en
Feedback
ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር ወደ ግሸን ላሊበላ ቁልቢ ገብርኤል እና ሌሎች ገዳማት ጉዞ እናዘጋጃለን

ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር ወደ ግሸን ላሊበላ ቁልቢ ገብርኤል እና ሌሎች ገዳማት ጉዞ እናዘጋጃለን

Open in Telegram

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ስርዓት እና ደንብ የተከተለ ሃይማኖታዊ መልእክት እሚተላለፍበት ነው ሃይማኖት እንደ አባቶቻችን ቴክኖሎጂ እንደዘመናችን! ተጠቅመን የገዳማት ታሪክ ወቅታዊ የቤ/ክ መልዕክት እና መረጃ የምንለዋወጥበት ቃለ እግዚአብሔር የምንማርበት ነ የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን

Show more
579
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
" ዮምሰ ሕይወት ኮነ ለሰብአ ዝንቱ ቤት " ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል(ሉቃ፣19፡9) ቤት መኖርያ ሀገር ቤተ ክርስቲያን ችግር ላለበት ቦታ ሁሉ ወዘተ መዳን ሆነለት   ቃሉ የሚያመለክተው መፍትሔ ሥሬይ ባለመድኃኒት የተገኘ የተፈጠረ ለድኅነት ለማዳን እየሠራ እየጣረ በትጋት ያለ መሆኑን መኖሩን ያሳያል።   ችግሮቹም በሀገር በቤተክርስቲያን በግል ሕይወት ላይ ፍትሕ ርትዕ ማጣት ኑሮ ጭንቀት በሽታ ሕመም ወዘተ ሁሉ የሚያሶግድ የሚፈታ የሚያድን ትሁት ምቾት የማይፈልግ የማንኛውንም ጭሆት የሚሰማ መድኃኒት የሚሆን ዛሬ ይፈለጋል "ይህ ስብስብ አባላት"      ፦"ይጸርሑ ወይብሉ ሆሣዕና....." ማቴ21፥9 ሆሣዕና እያሉ ይጮኹ ነበር   ፦ሆሣዕና ማለት_እባክህ አድነን ወይም መድኃኒትነት ማለት ነው   ይህ ሳምንት ዕለተ ሆሣዕና ስምንተኛ ሳምት ከዘወረደ ሰኞ አርባ ዘጠኝ ቀን በኢቤልዩ ስያሜ ሰባት ሱባዔ አሳልፈን የጌታችንን ሕማም የምናስታውስበት ዕለታት ቀርተውናል እንኳን አደረሳችሁ ቸርነቱ የማያልቅ መድኃኒት የሆነው የሕማም ሰው ደዌን ያውቃል ብሎ የተነበየለት ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ጥባቆቱ አይለየን ትንሣኤውን ያሳየን ፦ሆሣዕና_በሥጋም ሆነ በመንፈስ ክፋትን የሚያርቅ             ፦ከዘላለማዊ ሞትና ኃጢያት የሚያድን             ፦ታዳጊመሪ መድኃኒት ከጠላትየሚያድን   ወደ ርዕሰ ነገሩ ስንገባ ዛሬ መዳን ሆነለት የተባለው ባለታሪክ እንመልከት ምን አድርጎ ምን ሠርቶ በሥልጣን በገንዘብ በመማር በየትኛው መንገድ ተጠቅሞ የመዳን ቀን ሆነለት ?      ታሪክ፦" ወየኀሥሥ ይርአዮ "ዘኬዎስ የሚባል ስልጣንና ሀብት ያለው መሪ ታዲጊ መድኃኒት የሆነውን ጌታ ኢየሱስን ሊያይ ፈለገ   እኛ የፈለግነውን ለማግኘት ብንፈልግ አልጋ ባልጋ ሆኖ እንዳሰብነው እንዳቀድነው ስልጣንና ገንዘብ ስላለን ሰው ሠራሽና በተፈጥሮ የሚደርስብንን መሰናክል ያለጥረት ያለድካም ያለውጣ ውረድ ንስሃ ሳንገባ የበደልነውን ሳንክስ  ያላግባብ ሳንደክምበት የወሰድነውን ሳንመልስ የፈለግነውን ለማግኘት እንደማንችል ከዚህ ሰው መማር እንችላለን   ዜኬዎስ በፊቱ ሁለት ችግሮች አሉ ሰው ሠራሽ የሆነው የሰዎች ጭንቅንቅ ጭሆትና መገፋፋት አንዱን ረግጦ ማለፍ የበዛበት ፣ ሌላው ደግሞ በተፈጥሮ የተሰጠው ቁመት ማጠር ሲሆኑ ብዙ ትንታኔ ቢያስፈልገንም ፣   ፦አለቃ ነበር በስልጣኔ የነበረውን መገፋፋት በፓሊስ አጀብ ልሂድ የምፈልገውን ላግኝ አላለም ወደፊት ሮጠ እንጂ    ፦ሀብታም ባለጠጋ ነበረ በዘመኑ ጥበብ በገንዘቤ ጾታቸውን እንደሚቀይሩ የመጠን ቁመቴን ላስቀይር ሳይል ታላቅ ሾላ ላይ ለመውጣት ሮጠ ደከመ ወጣ ወረደ  ንስሃ ገባ እንጂ በሃብት በስልጣኔ እምፈልገውን ላግኝ አላለም በዘመናችን ያለነው ዛሬ እንዴት ይታያል   ፦"ወይቤሎ እስመ ዮም ሀለወኒ አዐል ቤተከ" በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል አለው በቤታችን እንዲገባ መድኃኒት እንድናገኝ ዘኬዎስን መሆን     ፦መድኃኒት ሆሣዕና የመጣው ስልጣንና ሀብት ላለው በዕውቀቴ በአነጋገሬ በስልጣኔ ዘመናዊነት በመከተሌ አገኛለሁ ለሚል ሳይሆን የልብ መሻት አሚን ተስፋ ትግስት ጥረት ሲኖር ብቻ ነው "እስመ መጽአ ወልደ እጓለ እመሕያው ይኅሥሥ ወያድኅን ዘተኀጉለ"   የሰው ልጅ የደከመውንና የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቷልና። ፦የዘላለም ቤዛነት አግኝተን ከሞተ ሥራ ኅሊናችንን እንድናነፃ የመጣ መድኃኒት ነው ፦ለተጠራነው ለእኛ በእምነት ፀንተን ለምንገኝ የዘላለም እርስት የተስፋ ቃል አንዲሰጠን መጣ ፦ታሥራ የነበረችውን አህያይቱ ዓለም አዳም ከነልጅ ልጁ በኃጢያት መከራ ተውጦ ታሥሮ የነበረውን ሁለቱን መልክተኛ መለኮትና ነፍስ ዮሐንስና ጴጥሮስ ከታሠሩበት ሲኦል ቤት ለመፍታት መጣ ስለዚህ መከራ ሳንቀበል ኃጢአት አይሰረይምና ሰውነታችንን ለማስደሰት ጭንቀታችንን ለማራቅ ርቀን ብንጓዝ በዝማሬ በእልልታ ለአንደበታችንና ለእግራችን ነጻነት ብንሰጥ ኃጢአታችንና መከራችን አይቀርምና የአህያዪቱን ትዕግስት እንይ እኛ በአርያው ፈጥሮናልና። በአርያው ለፈጠረን በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ያውጅልን

