en
Feedback
Abdur-Razzaq|Al-Habeshi

Abdur-Razzaq|Al-Habeshi

Open in Telegram

والسلام على من اتبع الهدى!

Show more
3 395
Subscribers
-124 hours
+37 days
+6530 days
Posts Archive
​«ሰው ከተቸረው ጸጋ ሁሉ እንደ ጤና ያለ ትልቅ ሲሳይ የለም፤ ከሰጠውም ምጽዋት ሁሉ እንደ በጎ ምክር ያለ ውድ ስጦታ የለም፤ ከአላህም ከለመነው ነገር ሁሉ እንደ ምህረት ያለ ታላቅ ጥያቄ የለም።»
​«ሰው ከተቸረው ጸጋ ሁሉ እንደ ጤና ያለ ትልቅ ሲሳይ የለም፤ ከሰጠውም ምጽዋት ሁሉ እንደ በጎ ምክር ያለ ውድ ስጦታ የለም፤ ከአላህም ከለመነው ነገር ሁሉ እንደ ምህረት ያለ ታላቅ ጥያቄ የለም።» ✨አቡ ወህብ አልንደሉሲ ​(ሲየር አዕላም አን-ኑበላእ — 15/507)

​«ደስተኛ (የተሳካለት) ማለት ሰለፎች (ቀደምቶች) በነበሩበት መንገድ ላይ የፀና እና ኸለፎች (ተከታዮች) የፈጠሩትን አዲስ ነገር (ቢድዐ) የራቀ ነው ።» ➖ኢብኑ ሐጀር ​ 📚ፈትሑል ባሪ (13/2
«ደስተኛ (የተሳካለት) ማለት ሰለፎች (ቀደምቶች) በነበሩበት መንገድ ላይ የፀና እና ኸለፎች (ተከታዮች) የፈጠሩትን አዲስ ነገር (ቢድዐ) የራቀ ነው ።» ➖ኢብኑ ሐጀር ​ 📚ፈትሑል ባሪ (13/267)

⌛ መለኮታዊ መገለጥ ( Divine enlightenment) በሸውራራ ምልከታ ! በመለኮታዊ መገለጥ ስር የተሸገጉ ስብዕናዎች  በተቃራኒው በስጋቸው ዝንባሌና በስሜታቸው ሰመመን ውስጥ እስረኛ ሆነው ማየት የተለመደ  የተቃርኖ ሙግት ሆኖ እናስተውላለን። ወደ መለኮት የተጠጋ ሚስጥረ ፈጣሪ የተገለጠለት፣ ብፁህ ለመሆንና ሰማይ ለመንካት የቀረበን ልቦናን እየሞገተ ከተራ አፍቅሮተ ነዋይ ያልሸሸ ሰርክ የሚቋምጥ የነፍሱ ሽሽት ተላላኪ ሆኖ ይከርማል። የመለኮት ሚስጥርን መጋራት የራቀና የላቀን ፍፁም ተገዢነትንና አጎብዳጅነት ካላወረሰ ነፍስን ለመውቀስ ሰበብ ካልሆነ ለፈጣሪ አላህ መቅረብና መመሳጠርን ካልለገሰ ፍፁም ሀሰት ሙግት ነው። ሚስኪን ባሮች ላይ ለመኮፈስ እኔ ልዩ ነኝ የሚል ሽታን ለመርጨት በንፍቅና ለሚሰላችልት አምልኮ የተነሳሽነት ጣዕሩ ለሚያቃስትለት ተገዢነት ምክንያት ሲፈልግ የመገለጥን ካባን አልብሶ አይኑን በጨው አጥቦ አመስግኑኝ የሚል የለየለት የስሜቱ ባሪያ፣ የዝንባሌው ሎሌና የቅዠቱ አሽከር ነው። ይህ ስብዕና የተጠናወተው ባተሌ ንስሓ ለራቀው ማንነቱ፣ ኩነኔ ለወረረው የስደት አካሉ የሚታገል፣ ለፅድቅ የሚዋደቅና ለስርየት የሚማልድ ከመሆን ሸሽቶ የሀሰት ገፅታ ግንባታ ላይ የሚኳትን በአዞ እንባ የሚያላዝን በተውኔት የተካነ በአምልኮ የሚሰቃይ ገፀ ባህሪን መላበስ ጌጡ በመሆኑ የአያሌዎችን ቀልብ ለመማረክና እጃቸውን ለማዘርጋት ሲከብደው አይስተዋልም። በስሜቷ ዳዴ የምትንፏቀቅ ነፍሱን ቀና ለማድረግ የማይተጋ ከሻከረናው በወንጀል እድፍ ለነተበው አካሉ የሰላትን እጥበት ለነፈጋት በምናቡ ለሰከረ እንዴት መለኮታዊ መገለጥን ሲሾመውና ሲደሰኩረው ይሁንታን እንቸረዋለን? 📱https://t.me/abdurezaq27

