880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
Repost from cheffie primary school 2013
ቀን 06/01/2017ዓ.ም
ጨፌ ቅድመ አንደኛ, አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2017ዓም የትምህርት ዘመን ትምህርትን ጀመረ።
በትምህርት መክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህርት ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ዋቁማ እና የወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ: ነባር ተማሪዎች ለአዳዲስ ተማሪዎች የእንኳን መጣችሁና የተለያዩ ሰነዶችን ልውውጥ በማድረግ, የትምህርት ዘመኑ ብሩህ ይሆን ዘንድ የችቦ ማብራት ስነስርዓት በማካሔድ በይፋ ተጀምሯል።
እንዲሁም በወ/ሮ ሙሉዓለም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ሱፐርቫይዘር እና በአቶ ዘሪሁን የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ሱፐርቫይዘር አማካኝነት የትምህርት ግብዓቶችን ስጦታ ማበርከት ተችሏል።
በመጨረሻም በዕለቱ ለተገኙ ተማሪዎች ስም ጠሪ መምህራን በተማሪዎች ስነምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ዙሪያ በየክፍሉ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል።
ቀን 04/01/2017
ለተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሙሉ:
ትምህርት የሚጀምረው ሰኞ በ06/01/2017ዓም ስለሆነ በዕለቱ የ2017ዓም የትምህርት ዘመንን ለመጀመር እንድትገኙ ስንለ እናሳውቃለን።
Repost from cheffie primary school 2013
ቀን 06/12/2016ዓም
የተመዘገቡ ተማሪዎች ዝርዝር ነው።
ስለሆነም ስም ዝርዝራችሁ የሌለ ተማሪዎች ካላችሁ እንድታረጋግጡ።
በተጨማሪም ከነገ 07/12/2016ዓም ጀምሮ በወጣው ፕሮግራም መሠረት መፅፍ የምንሰጥ መሆኑን በድጋሚ እናሳስባለን።
ከፕሮግራም ውጭ የሚመጣ ተማሪ በቀጣይ በሚወጣ ፕሮግራም መሠረት የሚስተናገድ ይሆናል እንጅ ያለፕሮግራም የማይተናገድ መሆኑን እናሳውቃለን።
Repost from cheffie primary school 2013
ቀን 16/11/2012ዓም
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር ወረዳ 03 አያት ኮንዶሚኒየም አካባቢ የምትኖሩ የተማሪ ወላጆች
ጨፌ ቅድመ አንደኛ,አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ2017ዓም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ከሐምሌ 1/11/2016 - 15/11/2016ዓም ነባር ተማሪዎችን ስንመዘግብ ቆይተናል።
ከዛሬ ሀምሌ 16/11/2016ዓም ጀምሮ አዳዲስ ተማሪዎችንም ምዝገባ የምናከናውን መሆኑን እናበስራለን።
ምዝገባ ሲመጡ:-
1. የተማሪው ፎቶግራፍ
2.የወላጅ ፎቶ ግራፎ
3.የተማሪው የውጤት መግለጫ ካርድ
4. ከዚህ በፊት ሲማር ከነበረበት ትምህርት ቤት መሸኛ
5. የተማሪው የልደት ሰርተፍኬት
6.የወላጅ መታወቂያ
አሟልታችሁ መቅረብ ይጠበቅባችሗል።
ለበለጠ መረጃ
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/cpscpss