እግዚአብሔር በቸርነቱ የዘመናት ባለቤት ሁሉን የፈጠረ የዚህ ዓለም አስገኝ ጸጋውን ሊያጎናጽፈን መንግሥቱን ሊያወርሰን የፈጠረን እንኳን ለ ዐቢይ ጾም አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት አደረሳችሁ   ደብረ ዘይት የተባለበት የቤተ ክርስቲያን ማኅቶት የሆነው ቅዱስ ያሬድ ሲሰይመው ጌታችን ታላቅ ሥራ የሠራበት በመሆኑ ሰይሞታል ይኸውም ሲጠራ እኩለ ጾም መለያ ሆኖ ይጠራል ከሠራቸው ሥራዎች    ፦ሥልጣኑን ያሳየበት_ በሆሳእና ዕለት በአህያ ውርጫ ተቀምጦ ኢየሩሳሌም የገባ ከዚህ ነው    ፦የዓለም መጨረሻ የተረከበት_ ለሐዋርያት ተሰብስበው ወንበር ዘርግቶ እንደሚያስተምር የዓለም ፍጻሜ ምልክቱን ምን ሆነን መጠበቅና ከሚያስቱ መምህራን እንዲጠነቀቁ ያስተማረበት     ፦የዓረገበት _ በዚህ ዓለም የዕብራውያንን ሕግ ከኃጢአት በስተቀር ፈጽሞ ያረገበት ና በዕለተ ምጽአት ለፍርድ የሚመጣበት ሥፍራ መሆኑ ከብዙ በጥቂቱ ለመጥቀስ ነው      ደብረ ዘይት ማለት ደብር ተራራ ዘይት ከወይራ ዛፍ ስለሚገኝ በዚህ ተራራ ላይ የወይራ ዛፍ በብዛት ስለሚገኝ በዚህ ምክንት ተሰይሟል        ወይራ ጠንካራ በመሆኑ ዘይትም ብርሃን ይሰጣልና ብርሃነ ዓለም ክርስቶስ ብርሃን ሆኖበታል     ወደ ዛሬው በዓለ ደብረዘይት ስናነሳ የዘንድሮው አመት ፈተና በገባችበት ሀገራችንና ቤተክርስቲያናችን ከዘጠኙ ዐበይት ና ንዑሳን በዓላት መካከል በአንድ ቀን ሲከበሩ ዕለቱም አንድ ሲሆን በእግዚአብሔር ዘንድ ምን አስቦ ይሆን አንድ ነገር ይመጣል የሚል ትንቢት ይኖራል በልባችሁ አኑሩት   ለምሕረት ለማዳን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ቃል የተፈጸመበት    ለሰው ልጆች እንደ ሥራቸው መጠን የሚከፈልበት የፍርድ የምጽአት ቀን አብረው ይታሰባሉ    ፦ጽንሰት፡እሜቤታችን የመልአኩን መልካም ዜና የሰማችበት እግዚአብሔርና ሰው እርቅ የተጀመረበት መጋቢት 29ቀን ዓለም የተፈጠረበት ዕለተ ምጽዓት የሚፈጸምበት ሁሉም ሊሆን ግድ ነውና በመጸነሱ ይቅርታን በምጽአቱ መልካም ፍርድ ፍት ሐሴት  የምናገኝበት ይሁንልን     ፦ደብረ ዘይት ፡የሚነገረው ጌታችን ስለ ቤተ መቅደስ መፍረስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሕንጻ ሥላሴ ሰው መፍረሱ ፣የመመስገኛው ቦታ የጥጦስ ዘመን ዓይነት ሁኔታ ተፈጥሮ ቤተክርስቲያኗ አንዳንድ ድንጋይ ብር እናገኛለን ብለው እየፈነቀሉ እንዳፈረሱት ዛሬ ምኑ ተዘርዝሮ ይገለጻል ከውስጥ ከውጭ የሕንጸዋ ግንብ ድጋይ ዶግመዋ ቀኖናዋ እሴቷና ባህሏን እየፈነቀሉ እያፈረሷት ትገኛለች   ለዚህ  ኅብር በዓል ጥቅስ መዝ 49፣1 ጀምሮ ቢታይ    ፦አምላከ አማልክት እግዚአብሔር ነበበ ወጸውዓ ለምድር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር በምድር ላይ የሚኖሩ እንደፈለጋቸው  ተመችታን እንድንኖር ገነት እናረጋታለን እያሉ በምድር ገዥዎች ቤተ መንግስትም ሆነ ቤተ ክህነት ፈጣሪዋን ስላስቀየሙ በድለዋልና እንዳትመች ጠራት ቸነፈሩ ርሃቡ ደዌው ጦርነቱ እንድታፈራ አዘዛት "እግዚአብሔር ገሃደ ይመጽእ ወአምላክነሂ ኢያረምም እሳትይነድ ቅድሜሁ "   ይለናል ነቢዩ በመምህራን ይነግረናል ዝም አላለም በእሳቱ እየተፈተንን ቀልጠንም ጸንተንም እየኖርን እንገኛለን   መቅለጣችን ምንም እንዳልተፈጠረ ተመቻችተን አለማሰባችን      መጽናታችን በመከራው እየሞትን እየተፈናቀልን አኗኗራችን ችለን ፈጣሪያችንን ሳናማርር መገኘታችን ነው    እስከ መጨረሻ የሚጸና እርሱ ይድናልና ጸንተን እንኑር (ማቴ24:1)    እግዚአብሔር ቸርነቱን ይላክልን ትንሣኤውን ይግለጽልን

🕯...እንኳን አደረሳችሁ መጋቢት 27 ጥንተ ስቅለቱ ለመድኃኒነ...🙏 "ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡ ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤  ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡ ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። /ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/

