የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ
Open in Telegram
ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.
Show more447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
❤️የዕለቱ መልዕክት❤️
#የሰላም_ዋጋ_ስንት_ነው?
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉 እንደ ግለሰብ ያለን ሰላም ከሌሎች ጋር ያለንን ሰላም ይወስናል።በራሱ ጉዳይ ሰላም የሌለው ሰው አብሮአችሁ እየሠራ ከኾነ በሰላም መሥራት አትችሉም።በትንሹም በትልቁም ይጋጫችኋል።የውስጥ ብሶቱን እናንተ ላይ ነው የሚወጣባችሁ።እናንተም ሰላም ከሌላችሁ ለሌላው የምትሰጡት ሰላም አይኖራችሁም።ስለዚህ ኹሉም ሰው ከራሱ ጋር ቅድሚያ ሰላም መኾን አለበት።
👉 አኹን ባለው ሐገራዊ ሁኔታ ውስጥ የሰላም መሣሪያ የኾኑ አገልጋዮች ያስፈልጉናል።ኦሮሞ ምን ያህል በአማራና በትግሬ እንደተጎዳ የሚነግረው ሳይኾን የኦሮሞ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ለበደለው ነገር ይቅርታ እንዲጠይቅ፤ የበደሉትንም ይቅር እንዲል መሥራት ያስፈልጋል።አማራውም በድሎኛል ያለውን ብሔር ይቅር እንዲል የበደለውንም ይቅርታ እንዲጠይቅ መሠራት አለበት።ትግሬውም እንዲሁ።
✋ ለመጪው ትውልድ ያሰበ ሥራን መሥራት ካኹኑ ነው።የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሰላም አለመኾን የኹሉም ኢትዮጵያዊ ሰላም አለመኾን ነው።ከዳር ቆመን ያየነው እሳት እኛም ጋ ይመጣል።የሙስሊሞች ሰላም አለመኾን የኹሉም ኢትዮጵያውያን ሰላም አለመኾን ነው።ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ሰላም አጥቶ ሰላም የምታገኝ ኢትዮጵያ አትኖርም።የወንጌላውያንም እንዲሁ ነው።
🪢 የምንኖረው ኢትዮጵያ በምትባል አንዲት ቤት ውስጥ ነው።ስለዚህ በአንድ ቤት ውስጥ እየጨሰ ያለ ከሰል በቤቱ ውስጥ ያለውን ሁሉ አፍኖ ሳይገለው አይቀርም።
#ሳናጣው_ስለሰላም_እንጸልይ ፣ #እናውራ፣ #እንንቃ፣ #እናንቃ።
የሰላም አለቃ ጌታ ኢየሱስ ፍጹሙን ሰላም ይሰጠን አሜንንን።
መዝሙር 122
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ለኢየሩሳሌም(ለኢትዮጵያ) ሰላምን ለምኑ፤ አንተንም ለሚወድዱ ልማት ይሁን።⁷ በኃይልህ ሰላም፥ በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን።⁸ ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም፦ በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ።⁹ ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ።
✍ 07/06/2015 የምሕረት ዓመት
የ"መምህራኑ" ኑፋቄና ድፍረት