​"ደስተኛ ሰው ማለት በትናንሽ ነገሮች፣ በእለት ተእለት ቀላል ደስታዎች እና በተለመዱ ሁነቶች መደሰት የሚችል ሰው ነው።"

إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا

📚ሱረቱ'ል ከህፍ ➖ سورة الكهف 😀خليفة الطنيجي 🔣የተረጋጋና አስተወሎት የሚያሰርፅ ቂርኣት❗️ https://t.me/abdurezaq27

"የተዋበ ግብረ-ገባዊነትን (አኽላቅ) የተጎናጸፈ ሰውን ባየሁ ቁጥር — በሕመም፣ በመከራና በነፍስ ቁስለት ሲጠበስ እንጂ አላየሁትም። ዘወትርም ከዚህ ውበት በስተጀርባ ያለውን ድብቅ ምስጢር የማየት ጉጉት ያድርብኝ ነበር። በመጨረሻም ተረዳሁ፤ ነፍሳቸውን ገርፎ ያራራት፣ በከፍታ ያነጻት እራሱ የመከራቸው እሳት ኖሯል!" 👌ጠንጣዊ

"አንዳንድ ጊዜ ለማንም ሰው ቢሆን ያን ያህል ትልቅ ቦታ እንደሌለህ ማወቅ ከሚለው እውነት ጋር መላመድ (መቀበል) አለብህ!"

"ሞኝ ማለት እንዲጠብቀው ሳይጠይቀው ሰውን ለመጠበቅ የወሰነ ሰው ነው!"

"ለእምነታቸውና ለመርሆቻቸው ሲሉ የሚሞቱ ሰዎች አሉ፤ እንዲሁም በተቃራኒው በጥቅም ደጃፍ ላይ መርሆቻቸው የሚሞቱባቸው ሰዎችም አሉ!"

በዘመናት ልውውጥና በባህላዊ ውህደቶች ምክንያት በሃይማኖታዊ የቃላት ፍች ላይ የሚከሰተው የመርገብገብና የትርጉም መሸርሸር፣ በሕጉ መሠረታዊ ድንጋጌዎች ላይ ብዥታን በመፍጠር የመንፈስ ድቅድቅነትን ይፈጥራል። በመሆኑም፣ የመለኮታዊ ድንጋጌዎችን ትክክለኛ መንፈስ ለመረዳት ወደ ቀደሙት አበው፣ ይኸውም ወደ ነቢዩ ባልደረቦችና ወደ ተከተሏቸው የታላላቅ ሊቃውንት የቃላት አጠቃቀም ጥበብ መመለስ ግዴታ ይሆናል። በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ የሚገኙት መመሪያዎች እንደሚያስረዱት፣ ሴቶች በቤታቸው እንዲረጉና በበፊቱ የድንቁርና ዘመን ይደረግ እንደነበረው ውበታቸውንና አካላቸውን እያበሻቀጡ ከመውጣት እንዲቆጠቡ ታዝዘዋል። ​በሱረቱ አን-ኑር የተጠቀሰው «ጌጣጌጣቸውንና ውበታቸውን አይግለጹ፤ ከእርሱ በግልጽ ከወጣው በስተቀር» የሚለው ቅዱስ ቃል፣ የቀደሙት ሊቃውንትና የታላቁ የቁርኣን ተፍሲር ሊቅ ዐብዱላህ ኢብኑ መስዑድ እንዳብራሩት፣ «በግልጽ ከወጣው» ሲባል ውጫዊውን ድራቢ ልብስ እንጂ ፊትንና የተሸሸጉ ውበቶችን እንደማያመለክት በግልጽ ተደንግጓል። በመሆኑም የሒጃብ ዋና መንፈስ ሴቷን በስጋዊ ዕይታዎች ከመገፈፍ መታደግና የመንፈሳዊ ውበቷን ጥበቃ ማረጋገጥ ነው።