ቁሙ እንከ ወኢትሑሩ ዳግመ ውስተ አርዑተ ቅኔ ፣ገላ5:1    እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ    የቆምን መስሎን ያለን ሁሉ እንዳንወድቅ ወድቀንም ሌሎች ቀድመውን እየወረዱ ከወደቁበት ሲነሱ ባለንበት ሰው የለንም እያልን ተጨብጠን ጎብጠን ወድቀን እንዳንቀር በአስተሳሰብ በአመለካከት እንጽና       ፨የእብሔር ልጆች እንኳን ለአራተኛው ሳምንት ኃጢአት በሚተውባት የምህረት ቃል የተሰማባት ለረዥም ጊዜ ሰው የለኝም ብሎ ተስፋ የቆረጠ ሰላሣ ስምንት አመት ወድቆ ተጨብጦ ጎብጦ የነበረው መጻጉዕ የዳነበት ቀን መታሰቢ "እስብክ ግዕዛነ አቡየ ፈነወኒ" ያለበት ዕለተ እሁድ ትሰመይ መጻጉዕ በጤና በሰላም ከዘመኑ በሽታ ጠብቆ አደረሳችሁ።    መጻጉዕ ማለት የወደቀ የጎበጠ የተጨበጠ የሰለለ ልሙሾ የሆነ ማለት ነው     ዕለቱን ስናስብ ወደከተማይቱ ብዙ ሕዝብ ወደሚኖሩበት የሚወጣ ግዕዛንን የሚሰብክ ከሁሉ ነጻ የሆነ አባቱ መምህሩ የላከው ሰውን እናስባለን   በከተማ ውስጥ በተለያየ የበሽታ አይነት የተጠቁ ሰው እናያለን ለምን ቢባል የከተማ ኑሮ ቀላል ነው ፣ለተቸገሩም መፍትሔ የሚሰጥ አይጠፋም ተብሎ ስለሚታሰብ   ፦አንካሳ _በሁለት አሳብ ይሚጓዝ ከሃይማኖቱ ወይ ከፖለቲካው ያለየለት በሽታ    ፦ዕውራን_በሚሄድበት የሚቅበዘበዝ ዘንጉን መሪውን የማይከተል ቢሆንም  መንገዱ የተበላሽ ዘንጉ የተሰነጠረ እጅ የሚቆረቁር የሚያቆስል ስለሆነ     ፦ዲዳ _ ጠቃሚ ነገርን ሃሳብን የማያፈልቅ ለራሱ የሚኖር በመሆኑ     ፦ጉንድሽ _አርቆ የማያስብ ራዕይ የሌለው ያለፈውን አባቶች የሚመጣው ለትውልድ የማያስብ ጊዜአዊውን የሚመለከት ስለሆነ አዝኖ  በኑሮ መንገድ እንዳይዝሉ ጦማቸውን እንዳይሆኑ አርነት የሚያወጣ የሚፈውስ አሁን ያስፈልጋል   በዕለቱ የሚነገረው የሰላሳ ስምት አመት መጻጉዕ የነበረው ሲፈወስ የሰላሳ ስምት ዘመን ታዳጊ መጻጉዕ ሆኖ እናየዋለን ዶክተር ብሮፊሰር ነበርን   ይህ በሆነበት የሰው በሽታ በሽታ የማይመስለን እንኖራለን ለመሆኑ ሕግ ጠብቀናል ብለን እንድናለን እንፈልግ ይሆናል ከውነተኛው ፈራጅ ክርስቶስ ከደዌው ድኅነት ስጦታ ተለይተን ወድቀን ተሰደን እንገኛለን   ከዚህ የባሰ እንዳያገኘን ጸንተን እንቁም ወደፈጣሪያችን ዐይነ ልቡናችንን በመሰብሰብ ኅሊናችንን በማቅናት በጸሎት እንጽና     ዓለም በፈጣሪያችን ቸርነት በአራቱ አፍላጋት ከገነት አፍልቆ እንድትረካ እንድትለማ ሕይወት እንዲኖራት አድርጎ ነበር   ዛሬ  ከላይ በዘረዘርናቸው በአራቱ የትርጓሜ ጥበባት አፍላጋት ገነት ከሆነው ሰው አእምሮ እየመነጨ ዓለም መጻጉዕ ሆኗል "ዘይሰብክ ግዕዛነ ይፈኑ ለነ"ነጻነትን የሚሰብክልንን ይላክልን የቅዱሳን አምላክ

ሃይማኖትሰ ጥይቅት ይእቲ ለዘይሴፈዋ፣ ዕብ፣11፡1 እምነትምሃይማኖት ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥልን ነው በተነገረን በተማርነው የሃይማኖት ትምህርት ጸንተን በእርሱ አምነን ለእርሱ ማደሪያ እንሁን   የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንኳን ለምኩራብ ሦስተኛው ሳምት ዓቢይ ፆም አደረሳችሁ ።    ምኩራብ ማለት የጸሎት ቤት ፣ቤተ ክርስቲያን፣በግሪክኛ ኤክሊሲያ ይባላል በዚህ ቦታ የኃጢአት ማስተስረያ መሷዕት የሚቀርብበት እግዚአብሔር ማደሪያ ቸርነቱን ምህረቱን ይቅርታውን አምነው ለሚጸልዩ የሚሰጥበት የሚያገኙበት የእዚአብሔር ማደሪያ ቅዱስ የተለየ ቦታ ነው ዮሐ፣2፡13 ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ትሰመይ ወኢትረስዩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ ወይቤሎሙ ለእለ ይሠይጡ ርግበ አሰስሉ ወአውጽኡ ዘንተ እምዝየ የአባቴን ቤትየንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው የጸሎት ቤት ማለት ከእግዚአብሔር መገናኘት ሲሆን በኅብረት፣ምስጋና ልምና ስግደት የምናቀርብበት ነው ፦ኅብረት በአንድነት አንድ ሆነን ሲሆን በመለያየት በመከፋፈል መነገጃ ሆናለች ፦ምስጋና እግዚአብሔርን ሳይሆን ባለስልጣንን  ተዋቂ ሰዎችን ሃብታሞችንማወደሻ ሆናለች ፦ልመና ለሀገር ለሕዝብ ሳይሆን ለስልጣን ለገንዘብ የሚለመንበት ሆነ   ፦ስግደት ለእግዚአብሔር ሁሉን ለፈጠረ ሳይሆን ለምድራዊ ስልጣን ላለው በማድረጋችን ምክንያት "ወገብረ ጥብጣቤ"የመግረፊያ ጅራፍ አዘጋጀልን  እውነተኞቹን እግዚአብሔርከመከራው ያድናቸዋልኃጥአን ግን ጽኑ ፍዳ እንዲቀበሉ የቁርጽ ቀን እየቀረበች ነው "ወአንትሙሰ አኀዊነ ተዘከሩ ቃለ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ወንድሞቻችን እናንተ ግን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራችሁን አስቡ ከልቡናችን ከእግዚአብሔር ማደሪያ አሶግደን መንግሥቱን ለመውረስ እንዘጋጅ የእግዚአብሔር ጸጋ ይብዛላችሁ በረከቱን ያሳድርብን ትንሣኤውን ይግለጽልን