የኦርቶዶክስ "መምህራን" በየጊዜው ዐዳዲስ ትርጓሜና ትምህርት ይፈበርካሉ።ወጣቱ ለሚጠይቃቸው ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሽ እንዲሰጡት ሲጠይቃቸው ሦስት ዓይነት የአመላለስ መንገዶችን ይጠቀማሉ።እነዚህም የማምለጫ መንገዶች፦
#1 መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያሉትን ጥቅሶች ከዐውዱ አፋተው፣ ከፈለጉ ቃሉን ሳይቀር ቀይረው እነርሱ እንደሚፈልጉት አድርገው መተርጎም ነው።
ለምሳሌ፦ ሮሜ.8:34 ኢየሱስን በግልጽ አማላጅ መኾኑን ስለሚናገርባቸው "የሚፈርደው" ብለው ቃሉን እስከመለወጥ ድረስ ርቀው ይጓዛሉ።ምን ቃል መቀየር ብቻ ፣ሙሉ መጽሐፍ ቅዱሱን ለራስዋ አስተምህሮ እንዲመቻት አድርጋ እስከመቀየር ደርሳለች።የኹለት ሺ ዓመተ ምሕረት ዕትም እንዲኖራት ያደረገችውም የ1954ቱ ዕትም ከአስተምህሮዋ ጋር አልሄድ ስላላት ጭምር መኾኑን ራስዋ በመቅድሙ ላይ ተናዝዛለች።
ከዐውዳቸው ውጭ ተተርጉመው ዶክትሪን ሳይቀር የተሠራባቸው እልፍ ጥቅሶች ሞልተዋል።ለምሳሌ፦ ስለእንጨቱ መስቀል(ዕጸ መስቀል) የማያወሩ ቢኾኑም መስቀል መስቀል የሚሉ ጥቅሶች በሙሉ ለእንጨቱ መስቀል ማስረጃ ኾነው ይቀርባሉ።ምን ይሄ ብቻ ስለ ምልጃ፣ ስለድነት፣ ስለጽዮን ወዘተ ማስረጃ ተደርገው የሚቀርቡ አብዛኞቹ ጥቅሶች ከዐውዳቸው የተፋቱና በግድ ተጠምዝዘው ሊሉ ያልፈለጉትን እንዲሉ የተገደዱ ናቸው።
#2 መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ጥቅስና ማስረጃ ከታጣላቸው ደግሞ ራሱን መጽሐፍ ቅዱስን ማጣጣል፣ በቂና ብቁ እንዳልኾነ መናገር ነው።
ለምሳሌ፦ መጽሐፍ ቅዱስን ቤተክርስቲያን አስገኘች እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ቤተክርስቲያንን አላስገኘም ብሎ መናገር
ሲፈልጉ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ ኢየሱስ በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ተአምራት አድርጎአል ስለሚል ሌሎች መጻሕፍቶች እንዳሉ ይጠቁማል።ኢየሱስ 30 ዓመት ሙሉ ምን ሲሠራ እንደኖረ ስለማናውቅ እርሱን ለማወቅ "ተአምረ ኢየሱስ" ሚባል መጽሐፍ ያስፈልገናል ይላሉ።ያው ተአምረ ኢየሱስ የኢየሱስ የሰላሣ ዓመታትን ታሪክም ኾነ ተአምራትን የያዘ መጽሐፍ ባይኾንም እንዲህ ከማለት ግን አይመለሱም።
#3 በማነጻጸር ትምህርት መሥራት
ተገቢና ሊነጻጸሩ በሚችሉ ትምህርቶች ንጽጽር ተገቢ ነው።ኾኖም የኦርቶዶክስ "ሊቃውንት" ግን በግልጽ ከተጻፈው ንጽጽራዊ ትምህርት ይልቅ በራሳቸው መንገድ በንጽጽር መጠመድን ሥራ አድርገው ይዘውታል።
በመጽሐፍ ቅዱስ አዳምና ኢየሱስ ብቻ የተነጻጸሩ ቢኾንም "ሊቃውንቱ" ግን ሔዋንንና ማርያምን ያነጻጽራሉ።የያዕቆብ መሰላል ከክርስቶስ ጋር በራሱ በክርስቶስ ትምህርት ቢነጻጸርም እነርሱ ግን ከማርያም ጋር ያነጻጽሩታል።ስለ አጋንንት የተጻፈውን ተቃራኒውን ወደ መላእክት መተርጎም።ለምሳሌ፦ ሰይጣን ከከሰሰ መላእክት ያማልዳሉ፤ሰይጣን ሰውን ካሳሳተ መላእክትማ ሰውን ይመራሉ ወዘተ እያሉ ስለመላእክት ባልተጻፈ ግን በተነጻጸረ መንገድ መልስ ለመስጠት መሞከር ናቸው።ይኼን አካሄድ ደግሞ የወለደው በግልጽ የተጻፈውን ከመረዳት ይልቅ "ምሥጢራዊ ፍች" ፍለጋ መድከም ነው።
