en
Feedback
የኢትዮጵያ ክንድ

የኢትዮጵያ ክንድ

Open in Telegram

መከላከያ ሠራዊታችንንና ሌሎች የፀጥታ ጉዳዮችን የተመለከቱ ፈጣንና እውነተኛ መረጃዎች!

Show more
2 787
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
👉 ከ300 በላይ የአሸባሪው አልሸባብ ታጣቂዎች ተደመሰሱ‼️ ከ300 በላይ የአሸባሪው አልሸባብ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላት መቁሰላቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። በሶማሊያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ኃይል ለመቀየር ተልዕኮ ወደ ሚፈፀምበት ቦታ በተንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ ጠላት ቀድሞ ባገኘው መረጃ መሠረት ደፈጣ ይዞ ሠራዊቱ ላይ ጥቃት ለመሠንዘር የሞከረው አልሸባብ ባላሠበው መልኩ ክፉኛ መመታቱ ተገልጿል። በተሳሳተ ስሌት የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ቅይይር ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረው የአልሸባብ ኃይል ከ300 በላይ ታጣቂዎቹ ሲገደሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱም ቆስለዋል። የመከላከያ ሠራዊቱን ምት መቋቋም ያልቻለው አልሸባብ የሞቱ ታጣቂዎቹን አስክሬን እያንጠባጠበ ቁስለኞቹን በመያዝ ወደኋላ ለመፈርጠጥ ተገዷል። የኢትዮጵያ ሠራዊት የአሸባሪውን አልሸባብ ደፈጣ እያስወገደና በየመንገዱ የጠመዱትን ፈንጂና መሠናክሉን እያስወገደ ከተልዕኮው ቦታ ሁዱር መድረስ መቻሉን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ አመላክቷል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ለመከላከያ ሠራዊት ምግብ እና ውሃ በማቅረብ ደስታቸውን እና ምስጋናቸውን የገለፁ ሲሆን በእልልታ እና በሞራል ያላቸውን ድጋፍም አሳይተዋል። #የኢትዮጵያ_ክንድ

👉 ሠራዊቱ ዛሬም የሕዝብ አገልጋይ ነው‼️ #የኢትዮጵያ_ክንድ

👉 መርማሪ ቦርዱ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ጋር ተወያየ‼️ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አደረገ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርዱ በሸዋሮቢት፣ በጎንደር፣ በኮምቦልቻ እና በባህር ዳር በወንጀል ተጠርጥረው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ በህግ ጥላ ስር ያዋሉትን ተጠርጣሪዎች በጎበኘበት ወቅት ተጠርጣሪዎቹ ባነሷቸው ሀሳቦች ዙርያ ቦርዱ ምክረ ሀሳብ ለእዙ በማቅረብ ውይይት አድርገዋል። #የኢትዮጵያ_ክንድ

photo content
+3

👉 ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ መግለጫ‼️ ♦️ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ የማገቻ ካምፕ የለውም‼️ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ እስካሁን ያዘጋጃቸው የማቆያ ቦታዎች 5 ብቻ ናቸው። እነርሱም በኮምቦልቻ፣ ጎንደር፣ ባሕርዳር፣ ሸዋ ሮቢት እና አዋሽ አርባ የሚገኙ ናቸው። በእነዚህ ቦታዎች የሚገኙ ተጠርጣሪዎች 764 ብቻ ናቸው። ተጠርጣሪዎቹ ያሉበት ሁኔታ በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ምርመራ ቦርድ እና በኢሰመኮ ተጎብኝተዋል። ከዚህ ውጭ የተለያዩ ፎቶዎችን እየለጠፉ የሕጻናትና የዐዋቂዎች የማገቻ ካምፖች ናቸው የሚባሉት ቦታዎች ፈጽሞ እውነት ያልሆኑ የፈጠራ ዜናዎች ናቸው። በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ ምክንያት ሰዎችን ከዕዙ ዕውቅና ውጭ ማሠርና ማገት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል ነው። ስለዚህም በመንግሥታዊ አካል ሊፈጸም አይችልም። መንግሥትም ይህ ዓይነት ፍላጎት የለውም ሲል የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ አስታውቋል። በዚህ እኩይ ተግባር የተሠማሩ አካላትም ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ዕዙ በጽኑ አስጠንቅቋል። የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ መስከረም 1 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ #የኢትዮጵያ_ክንድ