#ዘወረደ - ቀዳሚ ሳምንት ................... ጾም ሲመጣ በቀዳሚነት አጋንንት ይቃጠላሉ። ነፍስ ትጠነክራለች። (ዘወረደ)፤ የአቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት # ዘወረደ » ማለት « የወረደ»
#ዘወረደ - ቀዳሚ ሳምንት ................... ጾም ሲመጣ በቀዳሚነት አጋንንት ይቃጠላሉ። ነፍስ ትጠነክራለች። (ዘወረደ)፤ የአቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት # ዘወረደ » ማለት « የወረደ» ማለት ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣ የሚታወስበት፣ የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አንደኛው ሳምንት ነው፡፡ ዮሐ.3-13፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በገባዉ ቃልኪዳን መሰረት “ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ ” እንዳለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ የጠፋዉን አዳም ፍለጋ ከአባቱ እሪና ሳይጎድል ሳይለይ ከሰማይ መዉረዱን የምናዘክርበት በዓል ነዉ። ይህ ጾም የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም “ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅየ አድንኃለሁ” ብሎ ለአዳም ቃል ገባለት ፡፡ ዘፍ. ፫ ፥ ፲፭ ይህ ኪዳነ አዳም ይባላል ፡፡ የቃል ኪዳን ሁሉ መሠረት ነው ፡፡ ሁለቱን ኪዳናት (ብሉይ ወሐዲስ) በፅኑዕ ተስፋ ያስተሳሰረ የረጅም ዘመናት የድኅነት ሰንሰለት ነው ፡፡ ዘወረደ እርቀ አዳም ፤ ተስፋ አበው ፤ ትንቢተ ነቢያት ፤ ሱባኤ ካህናት መፈፀሙ ፤ ኪዳነ አዳም መሲህ መወለዱ የሚነገርበት የፍቅር አዋጅ ነው፡፡ ጾሙን የሰላም የፍቅር በረከት  የምናገኝበት ያድርግልን አሜን #መልካም_ጾም_ይሁንልን

*‹‹እርሷንስ አልክድም›› ስላው በደንጊያ ቀጥቅጦ ገደለው፡፡ መላእክተ ጽልመት የሟቹን ነፍስ ሊወስዱ ሲሉ መላእክተ ብርሃንም አብረው ቀረቡ፡፡ እመቤታችንም ጌታችንን ‹‹ልጄ ይህችን ነፍስ ማርልኝ?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ከልብኑ ይትመሐር እምየ፤ እናቴ፣ ውሻ ይማራልን?›› አላት፡፡ እመቤታችንም፡- ‹‹‹ስምሽን የጠራውን፣ መታሰቢያሽን ያደረገውን እምርልሻለሁ› ያልኸው ቃል ይታበላልን?›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹ምሬልሻለሁ›› አላት፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ‹‹ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› ባለው መሠረት ከቅዱሳን ጋር ያደረጋቸው ቃል ኪዳኖች ብዙዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ከላይ በተአምራቱ እንደተመለከትነው አንዱ ለእመቤታችን የሰጠው የአማላጅነት ኪዳን ነው፡፡ ማማለድ ማለት ስለሌላው መጸለይ፣ መለመን፣ የደረሰውን ችግር እንዲወገድ ማድረግ፣ ማስማር (ይቅርታ ማሰጠት) ማለት ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ከእግዚአብሔር በታች ከቅዱሳን ዅሉ በላይ ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእግዚአብሔር በተሰጣት የማማለድ ሥልጣን ‹‹ሰአሊ ለነ ቅድስት፤ ቅድስት ሆይ ለምኚልን›› እያሉ ለሚለምኗት ዅሉ ከእግዚአብሔር እያማለደችና እየለመነች ምሕረትን እንደምታሰጥ ቀናውንና የተመሰገነውን ሃይማኖት የምንከተል ምእመናን ዅሉ እናምናለን፡፡ ምክንያቱም ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር እናትና አገልጋይ እንደመኾኗ ከዅሉም ቅዱሳን በበለጠ ለእግዚአብሔር ቅርብ ናትና፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድም ኾነ በሰው ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘት ወይም ቅርብ መኾን ደግሞ አንድን ጉዳይ በቀላሉ ለማስፈጸም ይጠቅማል፡፡ ለምሳሌ፡- መልአኩ ቅዱስ ገብርአል በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም ባለሟል በመኾኑ የድኅነትን ምሥጢር አብሣሪ ኾኗል /ሉቃ. ፩፥፲፱-፳፮/፡፡ አስቴር የንጉሡ አርጤክስስ ሚስት በመኾኗ በወገኖቿ አይሁድ የታወጀውን የሞት አዋጅ አስለውጣለች /መጽሐፈ አስቴር ፫፥፲/፡፡ ነቢዩ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት ባለሟል በመኾኑ ‹‹ይህንን ኀጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን እኔን ከጻፍከው መጽሐፍህ እባክህ ደምስሰኝ?›› በማለት ለእስራኤላውያን ምሕረትን አሰጥቷል /ዘፀ.፴፪፥፲፬/፡፡ ስለዚህ የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትም እንደ ፀሐይ የበራ ሐቅ ነው፡፡ ይህንን እውነት ቅዱስ ያሬድ ሲመሰክር፡- ‹‹ወታስተሠርዪ ኀጢአተ ሕዝብኪ ተበውሀ ለኪ እምአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወከመ ትኩኒ ተንከተመ ለውሉደ ሰብእ ለሕይወት ዘለዓለም፤ ለሕዝብሽ፣ ለወገኖችሽ የኃጢአት ይቅርታን ታሰጪ ዘንድ፤ ዘለዓለማዊ ሕይወትንም ለሚወርሱ ዅሉ መሸጋገሪያ ድልድይ ትኾኚ ዘንድ ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ሥልጣን አግኝተሻል›› በማለት አመስግኗታል /አንቀጸ ብርሃን/፡፡ #አባ ጽጌ ድንግልም በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው፡- ‹‹ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ፤ የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት፣ መርገም (ኀጢአት) ባጠፋን ነበር›› ብለዋል፡፡ #አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው፡– ‹‹ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ፡፡ መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ፡፡ ለጻድቃን ያይደለ ለኀጥአን አሳስቢ፡፡ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሶስቢ፤›› ሲሉ ይማጸኗታል /ቅዳሴ ማርያም ቍ.፻፷፭-፻፸፩/፡፡ ስለዚህም ዘወትር በሥርዓተ ቅደሴአችን፡- ‹‹ድኅነትን የምንለምንሽ ክብርን የተመላሽ ቅድስት ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ ዅል ጊዜ ድንግል የምትኾኚ አምላክን የወለድነሽ የክርስቶስ እናት ሆይ ኀጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ወዳጅሽ ወደ ላይ ጸሎታችንን አሰርጊልን፡፡ በእውነት የጽድቅ ብርሃን የሚሆን አምላካችንን ክርስቶስን የወለድሽልን ንጽሕት ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ ንጽሕት ድንግል ሆይ ለነፍሳችን ይቅርታን ያደርግ ዘንድ፤ ኀጢአታችንንም ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ጌታችን ለምኚልን። በእውነት ለሰው ወገን አማላጅ የምትሆኝ አምላክን የወለድሽ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ የኀጢአታችንን ሥርየት ይሰጠን ዘንድ በልጅሽ በክርስቶስ ፊት ለምኝልን፡፡ በእውነት ንግሥት የምትኾኚ ንጽሕት ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ አምላካችን አማኑኤልን የወለድሽልን ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እውነተኛ አስታራቂ ሆነሽ ታስቢን ዘንድ እንለምንሻለን ። ለነፍሳችን ይቅርታን ያደርግልን ዘንድ ኀጢአታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ፤›› በማለት እመቤታችንን እንማጸናታለን፡፡ በአጠቃላይ ‹‹ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ፤ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ፤›› በማለት በነቢዩ ቅዱስ ዳዊት አድሮ ራሱ እግዚአብሔር ከመረጣቸው አበው ነቢያት፣ ጻድቃን፣ ቅዱሳንና ሰማዕታት ጋር ቃል ኪዳን እንደ ገባ፣ እንደሚገባ ተናግሯል /መዝ.፹፰፥፫/፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹እንግዲህ እርሱ ራሱ ካጸደቀ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሰዎች የሚቃወማቸው ማን ነው?