እናም የአኹኖቹ ኦርቶዶክሳውያን "መምህራን" ከዚህ በፊት ተሰምተው የማያውቁ ዐዳዲስ ትርጓሜና ትምህርትም አላቸው።ብቻ የሚሉትን ትምህርት ይደግፍላቸው እንጂ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛ ትርጉምና መልእክት አይጨነቁም።በዚህ ነገር ከሚታወቁት መምህራን አንዱ "መምህር" ዘበነ ለማ ነው።ኦርቶዶክሳዊው ምዕመን መቼም መጽሐፍ ቅዱስ ስለማያነቡ እንደኾነ ብሎ ዐሰበ መሰል ኤርምያስ7:25 አብ አማለደ ይላል ብሎ ሕዝቡን ስቶ አሳስቶአቸዋል።
ውድ ወገኖቼ ኦርቶዶክሳውያን እባካችሁ መጽሐፍ ቅዱስን አንብቡ።መምህራን የሚያስተምሩን ትምህርት እንደወረደ መቀበል ጽድቅ አይደለም ሞኝነት እንጂ፣ እንደቃሉ መመርመር ደግሞ ኃጢአት
አይደለም በሳልነት እንጂ።
✍ 26/0/2015 የምሕረት ዓመት
#ሐዋርያት_እና_ሐዲስ_ሐዋርያ
24/03/2015 ዓ/ም
👉በመጽሐፍ ቅዱስ ዋና ባለታሪክ እግዚአብሔር ነው።የሚታየውንና የማይታየውን ሲፈጥር ከታየበት ከዘፍጥረት አንድ ኹሉን አሳልፎ አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እስከሚፈጥርበት የዮሐንስ ራእይ ድረስ ሚተረከው ልዑል እግዚአብሔር ነው።በመጽሐፉም በብሉይ ኪዳንም ኾነ በሐዲስ ኪዳን የምናገኛቸው የእርሱ ባሪያዎች ማለትም አበው፣ነገስታት፣መሳፍንት፣ነቢያት፣ካህናትና ሐዋርያት ስማቸውና ታሪካቸው ተዘግቦ ይገኛል።የእነርሱ ታሪክ የተጻፈበትንም ምክንያት በቀላሉ መረዳት እንችላለን።
👉ስለእነርሱ የተጻፈበትም ምክንያት፦
አንደኛ ከእነርሱ እንድንማር
ኹለተኛም ከሕይወታቸው ምሳሌን እንድናገኝ ነው።
“አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥10
👉ታሪካቸውን ስናነብ፣ ትምህርታቸውን ስንሰማ የመጽሐፍ ቅዱስ አባቶች ከእኛ የተለዩ አይደሉም።እንደ እኛው ሰዎች ናቸው።እንደእኛው ኖረዋል፣እንደ ሰው ደክመዋል፣ኃጢአትም ሠርተዋል ንስሐም ገብተዋል።ድካምም ኾነ ብርታት ነበራቸው።
“ #ኤልያስ_እንደ_እኛ_የሆነ_ሰው_ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥”
— ያዕቆብ 5፥17
👉በሰዎች ዘንድ ጳውሎስ ከአማልክት እንደ አንዱ ሊያስቆጥረው የሚችሉ ተአምራቶችና ልምምዶች ነበሩት።በመገለጥ ታላቅነትም እንዳይታበይ የሥጋ መውጊያ የተሰጠውም ሐዋርያ ነበር።ከዚህም ያለፈ ብዙ ነገር በሕይወቱ ኾኖአል።ነገር ግን አልተጻፈልንም ጳውሎስ ራሱም አልነገረንም።ምክንያቱንም ሲገልጽ፦
“ልመካ ብወድስ ሞኝ አልሆንም፥ እውነትን እላለሁና፤ ነገር ግን ማንም ከሚያይ ከእኔም ከሚሰማ የምበልጥ አድርጎ እንዳይቆጥረኝ ትቼአለሁ።” — 2ኛ ቆሮ 12፥6
