880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
ጨፌ ቅድመ አንደኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው ዕለት ማለትም በቀን 09/11/2015ዓም የ2ኛ ሴሚስተር የማጠቃለያ ፕሮግራም ከተማሪ ወላጆች ጋር አካሔደ። በፕሮግራሙ ላይም የ2015ዓም የት/ቤቱ እና የወተመህ ሪፖርት እንዲሁም የተማሪዎች ውጤት ትንተና ቀርቦ ውይይት ተካሒዷል።ፕሮግራሙን ለማሳመር የት/ቤቱ የኪነ ጥበብ ክበብ የውዝዋዜ ግጥምና ሌሎችንም ዝግጅት አቅርበዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የወረዳ 03 ትምህርት ፅ/ቤት ሃላፊ, የወላጅ ተወካይ ተወካይ ወተመህ አባላት መምህራን ወላጆችና ተሸላሚ ተማሪዎች ተገኝተዋል።
በመጨረሻም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት በመስጠት እና ለሁሉም ወላጆች የልጆቻቸውን ሪፖርት ካርድ በመስጠት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