›› በማለት እግዚአብሔር ሰዎችን እንደሚጠራ፣ እንደሚያከብር፣ እንደሚቀድስና ቃል ኪዳን እንደሚሰጥ ነግሮናል /ሮሜ.፰፥፴፫/፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው ነገር ድንቅ ነው፤›› /መዝ.፹፮፥፫/ በማለት እንደተናገረው እግዚአብሔር አምላካችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የገባው ቃል ኪዳን ከቅዱሳን ቃል ኪዳን ዅሉ ልዩ ነው፡፡ ይህም እንደምን ነው ቢሉ፡- ➜ለአምላክ እናትነት የተመረጠች ልዩ እናት በመኾኗ፤ ➜አምላክ ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ከእርሷ በመወለዱ፤ ➜ከመለለዷ በፊት፣ በወለደች ጊዜ፣ ከወለደች በኋላ ምን ጊዜም ድንግል በመኾኗ፤ ➜በሁለቱም ወገን (በአሳብም በገቢርም) ድንግል በመኾኗ፤ ➜አማላጅነቷ የወዳጅነት ሳይኾን የእናትነት በመኾኑ፤ ➜ዓለም ይድን ዘንድ የድኅነት ምክንያት አድርጎ አምላክ ስለመረጣት ነው፡፡ ይህ ቃል ኪዳን የሚያገለግለው ለማን ነው? የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የሚያገለግለው በሃይማኖታቸው ጸንተው በመልካም በቅድስና ሥራ በመትጋት ለሚደከሙ ለኃጥአን ነው:: አባታችን ቅዱስ ሕርያቆስም ይህንን በቅዳሴ ማርያም “አዘክሪ ድንግል ለኃጥአን ወአኮ ለጻድቃን:- ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ” በማለት ይገልጸዋል:: አባ ጽጌ ድንግልም በማኅሌተ ጽጌው “ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ:- የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት ባጠፋን ነበር” በማለት የእመቤታችንን ቃል ኪዳን አማናዊነት ይገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የእመቤታችን የምህረት ቃል ኪዳን አለና በእርሱ ድኅነትን እናገኛለን በማለት በጎ ምግባርን፣ ትሩፋትን ከመሥራት ቸል ማለት አይገባም፡፡ እርሷ የሚላችሁን አድርጉ እንዳለች ልጅዋ የሚለንን ለማድረግና ባልቻልነው ነገር ደግሞ የእርሷን አማላጅነት እንጠይቃለን፡፡ ስለዚህ ብዙ ከንቱ አሳቦችን ትተን፣ እንደበላዔ ሰብእ በቃል ኪዳኗ ተጠቅመን፣ ንስሐ ገብተን፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን፣ የስሙ ቀዳሽ፣ የመንግሥቱ ወራሽ ለመኾን ያብቃን፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን አማላጅነት፣ የቅዱሳን ተራዳዒነት አይለየን፡፡

#ኪዳነሞሕረት!! ኪዳነ ምህረት የድኅነት ምክንያት ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የጥፋት እሳት ባጠፋን ነበር። #ኪዳን ምንድነው ! እግዚአብሔር አምላክ ዓለሙን ከፈጠረ ጀምሮ ፍጥረታቱን ሁሉ በቸርነቱ በርኅራሄው ይጠብቃል፤ ይመግባል፡፡ የሰው ልጆች ህግን በመተላለፍ፣ ኃጢአትን ሰርተው እግዚአብሔርን ባሳዘኑ ጊዜ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ዝለው ከእርሱ ከልዑል እግዚአብሔር በረከት ጥበቃ እንዳይርቁ ስለባለሟሎቹ ቅዱሳኑ ብሎ በቃል ኪዳኑ ይጠብቃል። እግዚአብሔር ከከባለሟሎቹ ጋር የሚያደርገው ቃል ኪዳን የቸርነቱን ብዛት ከሚገልጥባቸው መንገዶች አንዱ የሆነ ፍኖተ እግዚአብሔር ነው። ‹‹ኪዳን›› የሚለው ቃል ‹‹ተካየደ – ተዋዋለ፤ ቃል ኪዳን ተጋባ፤ ተማማለ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲኾን፣ ትርጕሙም ኪዳን፣ ውል፣ መሐላ፣ ቃል ኪዳን፣ የውል ቃል ማለት ነው /ዘዳ.፳፱፥፩፤ ኤር.፴፩፥፴፩-፴፫፤ መዝ.፹፰፥፫/፡፡ በሌላ በኩል ኪዳን የጸሎት ስም ሲኾን፣ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ፣ ከማረጉ በፊት ለሐዋርያት ያስተማራቸው ጸሎት ኪዳን ይባላል፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን (ውል፣ ስምምነት) የተቀበለችበት ዕለት (የክብረ በዓል ስም) ደግሞ ኪዳነ ምሕረት ይባላል፡፡ ምድርንና ሥጋ ለባሹን በንፍር ውኃ ዳግመኛ ላያጠፋ ለአባታችን ለኖኅ ቃል ኪዳን ገብቶለታል (ዘፍ.፱፡፩-፲):: ለቀደሙት አባቶችም ለእነ አብርሃም ለቅዱስ ዳዊት ቃል ኪዳን ገብቷል፤ መሃላንም አድርጓል: (ዘፍ.፳፪፡፲፰ ዘፍ.፳፮፡፬ መዝ.