👉ጳውሎስ ያደረገውንና የተቀበለውን ኹሉ ቢነግረን ሰው ኹሉ ራሱን ከጳውሎስ ያነሰ አድርጎ እንዳይቆጥር፣ ወደ አምልኮተ ሰብእም እንዳይቀር ነገርየው በጣም ተጠንቅቆአል።
#በየገድላቱ_ግን፦
ታሪካቸው የተጻፈበት ዓላማ ራሱ ገና ከጅምሩ አሻሚ ነው።ገድላቸውን የምናነብላቸው ሰዎች እነርሱን እንድንመስላቸው ነው የተጻፈው? ወይስ እንድናደንቃቸው? ወይስ እንድናመልካቸው? ግልጽ ዓላማ የለውም።
ለምሳሌ፦ ዛሬ ልደታቸው የሚከበርላቸው አቡነ ተክለሃይማኖትን ብቻ እንኳን እንውሰድ፦
እንደማንኛውም ሰው ያለ ተፈጥሮ የላቸውም።
👉"ምድራዊ ምግብ" በሕይወታቸው በልተው አያውቁም
👉በተወለዱ በሦስተኛው ቀን አፋቸውን ከፍተው ሥላሴን አመሰገኑ
👉መላእክት እየወረዱ ያጫውቷቸው ነበር።ምግብም ያመጡላቸው ነበር
በአንድ ዓመት ከሦስት ወራቸው ጊዜ ወይኑን፣ቅቤውን፣ዱቄቱን አበርክተዋል፣በዚሁ እድሜ እያሉ እኔ እቆያለሁ አንተ ቀድመኸኝ ትሞታለህ ብለው ለአባታቸውም ትንቢት ተናግረዋል።
👉ስድስት ክንፍ አብቅለው በረዋል፣ በሰማይም ከሃያ አራቱ ሽማግሌዎች ጋር የሥላሴን ዙፋን ሄደው አጥነው መጥተዋል
👉ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተቆርጦ፣ በአንድ እግራቸው ብቻ ሰባት ዓመት ቆመዋል
👉የጉልበት ሥራ ሲሠሩም ማንም ሰው ሊሠራው የማይችለውን ሥራ በጣም በፍጥነት ይሠሩ ነበር
👉በደመና ነበር የሚንቀሳቀሱት
👉ሚካኤል ለእርሳቸው የተመደበ ጠባቂ ነበር
👉ሰይጣንን ይዘውም ገርዘው አጥምቀው አመንኩሰዋል
👉በመጨረሻም በተቅማጥ በሽታ ተሰቃይተው ሲሞቱ ይኼም ሞት እንደ ክርስቶስ ስቃይ እንደሚቆጠርላቸው ገድሉ ይገራል።
ሰውም ሲሞት በሰማይ በር ላይ ቆመው መጀመሪያ የሚያገኛቸው እርሳቸውን ነው…
🛑ታዲያ ታሪኩ የአማልክት አፈታሪክ ነው ወይስ እውነተኛ ታሪክ? ታሪኩስ የተጻፈው በሕይወት እንድንመስላቸው ወይስ እንድናመልካቸው?
👉አምላክ ሰው ኾኖ እንኳን በምድር ሲመላለስ እንዲ ሰማይ ሰቀል ታሪክ አልተጻፈለትም።
👉ተክለሃይማኖት ምንም በልተው አያውቁም ክርስቶስ ግን እየበላና እየጠጣ መጣ።ሲያድግም እንደማንኛችንም ሰዎች በሥርዓቱ ነው ያደገው።ተክለሃይማኖት ግን በተወለዱ በሦስት ቀን ውስጥ አፍ ፈትተው ሥላሴን አመሰገኑ
👉ሐዋርያት አጋንንትን በኢየሱስ ስም ቢያወጡም ሐዲሱ ሐዋርያ ተክለሃይማኖት ግን አንገቱን ኹሉ ይዘው ይደበድቡት ነበር።ሆ
ወደ ቃሉ እንመለስ።አንዱ ብቻ በልባችን ይንገስ።
እግዚአብሔር አምላኩ የኾነለት፤ ቃሉንም የሚያውቅ ሕዝብ ምስጉን ነው።
ሊቀ ሐዋርያት ጴጥሮስ እንዲህ ይላል፦
“የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ #በብልሃት_የተፈጠረውን_ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥16
To join the meeting on Google Meet, click this link:
https://meet.google.com/kyq-nmwo-uop
Or open Meet and enter this code: kyq-nmwo-uop
ስንበዛ እንገድላለን፤ ስናንስ ሰማእት እንኾናለን!!!