ሰው ልጅ በመለኮታዊ እጅ ከተበጀበትና በነፍስ የተነፋበት የመጀመሪያው ምድር መረገጫ ቅጽበት ጀምሮ፣ የከበሬታና የኃፍረት ስሜት በተፈጥሮአዊ ስሪቱ ውስጥ በጥበብ ተተክሏል። ይህ ድንቅ የተፈጥሮ ስጦታ
ሰው ልጅ በመለኮታዊ እጅ ከተበጀበትና በነፍስ የተነፋበት የመጀመሪያው ምድር መረገጫ ቅጽበት ጀምሮ፣ የከበሬታና የኃፍረት ስሜት በተፈጥሮአዊ ስሪቱ ውስጥ በጥበብ ተተክሏል። ይህ ድንቅ የተፈጥሮ ስጦታ በሰው ልጅ የታሪክ ጉዞ፣ በነቢያት ጥሪና በሰማያዊ ድንጋጌዎች ሁሉ ሳይለወጥና ሳይዛባ የጸና እውነት ሆኖ ዘልቋል። ልብስ የሰው ልጅን አካላዊ ዕርቃን የመሰወር ቁሳዊ መሳሪያ ብቻ ሳይሆን፣ የነፍስን ቅድስና፣ የመንፈስን ከፍታና የስብዕናን ሙሉነት የሚያንፀባርቅ መለኮታዊ ጸጋ ነው። በሃይማኖታዊ ድንጋጌዎች ሚዛን ውስጥ የሴት ልጅ ሒጃብ የሚመደብበት መሠረታዊ ምክንያቱ፣ ሴቷን ከዕይታ ወጥመድ፣ ከስጋዊ ፍላጎት መጫወቻነትና ከንግድ ዕቃነት ነፃ አውጥቶ፣ ወደ ተከበረ የመንፈስና የኅሊና ማዕረግ የሚያሸጋግር ታላቅ መለኮታዊ ጥበቃ ሆኖ በመቆሙ ነው።

«ለወዳጅህ ልቡን የሚያሳዝነውንና ማወቁ ምንም የማይጠቅመውን ወሬ አታድርሰው፤ ይህ የወራዶች ተግባር ነውና። በሌላ በኩል ደግሞ ባለማወቁ ምክንያት ሊጎዳ የሚችልበትን እውነት ከእሱ አትሸሽግ፤ ይህ የክ
«ለወዳጅህ ልቡን የሚያሳዝነውንና ማወቁ ምንም የማይጠቅመውን ወሬ አታድርሰው፤ ይህ የወራዶች ተግባር ነውና። በሌላ በኩል ደግሞ ባለማወቁ ምክንያት ሊጎዳ የሚችልበትን እውነት ከእሱ አትሸሽግ፤ ይህ የክፉዎች ተግባር ነውና።» ✅ኢብኑ ሐዝም

«በሃብቱ (በንብረቱ) መቀነስ በሚያዝን ሰው ተደንቄአለሁ፤ እንዴትስ በእድሜው (በሕይወቱ) መቀነስ ላይ አያዝንም!» ✅የሕያ ብኑ ሙዓዝ (አላህ እዝነቱን ይለግሳቸውና)
«በሃብቱ (በንብረቱ) መቀነስ በሚያዝን ሰው ተደንቄአለሁ፤ እንዴትስ በእድሜው (በሕይወቱ) መቀነስ ላይ አያዝንም!» ✅የሕያ ብኑ ሙዓዝ (አላህ እዝነቱን ይለግሳቸውና)

قال ابن حزم رحمه الله: «لا تنصح على شرط القبول، ولا تشفع على شرط الإجابة، ولا تهب على شرط الإثابة.. ولكن على سبيل استعمال الفضل، وتأدية ما عليك من النصيحة والشفاعة، وبذل المعروف». . 📖: الأخلاق والسّير (٤٠).

ለአንድ አማኝ በህይወቱ ታላቅ የደስታና የሀሴት ለሊት የሚሆነው የሚሞትበት ቀን ነው።

​«ከነቢያት ወራሽ መሆንንና በዕርሻዎቻቸውም ውስጥ አራሽ መሆንን የሚወድ ሰው፤ ጠቃሚውን እውቀት ይማር።» ​— ኢብኑል ጀውዚ (ረሒመሁልላህ) (አት ተዝኪራ ፊል-ወዕዝ 1/55)
«ከነቢያት ወራሽ መሆንንና በዕርሻዎቻቸውም ውስጥ አራሽ መሆንን የሚወድ ሰው፤ ጠቃሚውን እውቀት ይማር።» ​— ኢብኑል ጀውዚ (ረሒመሁልላህ) (አት ተዝኪራ ፊል-ወዕዝ 1/55)

«በልብ ላይ ወንጀል መውደቁ፤ በልብስ ላይ ዘይት/ቅባት እንደመውደቅ ነው፤ ፈጥነህ ካላጠብከው በስተቀር ይሰፋል (ስር ይደዳል)።» ኢብኑ'ል ጀውዚይ ​አል-ሙድሂሽ (1/357)

‏القلب محتاج إلى ما يحفظ عليه قوته، وهو الإيمان وأوراد الطاعات؛ وإلى حمية عن المؤذى الضار، وذلك باجتناب الآثام والمعاصي وأنواع المخالفات ؛ وإلى استفراغه من مادة فاسدة تعرض له وذلك بالتوبة النصوح واستغفار غافر الخطيئات. ‏إغاثة اللهفان ‏  ١ / ٢٤

قال ‎ابن رجب رحمه الله: إصرار القلب على محبة ما يكرهه الله نقص في ‎التوحيد، وهو نوع من الشرك الخفي.
جامع العلوم والحكم (542/2)