፹፱፡፫):: ይህም ቃል ኪዳን እንደ ተርታ ውል ያለ ሳይሆን የፀና የምህረት ቃል ኪዳን ነው:: በብሉይ ኪዳን የተፈጸሙት ኪዳናት በዓመተ ፍዳ የተፈጸሙ ስለሆኑ የመከራውን ጊዜ ያወሳሉ። በሐዲስ ኪዳን የተፈጸሙት ኪዳናት ደግሞ ዘመነ ምህረትን የሚያውጁና ጸጋቸውም የበዛ አማናዊ ኪዳናት ናቸው። በአንጻሩ ከቅዱሳኑ ጋር ያደረገው ኪዳን በአምላክ ሰው መሆን ፍጻሜን አግኝቷል። የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋት የተነሳ በቅድስና ክብር አክብሮ ለገድላቸው እንዲሁም በተጋድሎ ላሳለፉበት ቦታ ለረገጡት አፈር ሁሉ በረከታቸው ተርፎ ዛሬ እኛ ምእመናን በየመካናቱ እምነቱን በመተሻሸት በመጠጣት ከቅዱሳኑ በረከት እንሳተፋለንል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ምህረት የባሕርይ ገንዘቡ ነውና ለሚወዱትም ትእዛዙን ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን እንደሚያደርግ በመጽሐፍ እንደተጻፈ ከቅዱሳኑ ጋር ውልን የሚያደርገው እኛን የሰው ልጆችን በቅዱሳኑ በጎ ሥራ ለመጥቀም ፈልጎ ነው (ዘጸ ፳:፪-፮):: “እንዲህም ይሆናል፤ ይህችን ፍርድ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳንና ምሕረት ለአንተ ይጠብቅልሃል” ዘዳ ፯:፲፪ በየዓመቱ የካቲት ፲፮ ቀን የምናከብረው ይህ በዓል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጎልጎታ በልጇ በመቃብር ላይ ኾና ‹‹ኦ ወልድየ ወፍቁርየ እስእለከ በእንተ ዘተሰባእከ እምኔየ ወበማኅፀንየ ዘጾረተከ፦ ልጄ ወዳጃ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ፣ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው ስለመኾንህ፤ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ስለቻለችህ ማኅፀኔ፤ ከአንተ ጋር ከአገር ወደ አገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ›› እያለች ስትጸልይ ጌታ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደእርሷ መጥቶ ‹‹ሰላም ለኪ ማርያም እምየ፤ እናቴ ማርያም ሰላም ላንቺ ይኹን! እንዳደርግልሽ የምትለምኚኝ ምንድን ነው?›› አላት፡፡ እመቤታችንም በስሟ የሚማጸኑትንና መታሰቢያዋን የሚያደርጉትን፣ ለችግረኛ የሚራሩትን፣ ቤተ ክርስቲያን የሚያንጹትን፤ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጡትን፤ ለእመቤታችንና ለሃይማኖታቸው ካላቸው ፍቅር የተነሣ ልጆቻቸውን በስሟ የሰየሙትን ዅሉ እንዲምርላትና ከሞተ ነፍስ እንዲያድንላት ጠየቀችው፡፡ ጌታችንም ‹‹ይህን ዅሉ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ›› ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላት ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በቅዳሴው ‹‹… ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማፅነናል፤ ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት፡፡ አንተ ‹መታሰቢያሽን ያደረገ፣ ስምሽንም የጠራ፣ የዘለዓለም ድኅነትን ይድናል› ብለሃታልና …፤›› በማለት የሚማጸነው፡፡ በተአምረ ማርያም መጽሐፍ እንደተመዘገበው በዚህ ዕለት የሚታሰቡ ሁለት ተአምራት አሉ፤ ከእነዚህም አንደኛው የስምዖን ታሪክ ነው፡፡ ስምዖን የሚባል እንግዳ ተቀባይ ደግ ሰው ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያፍርምና ከዕለታት አንድ ቀን በእንግድነት ከቤቱ ገብቶ ‹‹ልጅህን አርደህ ካላበላኸኝ ሌላ ምግብ አልበላም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ስምዖን ሲያወጣና ሲያወርድ ቆየና ‹‹አብርሃም ልጁን ሰውቶ ነው የእግዚአብሔር ሰው የተባለው›› በማለት፣ ‹‹የእግዚአብሔርን እንግዳ›› ላለማሳዘን ሲል ልጁን አርዶ አቀረበለት፡፡ እንግዳ መሰሉ ሰይጣንም ሥጋውን ቅመስልኝ ብሎ ግድ አለው፡፡ ስምዖንም (በላዔ ሰብእ) አርዶ ያዘጋጀውን የልጁን ሥጋ በቀምሰ ጊዜ ሰይጣን ስላደረበት (ስለተዋሐደው) ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ቤተሰቦቹን፣ ጎረቤቶቹንና መንገደኛውን ዅሉ ይበላ ጀመር፡፡ በአጠቃላይ ፸፰ ሰዎችን ከበላ በኋላ አንድ በቍስል የተመታ ሰው አገኘና ሊበላው ሲል ‹‹ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ በሥላሴ፣ በቅዱስ ሚካኤል፣ በቅዱስ ገብርኤል ስም ለመነው፤ እርሱም ዝም አለው፡፡ በመጨረሻም ‹‹በድንግል ማርያም ስም›› አለው፡፡ ስምዖን የእመቤታችንን ስም በሰማ ጊዜም ወደ ልቡናው ተመልሶ ‹‹እስኪ ቃሉን ድገመው›› አለው፤ በሽተኛውም መልሶ ‹‹ስለ ድንግል ማርያም ውኃ አጠጣኝ›› ብሎ ለመነው፡፡ ያን ጊዜ ‹‹ይህችስ እንደምታስምር በልጅነቴ ሰምቻለሁ›› ብሎ ጥቂት ውኃ ሰጠው፤ ውኃው ጕሮሮውን እንኳን ሳያርስለት ‹‹ጨረስህብኝ›› ብሎ ነጥቆት ሔደ፡፡ በሌላ ቦታም አንድ ገበሬ አግኝቶ ሊበላ ሲል ገበሬው ‹‹በላዔ ሰብ የምትባል አንተ ነህ?