በአንድ ወቅት ማኅተማ ጋንዲ እንዲ ብለው ስለ ክርስቲያኖች መናገራቸውን አንብቤ ነበር፦ "ክርስቶስን እወደዋለኹ ክርስቲያኖችን ግን እጠላቸዋለኹ ምክንያቱም ክርስቶስን ያምኑበታል እንጂ እርሱን አይመስሉም" በተጨማሪም "ዓለም ኹሉ የክርስቶስን የተራራውን ስብከት ተግባራዊ ቢያደርግ ምድር ምድር መኾኗ ቀርቶ ገነት ትኾን ነበር" ብለዋል።እንግዲህ በታሪክ ውስጥ እንደምናውቀው የክርስትና መስፋፋት መሠረቱ ክርስቶስን መስሎ መሞት እንጂ ሰይጣንን መስሎ መግደል አልነበረም።ከ12ቱ ሐዋርያትም መከራ ያልተቀበለና ያልተሰቃዬ ሐዋርያ አታገኙም።ግን ይሄ ክርስቶስን መስሎ መገደል እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ብቻ የዘለቀ ነበር።በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዘመን በኋላ ግን ቤተክርስቲያን ከስደት ስታርፍና ከጉድጓድ ወጥታ ወደ ሕንጻ ስትገባ፤ ክርስቲያኑ ንጉሥ የቤተክርስቲያኒቱን የቀደመ መልክ ለወጠው ጣኦት አምላኪዎችን ክርስቲያን እንዲኾኑ ማስገደድ ጀመረ።እሺ ያሉትን ለሹመት እምቢ ያሉትን ለስደት ዳረጋቸው።ቤተክርስቲያን በሀብትም በብዛትም እየጨመረች ስትመጣ ወንጌል መስበክ ብቻ ሳይኾን ጉልበትም ተጠቃሚ ኾነች።
ቤተክርስቲያን በቁጥር በበዛችበት ሀገር ገዳይ፤ በቁጥር ባነሰችበት ደግሞ ሰማእት ኾነች።ሙስሊሞች በበዙበት ሀገር ስደተኛ፤ ክርስቲያኖች በበዙባት ሀገር ደግሞ አሳዳጅ ናት። ሉተር፥ ካልቪን፥ ኦርቶዶክስም ኾነ ካቶሊክ ታሪካቸው ይኼው ነው።ከበዙ ይገድላሉ ካነሱ ሰማእት ይኾናሉ።በየትኛውም የክርስትና ታሪክ የበዙ ክርስቲያኖች ባሉበት ጥቂት ያላመኑ ሰዎች ክርስቲያኖችን ገድለው አያውቁም።ክርስቶስ ይዞ የመጣው ትምህርትን ነው።ሰይጣን ግን ያለው መሣሪያ ሰይፍ ነው።
ሙስሊሞችም እንዲኹ ናቸው።ሲበዙ እንደ ሳውዲ ነው ሕጋቸው።ስለ እስልምና ስሕተት መጻፍና መናገር ቀርቶ መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ መታየትም ኾነ ማምለክ አትችልም።ባነሱበት ኹሉ ግን ኢስላም ሰላም ነው።የሰውን መብት የሚያከብር ሃይማኖት ነው።
በቁጥር የበዛው ሃይማኖት የፈለገውን መናገር፥መስበክ፥መሳደብ ይችላል።አናሳው ግን ስሕተቱን ስሕተት ማለቱም ከትንኮሳ ስለሚቆጠር ጳጳሱ እንደተናገሩት "አንገታችን እንሰጣለን።ግን ዝም ብሎ አንገት አይሰጥም አንገት ይዞ መውደቅም አለ እንጂ።"
ዐሳብን በዐሳብ፤ትምህርትን በትምህርት ለመመከት፤ ለዐሳብ ነጻነት ጊዜው ገና ነው።
የክርስቲያኖች Dark Side ይኼው ነው።ከበዙ ይገድላሉ ካነሱ ሰማእት ይኾናሉ።በሉ እንግዲህ አናሳዎች ሰማእት ኹኑ፤ብዙዎችም ግደሉ፥እሰሩ፥አሳዱ።
“እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።” — ዮሐንስ 8፥44
ይህ ዐዲስ የተከፈተው የዋትስአፕ ግሩፕ ሲኾን ዓላማው የእግዚአብሔርን ቃል በልብ ስፋት እንድንወያይና እንድጠያየቅ ማድረግ ነው።
ጆይን አድርጉ……ሼር ማድረግም እንዳትረሱ ተባረኩልኝ።
https://chat.whatsapp.com/DkKvUSr6hRlI9ixvbkSCk6
ጎንደር!!! የሚስዮናዊነት ማሕደር
"ፈረንሳዊ ሆኖ ፓሪስን ያላየ ኢትዮጵያዊም ሆኖ ጎንደርን ያላየ ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ የተረገመ ነው!"