👉 ጀግኖቻችን እንኳን አደረሳችሁ‼️💪💪 ስለ እኛ ሠላም ስትሉ፤ ከቤተሰባችሁ ተነጥላችሁና ኑሯችሁን ትታችሁ፤ በዱር፣ በገደሉ፣ በጥሻ፣ በሸንተረሩ...ለምትዋደቁልን ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን አባላት በሙሉ እንኳን ለ2016 ዓ.ም አደረሳችሁ‼️ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ‼️ #የኢትዮጵያ_ክንድ

photo content
+3

👉 እንኳን ደስ አላችሁ‼️ "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበሥር በታላቅ ደስታ ነው። ኢትዮጵያዊያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በሥራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል። ብዙ ፈተና ነበረው፤ ወደኋላ እንድንመለስ ብዙ ተጎትተን ነበር። በውስጥ ፈተና በውጭ ጫና ነበረብን። ከፈጣሪ ጋር የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚህ ደርሰናል። ነገር ግን የዳገቱ ጫፍ ላይ ደረስን እንጂ ዳገቱን ወጥተን አልጨረስነውም። በቀጣዩ ጊዜ ያቀድነውን አጠናቅቀን ፈጣሪን እንደምናመሰግን እምነቴ ነው። ለግድቡ የምናደርገውን ማናቸውንም ድጋፍ እስከ ፍጻሜው እንድንቀጥል በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ።" ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ

photo content
+1

👉 ሠራዊቱ ተዋጊ ብቻ ሳይሆን፣ አምራች ኃይል መሆኑንም እያረጋገጠ ነው‼️--ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ሠራዊቱ የሀገሩን ሉዓላዊነትን እና የህዝብን ደህንነት ከማረጋገጥ ተልዕኮ ጎን ለጎን ራሱን በግብርና ልማት ስራዎች ተሳታፊ በማድረግ ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንደሚችል በዕዙ የተጀመሩ የግብርና ስራዎች ማሳያ ናቸው ሲሉ የዐዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናግረዋል። ጷጉሜ 4 የአምራችነት ቀንን ምክንያት በማድረግ በሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የተመራ የዕዙ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ መኮንኖች በጠቅላይ መምሪያው በመልማት ላይ የሚገኙ የግብርና ልማት ስራዎችን ጎብኝቷል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት፤ የመከላከያ ሠራዊት በግብርና ልማት ስራዎች ውጤታማ ከመሆንም ባሻገር የፍሬው ተቋዳሽ እየሆነ መምጣቱን የተግባር ሥራዎቹ ከምስክር በላይ ሆነው አረጋግጠውልናል ፤ሠራዊት አምራችና አልሚ አይደለም የሚለውን አባባልም ያስቀረ ነውም ብለዋል። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ግብርና ልማት ክፍል ኃላፊ ኮሎኔል አለም ወልጫፎ በበኩላቸው፤ በዕዙ ቅጥር ግቢ ውስጥ ያለምንም አገልግሎት ለበርካታ ዓመታት ተራቁቶ የኖረን መሬትን ለግብርና ልማት በማመቻቸት የተለያዩ አዝዕርቶችን በመዝራት ተስፋ ሰጪ ጅምሮች መታየታቸውን ገልፀዋል። "ለዓመታት ካለምንም ጥቅም ሲባክን የነበረን መሬት በግብርና ልማቶች እንዲሸፈን በማድረግ የተለያዩ የእህል ዘሮች እያለማን ስንገኝ 29 ሄክታር በበቆሎ 5 ሄክታር በዳጉሳና በጤፍ ዘርፍ በአጠቃላይ 34 ሄክታር መሬት በዘር እንዲሸፈን አድርገናል። በቀጣይነትም ተጨማሪ መሬቶችን በመጠቀም ሌሎች አዝዕርቶችን ለማልማት ተዘጋጅተናል" ሲሉ የግብርና ባለሙያው ምክትል መቶ አለቃ መስፍን ተናግረዋል። FDRE Defense Force #የኢትዮጵያ_ክንድ