›› ባለው ጊዜ ‹‹ለካስ አመሌን ሰው ዅሉ አውቆብኛል›› ብሎ ዋሻ ገብቶ በመጸጸት በዚያው ሞተ፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ጽልመት መጥተው ሲወስዷት እመቤታችን ‹‹ልጄ በማይታበል ቃልህ ይህችን ነፍስ ማርልኝ?›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹ሰባ ስምንት ነፍስ ያጠፋ፣ ፈጣሪውን የካደ ሰው ይማራልን?›› አላት፡፡ እመቤታችንም ‹‹በስሜ የተጠማውን ውኃ አጥጥቶ የለምን?›› ብላ ስምዖንን (በላዔ ሰብእን) አስምራዋለች፡፡ ነፍሱንም መላእክተ ብርሃን መጥተው ወደ ገነት አስገብተዋታል፡፡ ሁለተኛው ተአምር ደግሞ ከብሮ ከኖረ በኋላ ለድህነት በተጋለጠ አንድ ምእመን ላይ የተደረገ ነው፤ ከክርስቲያን ወገን የኾነ ሀብት አግኝቶ ያጣ አንድ ሰው ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ‹‹ከብሬ በኖርኹበት አገር ተዋርጄ አልኖርም›› ብሎ ጓዙን ጠቅልሎ ከአገሩ ወጥቶ ሲሔድ ሰይጣን ያዘነ ሰው መስሎ ደንጊያውን በምትሐት ወርቅ አስመስሎ ‹‹ሥላሴን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትንን፣ መላእክትን ካድልኝና ይህን ወርቅ እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ ዅሉንም ካደለትና ወርቁን ተቀብሎ ዞርሲል ‹‹ምእመናን የሚመኩባት ድንግል ማርያም ‹የአምላክ እናት አይደለችም› ብለህ ካድልኝ›› አለው፡፡

ለተከበራችሁ የፍኖተ ጽድቅ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ ማህበራችን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የማህበራት ምዝገባ ክፍል ከካቲት 1 ቀን ጀምሮ እጋዊ እው
+1
ለተከበራችሁ የፍኖተ ጽድቅ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ ማህበራችን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የማህበራት ምዝገባ ክፍል ከካቲት 1 ቀን ጀምሮ እጋዊ እውቅና አግኝቷል እንኳን ደስ አላችሁ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመንገድ ሁኔታ ሰላም ከሆነ የመስቀለ እየሱስን በዓል መስቀሉ ባለበት በተናፋቂዋ እና በመስቀለኛው ቦታ በግሸን ማርያም እናከብራለን መመዝገቢያ ማረፊያ እና መስተንግዶን ጨምሮ 3500 ብር ብቻ ነው ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን ደውሉልን ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ።

ዛሬ ሕጻን ተወለደልን ታላቁ ሐዋርያ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱበት ቀን አደረሳችሁ ታላቅ የበረከት በዓል ነው በረከቱን ያድላችሁ ለጌታችን በዓለ ልደት ዋዜማ አደረሳችሁ   በዘመነ ኖላዊ ክርስቶስ በግርግም በተወለደበት ወቅት እርሱ በመልካም እረኛ ስንጠበቅ ታመን ሲፈውሰን ወድቀን ሲያነሳን ከስደት ሲመልሰን ከሞት ሲያነስ የእርሱን ሥራ እንዳይቋረጥ ከጸጋዘአብና ከእግዚእሐርያ እንዲወለድ አድርጎ ሰጠን በቸርነቱ አምላካችን ለሰው ልጅ ያለው ፍቅር በዚህ ይታወቃል ደገኛ እረኛ ይፍጠርልን ሰሎሞን በሕጻንነቱ አስተዋይ ልብ ሰጠው አባታችንም በሕጻንነታቸው በእናታቸው እቅፍ ላይ ሆነው የእግዚእሐርያን ለቅሶ አልቅሰው እቤት ካለው ዱቄት አበርክተው ወደ ደስታ ሰላም ቀይረው ከችግር ከረሃብ አውጥተዋቸዋል እኛንም ትኒሹን አበርክተው የሕጻንነት አስተሳሰብ አጎልምሰው ማስተዋሉን ይስጡን አምላከ ተክለሃይማኖት ከዘመኑ መከራ ሥጋ ወነፍስ ይሰውረን ይሰውራችሁ

ዓመታዊውን የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ቁልቢ ተገኝታችሁ ማክበር ለምትፈልጉ ምዕመናን ፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ የጉዞ ማህበር በልዩ ባስ እና በኖርማል ባስ የተለመደውን መስተንግዶ አጠናቆ ምዝገባ ጀምሯል ።መነሻ ታህሳስ 17 መመለሻ በ 20 ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮቹ ይደውሉ