ከተመሰረተ 15ኛ አመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ የሚገኘው የመካነ ኢየሱስ የሚስዮን ማኅበር በእነዚህ አመታት የሚስዮናዊ ጽንሰ ሐሳብ በምእምናን ለማስረጽ በኢትዮጵያ በተለይ በምእራቡና በደቡቡ አካባቢዎች ብዙ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ኣስደናቂ ነገሮች ሆነዋል እነሆ እግዚአብሔር ጊዜ አምጥቶ የሚስዮን ማኅበሩ ወደ ጎንደር የ3 ቀን የሚስዮናዊነት ስልጠና ለመስጠት አቅንቶአል ።
ጎንደር የጥንትዋ ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበር ። ጎንደር ክፍለህገር በሰባት አውራጅዎች ይከፈላል። እነዚህም አውራጃዎች ከነዋና ከተማቸው የሚከተሉት ናቸው፤ ወገራ አውራጃ ዋና ከተማው ዳባት፣ ሰሜን አውራጃ ዋና ከተማው ደባርቅ፣ ደብረታቦር አውራጃ ዋና ከተማው ደብረታቦር፣ ሊቦ አውራጃ ዋና ከተማው አዲስ ዘመን፣ ጋይት አውራጃ ዋና ከተማው ንፋስ መውጫ፣ ጭልጋ አውራጃ ዋና ከተማው አይክል፣ ጎንደር ዙሪያ አውራጅ ዋና ከተማው ጎንደር ናቸው።ዛሬ በስሜን ጎንደር ዞን በአማራ ክልል ሲገኝ ከጣና ሃይቅ ሰሜን አንገረብ ወንዝ ላይ ከሰሜን ተራራ ወደ ደቡብ ምእራብ ሰፍሮ ይገኛል። በ12°36′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°28′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ነው። አጼ ፋሲለደስ ጎንደርን እንደ ዋና ከተማነት ለመጀመሪያ ጊዜ ይጠቀሙ እንጂ ከዚያ በፊት በአካባቢው ሰዎች ይኖሩበት ነበር ሆኖም ግን ከተማው በታሪክ የገነነው አጼ ፋሲለደስ በአሁኑ ፋሲል ግቢ ወይም የነገሥታት ግቢ ውስጥ የፋሲል ግንብን በ1636 ሲያንጽ ነበር።
ጎንደር ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ 656 ኪ.ሜ. እንዲሁም ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር 175 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የምትገኝ በቀደምት ዘመናት የነገሥታት መናገሻ የነበረች ታሪካዊ ከተማ ናት። በ17ኛውና 18ኛው መ.ክ.ዘ የተሰሩ ታሪካዊ ቅርሶቿ የከተማዋ መገለጫዎች ናቸው። ታሪካዊ ቅርሶቿ የቱሪስቶች መዳረሻ ለመሆን አብቅቷታል። በታሪክና በባህል ነፀብራቅነቷም ትታወቃለች፡፡ የጎንደር ከተማ ዋነኛ የቱሪስት መስህብ የሆኑት አብያተ መንግስታትና አብያተ ክርስቲያናት በወርቃማው ዘመኗ የኢትዮጵያ ነገሥታት ያሰሯቸው ናቸው፡፡ አብያተ መንግሥታቱ በከተማው መሃል በሚገኘው ከፍተኛ ስፍራ ላይ ይገኛሉ። አብያተ መንግሥታቱ የተሰሩት ከድንጋይ፣ ከእንጨትና ከኖራ ሲሆን የጥንት ኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ረቂቅነትን ያንፀባርቃሉ፡፡ የፋሲል ግንብ የኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ አሻራ ያረፈበት ግንባታ ነው። አገራችን የራሷ ግብረ-ሕንፃ አሰራር እንደነበራት በዓለም የመሰከረውን ግብረ-ሕንጻ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /UNESCO/ እ.ኤ.አ ጥቅምት 1979 ዓ.ም. በዓለም ቅርስነት ሊመዘግበው ችሏል፡፡