👉 ታላቅ የምስራች ከጉባ ተራራዎች እምብርት‼️👇👇 የታላቁ የህዳሴ ግድብ 4ኛው የውሐ ሙሌት በስኬት ተጠናቅቋል። ውሐው ሞልቶ በመሀከለኛው የግድቡ ኮሪደር አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል። እንኳን ደስ ያለን፤ እንኳን ደስ ያላችሁ‼ #የኢትዮጵያ_ክንድ

photo content
+2

👉 "ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿ በሠላም እንዲኖሩ ጀግኖች ልጆቿ የከፈሉትን ተጋድሎና መስዕዋትነት መቼም ቢሆን ታሪክ አይረሳውም‼️"-- ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ የበጎነትን ቀንን አስመልክተው ለሠራዊቱ ቤተሰብ የበዓል መዋያ ስጦታ አበርክተዋል። ሠራዊታችን ሀገርን ከነ ሙሉ ክብሯ ለማስቀጠል በየትኛውም ቦታ ማንኛውንም ተፅዕኖ ተቋቁመው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍሰው ሀገርን በክብር እንድትቀጥል ሠንደቅ ዓላማዋ ከፍ ብሎ እንዲታይ በማድረጋቸው ታላቅ ክብር ሊሠጣቸው ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያዊያን ከቀደመው ዘመን ጀምሮ ሀገር እንድትቀጥል መስዕዋትነት ከፍለው ማለፋቸው መቼም ቢሆን የማይዘነጋ ታላቅ ታሪክ ነው ያሉት አዛዡ፤ የእነርሱን አደራ ተቀብለን ኢትዮጵያን ማሻገር የእኛ ድርሻ በመሆኑ ሀገርን በፅናት ልንጠብቃት ይገባል ብለዋል። ድጋፍ ከተደረገላቸው የሠራዊቱ ቤተሰቦች መካከል ወይዘሮ እታለም ቢራራ እና ወይዘሮ ራሄል ብርሃኑ በሰጡት ተመሳሳይ አስተያየት፤ "አዲሱን አመት አስመልክቶ ለበዓል መዋያ የአስቤዛ፣ የመማሪያ ቁሳቁሶችንና የሰንጋ ስጦታ ድጋፍ አድርጋችሁ ቤተሰባዊ የሆነ ክብርና ፍቅር በተግባር ስላሳያችሁን የከበረ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፤ አዲሱ ዓመት የሠላምና የደሥታ ይሁንላችሁ" ብለዋል። FDRE Defense Force #የኢትዮጵያ_ክንድ

