኳን መጠቀም መታረም የማይችል አደጋ ውስጥ የሚከት ነው።ሕመሙም ካታራክት አይነት ሕመም ማስከተል ብቻ ሳይሆን የአይን ካንሰርም ያስከትላል።ይህ ደግሞ መድሃኒት የሌለው በመሆኑ አይን ሲጠፋ ብቻ ቁጭ ብሎ መመልከት ነው ይላሉ ሃኪሙ። ይህን መልዕክት ያስተላለፉት 254 የሚሆኑ የአይን ስፔሻሊት ሃኪሞች አንድ ላይ በመሆን ነው። ብዙ ሰዎች ማታ አልጋቸው ላይ ሆነው መብራት አጥፍተው ወይም ፈዘዝ ባለ መብራት ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን እንደሚጠቀሙ ስለምናውቅ አደራ፣አደራ፣ራሳችሁን ከማይድን ሕመም ጠብቁ ብለዋል።
ልብ ያለው ልብ ይበል!!!
ሞባይልን ቻርጅ ላይ አድርገው እንዳይጠቀሙ ተጠንቀቁ ። የአለም ዶክተሮች " አስጠንቅቀዋል ካንሰር የሚባል ቫይረስ በውስጡ እንዳለ ፈንድቶም ሒወት ሊያጠፋ
እንደሚችል ይመክራሉ ይህ የሞባይል ቫይረስ በዓለማችን ላይ በጣም አደገኛ ቫይረስ ነው ከፍተኛ የመግደል ፍጥነት አለው። እባካችሁ ይህን በ Telegram ኮንታክት ዝርዝራችሁ ላይ ላሉ ሰዎች ወይም ለቤተሰብ አጋሩ ሕይወት ወይም ሕይወቶችን
አትረፉ እኔ የኔን ድርሻ ተወጥቻለሁ አሁን የናንተ ተራ ነው ሼር አድርጉ
የእህትህ የወንድምህ ሀዘን የማያስደስትክ
ከሆንክ/ሽ
ይሄንን ትምህርት ሰጭ ፅሁፍ በየግሩፑ በማድረግ አስተላልፈው
እናንተም ድርሻችውን
ተወጡ ሜዳውም ፈረሱም ይሄው!!
ዶ/ር ሊያ ታደሰ
@Myppoem
ትምህርት ሚኒስቴር ‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️ ✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️ አዲስ የተማሪዎች ዝውውር መመሪያ ረቂቅ 2016ዓም ዋና ዋና ነጥቦች👇👇 👉ከዚህ በፊት በተለያዩ ክልሎች ወጥነት ያልነበረው የተከታታይ ምዘና አያያዝ ማለትም 60% ተከታታይ ምዘና 40% ማጠቃለያ ፈተና አሁን ወደ 40% ተከታታይ ምዘና 60% ማጠቃለያ ፈተና ተሰጥቶ ከ100% ይያዛል 👉ከ9-11ኛ ክፍል Maths and English ከ50% በታች ያመጣ ተማሪ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር አይችልም 👉ከ1-7ኛ ክፍል 6ኛን ሳይጨምር Maths እና የማስተማሪያ ቋንቋውን ከ50% በታች ካመጣ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር አይችልም። 👉አንድ ክፍል ደረጃ ከአንዴ በላይ ከደገመ ከትምህርት ይሰናበታል።
ጨፌ አፀደ ህፃናት እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በቀን 25/02/2016ዓም ከ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተካሔደ።
የውይይቱ ዓላማ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል ነው።
ውይይቱ ያተኮረባቸውምነጥቦች
1, የ2015ዓም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ውጤት ትንተና በዝርዝር እና በትምህርት ዓይነት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
2, የተማሪ ስነ ምግባር አያያዝ ተነስቷል።
3,የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ውጤት ለማሻሻል የተዘጋጀን የአንድ ገፅ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሔዶበታል።
4. ከመደበኛው የትምህርት ሰዓት በተጨማሪ ቅዳሜን የማጠናከሪያ ትምህርት መስጫ ቀን እንዲሆንም ከወላጅ ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል።