ጎንደር በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለምአቀፍ ደረጃ ስመ ገናና መሆን የጀመረችው ግን በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ-መንግስት ለመናገሻ ከተማነት ከተመረጠች ማግሥት ጀምሮ ለመሆኑ አሌ አይባልም። በተለይም በአባቱ በአፄ ሱሲንዮስ ዘመን ቅሬታ የነበራትን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅሬታ በመፍታት፣ በአባቱ የንግሥና ዘመን አብባ የነበረችውን የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ወደ ጎን በመግፋታቸው ከሀገር ውጭ ስሟ በደጉም በክፉም እንዲነሳ አድርጓታል። በተለይም አፄ ፋሲለደስ ከሚሲዮናውያን ጋር የገቡበት እሰጥ-አገባ ጎንደር ከኢትዮጵያ አልፋ በዓለም ላይ ስሟ ደጋግሞ እንዲነሳ አድርጓል።
አፄ ፋሲለደስ ጎንደር የከተማ ቅርፅ እንድትይዝና ዘመናዊ አኗኗር እንድታዳብር ከማድረግ ባለፈ በኪነ-ሕንፃ ተጠቃሽ ከተማ እንድትሆን ብርቱ ጥረት ያደረገ ንጉሥ ነው። በዚህ ጥረቱም ጎንደር እስከ 1855 ዓ.ም. ድረስ የኢትዮጵያ መዲና ሁና እንድታገለግል መሰረቱን ጥሏል። አሁን በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ አስደማሚ የኪነ-ሕንፃ ውጤቶችን በመገንባትም ፈር ቀደጅ ንጉሥ ነበር።
ጎንደር ከተማ ታሪክ የማይሽራቸው የጥበብ ውጤቶች መገኛ መሆኗ የቱሪስቶችን ቀልብ በቀላሉ የምትስብ ከተማ አድርጓታል። "ከተማዋ በጎርጎሮሳዊያን የዘመን አቆጣጠር በ1636 በአፄ ፋሲል የተገነባውን የፋሲል አብያተ መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ቅርሶችን በጉያዋ ይዛለች፡፡ የፋሲል ግንብ የሚገኝበት እጥር ግቢ 12 ቢሮዎች፣ 6 አብያተ-ክርስቲያናት ሌሎች በተመሳሳይ የስነ-ሕንፃ ጥበብ የተገነቡ ቀደምት ሕንፃዎችን አካቶ የያዘ ነው፡፡ የአፄ ፋሲል፣ የአፄ ዮሃንስ (ፃዲቁ)፣ የልጅ እያሱ (የአፄ አድያም ሰገድ ልጅ) የአፄ ዳዊት፣ የአፄ በካፋና የእቴጌ ምንትዋብ (ብርሃን ሞገስ)፣ የቋረኛው ኢያሱ ቤተ-መንግሥቶች በውስጡ ይዟል። በሌላ በኩል የአፄ ፋሲል የመዋኛ ገንዳ፣ እቴጌ ምንትዋብ ያስገነባችውና ድንቅ የስነ-ሕንፃ ጥበብ ያረፈባት የቁስቋም ቤተ ክርስትያን፣ አድያም ሰገድ ኢያሱ ያስገነቡትና የኢትዮጵያውያን የስዕል ጥበብ የታየባት ጥንታዊቷ የደብረብርሃን ሥላሴ ቤተክርስትያን፣ አፄ ፋሲል ያሰሯቸው ጎንደርን ከአጎራባች ከተሞች ጋር የሚያገናኟት ሰባቱ ድልድዮች፣ የዓባይን መነሻ ለማወቅ በመሻት ጎንደር የከተመው የስኮትላንዳዊው ጀምስ ብሩስ መኖሪያ እና ሌሎች ቅርሶችን አቅፋ የያዘች ድንቅ ከተማ ናት" ፈረንሲያዊ ሆኖ ፓሪስን ያላየ ኢትዮጵያዊም ሆኖ ጎንደርን ያላየ ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ የተረገመ ነው!" ብሏል
ይሕቺ ከተማ እንደገና በሚስዮን መንፈስ ልትነካ ጊዜ ሆኖላታል ለጎንደር እንጸልይ
Mission can, must and will win!!!