photo content
+4

👉 አዲሱ ዓመት አስተማማኝ ሰላም ሰፍኖ ልማት ላይ ትኩረት የሚደረግበት ይሆናል‼️--ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ለ2016 አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ መጪው አዲስ ዓመት ከግጭትና ብጥብጥ በመውጣት አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት ሰፍኖ ሙሉ ትኩረታችንን ልማትና እድገት ላይ እንደምናደርግ ያለኝን ተስፋ ለመግለፅ እወዳለሁ ብለዋል- በመልዕክታቸው። የጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ብርሃኑ ጁላ ሙሉ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ “በቅድሚያ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ፤ አደረሰን እያልኩ መጪው አዲስ ዓመት ከግጭትና ብጥብጥ በመውጣት አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት ሰፍኖ ሙሉ ትኩረታችንን ልማትና እድገት ላይ እንደምናደርግ ያለኝን ተስፋ ለመግለፅ እወዳለሁ። ሁላችንም ወደምንመኘው የተሟላ ሰላምና መረጋጋት እንሸጋገር ዘንድ ሰራዊታችን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ተልዕኮውን በጽናትና በቁርጠኝነት ሊወጣ መዘጋጀቱን እያረጋገጥኩላችሁ ፖለቲከኞቻችንም በሰለጠነ አግባብ የሰላማዊ ትግል አቅጣጫን በመከተል አገራዊ አንድነትን እንዲሁም ሰላምና እድገትን ለማስፈን የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ቢያበረክቱ መጪው አዲስ ዓመት የአዲስ ብሩህ ተስፋ ዘመን ይሆንልናልና ሁላችንም ለሰላም የሚጠበቅብንን እናበረክት ዘንድ አሳስባለሁ። መከላከያ ኃይላችንን ከውጪ የሚመጣን ጥቃትና የውስጥ የጸጥታ ስጋትን በሚያስቀርና ከመጣም በአስተማማኝና በአጭር ጊዜ መመከት በሚያስችል ቁመና ገንብተነዋል። ከውጪ የሚመጣን ጥቃትና የውስጥ የፀጥታ ስጋትን የሚያስቀርና የሚመክት ሰራዊት ከሌለ፤ የሀገር ቀጣይነት አደጋ ላይ ይወድቃል። ሰላምና መረጋጋትን ማስፈንም አይቻልም፤ ሰላምና መረጋጋት ካልሰፈነ የኢኮኖሚ ግንባታ ዕውን አይሆንም። በመሆኑም ሰራዊት የምንገነባው ሀገርን ለማስቀጠል ሰላምና መረጋጋትን በአስተማማኝ አስፍነን ሀገሪቱ በኢኮኖሚ እንድታድግና ህዝባችን ከድህነት ተላቆ ብልፅግናው አንዲረጋግጥ ለማስቻል ነው፤ ይህንን መሰረት አድርገን ያስቀመጥነውን የሃይል የበላይነቱ የተረጋገጠ ሠራዊት የመገንባት ግባችንን በ2015 ዓ.ም ባቀድነው ልክ አሳክተናል፡፡ ኢትዮጵያ የቀደምት ስልጣኔና ታሪክ ባለቤት የሆነች ገናና፣ አጅግ ሰፊ ግዛት የነበራት ግን ያንን ስልጣኔና ታላቅነት ከማስቀጠል ይልቅ በየዘመኑ በተፈጠሩ ግጭቶች ግዛቶቿ እየቀነሱ ከታላቅነቷ እያሽቆለቅቆለች በመሄድ በድህነትና ኋላ ቀርነት የምትጠቀስ ሆና እኛ ትውልድ ላይ የደረሰች ሀገር ናት። ይህች ሀገር አሁንም በጭቅጭቅና ግጭት ሰላም እንድታጣ በድህነቷና ኋላቀርነቷ እንድትቀጥል፣ ህልውናዋ አደጋ ላይ እንዲወድቅ፣ ህዝብ በሰላም ሰርቶ ሀገሩን እንዳያሳድግና ከድህነት እንዳይላቀቅ ግጭት እየጠመቁ ሀገር የሚበጠብጡ ሀይሎች አሉ። በግጭት ወይም በሀይል ሀገርን ማዳከም እንጂ ማሳደግ እንደማይቻል ከእስካሁኑ ታሪካችን መማር አለብን። ዓለም በሰለጠነችበት በዚህ ዘመን ስልጣንን በጠብመንጃ ለመያዝ መሞከር ኋላ ቀርነት ነው፤ በሰለጠነ መንገድ ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ፤ የፖለቲካ አላማችንን ለህዝብ አቅርበን በህጋዊ መንገድ ስልጣን በመያዝ እንወዳደር፤ ክዚህ ውጪ ያለው መንገድ ዝግ ነው፡፡ የሃይል መንገድን ተከትሎ የኢትዮጵያን ሰራዊት በማሸነፍ ፍላጎትን በሃይል ህዝብ ላይ መጫን አይቻልም፤ ትርፉ ከንቱ መስዋትነትን መክፈልና ህዝብን ሰላም መንሳት ብቻ ነውና ከዚህ የጨለማ መንገድ እንውጣ፡፡ መልካም አዲስ ዓመት!" FDRE Defense Force #የኢትዮጵያ_ክንድ