en
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

Open in Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

Show more
447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
#የሮሜ_መልእክት_መግቢያ 🗣 በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት #ማን_ጻፈው? ሮሜ.1:1 ላይ በግልጽ እንደተጻፈው የዚህ መልእክት ጸሐፊ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ነው።ጳውሎስ ይኼንን መልእክት ሲጽፍ የረዳውና የጻፈለት ሰውም ነበር እርሱም ጠርጢዮስ ይባላል።ሮሜ.16:22 #መቼ_ተጻፈ? ይህ መልእክት የተጻፈው ከ56-58 ባለው ጊዜ ውስጥ ነው። #የተጻፈበት_ዓላማ_ምንድን_ነበር? 👉ጳውሎስ በመልእክታቱ የክርስቶስን ወንጌል ምንነትና አስተምህሮ እንዲሁም ክርስቶስን በመከተል እግዚአብሔርን እንዴት ባለ ሕይወት ልናከብረው እንደሚገባ ይጽፋል።በዚህም በሮሜ መልእክቱ የሚታሰርለትን፣ የሚሞትለትንና የተላከበትን ወንጌል ለሮሜ ቤተክርስቲያን ያስተዋውቃል።ጳውሎስ በዚህች ቤተክርስቲያን ለማገልገል ከፍተኛ ፍላጎትና ጸሎት ነበረው።ጌታ ኢየሱስ ግን አልፈቀደለትም ነበር።ጌታ ኢየሱስ እስኪፈቅድለትና መጥቶ እስከሚያገለግላቸው ድረስ የሚሰብከውን ወንጌል ያስታውቃቸዋል።በመልእክቱም መሠረታዊውን የወንጌል እውነትና ሕይወት አስረግጦ ያስተምራቸዋል።ጽፎም ፌበን በተባለች እኅት እጅ ላከላቸው። #የመልእክቱን_ጥቅል_ሀሳብ_የተሸከሙ_ጥቅሶች፦ ሮሜ.1:16/ 3:9-11/3:20-23/ሮሜ.5:8/6:23/8:9/8:28/8:37-39/10:9/12:1/12:19/16:17 #የሮሜ_መልእክት_አከፋፈል፦ 👉ከምዕራፍ 1:1-17 ስለ ወንጌል 👉ከምዕራፍ 1:18-3:19 የእግዚአብሔር ቁጣ 👉ከምዕራፍ 3:20-ምዕራፍ 8 የእግዚአብሔር ጸጋ 👉ከምዕራፍ 9-11 ድረስ የእግዚአብሔር እቅድ ለእስራኤል 👉ከምዕራፍ 12-16 ድረስ የእግዚአብሔር ፈቃድ ናቸው #የሮሜ_መልእክት_በአጭሩ_ሲቀመጥ፦ 👉ጳውሎስ ይህችን መልእክት የጻፈው በቆሮንቶስ ሳለ ነበር።ወደ ሮምም ቤተክርስቲያን መምጣት እያሰበ እያለም በኢየሩሳሌም ታሰረ።ለአገልግሎት እሄድባታለሁ ወዳላት ሮምም እስረኛ ኾኖ ለመሄድ ተገደደ።የዚህ መልእክት አድራሽ የነበረችው ደግሞ ፌበን ነበረች። የመልእክቱ ዋና ዐሳብም "በዘመን መጨረሻ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ጽድቅ" ማስተዋወቅ ነው።መልእክቱ ሰው በኃጢአቱ ምክንያት የጠፋና መፍትሔ ያጣ መኾኑንና እግዚአብሔር ግን ለዚህ ኃጢአተኛ ሰው ያዘጋጀውን መፍትሔ ልጁን ክርስቶስን ያስተዋውቃል።ክርስቶስ ገና ኃጢአተኞች ሳለን ስለ እኛ በመሞት ፍቅሩን ገልጾልናል።ማንም በራሱ ጥረት መጽደቅ አይችልም።ጽድቅ የሚገኘው እንዲሁ በነጻ ክርስቶስን በማመን ብቻ ነው። 👉ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍትም እየጠየቀሰ አይሁድን ይሞግታል።በእምነት ስለጸደቀው አብርሃም፣ በአዳም አለመታዘዝ ኃጢአተኛ ስለመኾናችን በአንጻሩ ደግሞ በክርስቶስ መታዘዝ ስለ መጽደቃችን፣ ዳዊት ኃጢአተኛ ስለሚጸድቅበት የጌታ ጸጋ ስለመተንበዩ እያነሣ ጽድቅን ያብራራል። “አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥”   — ሮሜ 3፥21 ከብዙ በጥቂቱ የሮሜ መግቢያ ይኼንን ይመስላል። ✍ 15/09/2015 የጌታ ዓመት

#ጨለማ_የነበረ_ወይስ_የተፈጠረ_ነው? 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት #በመንፈሳዊው_ጨለማና_በተፈጥሮአዊው_ጨለማስ_መካከል_ልዩነት_የለምን? 👉ጨለማም ኾነ ብርሃን ፍጡራን ናቸው።አንዳንዶች እንደሚያስቡት ጨለማ የብርሃን አለመኖር ነው።እግዚአብሔር ጨለማን አልፈጠረም ብለውም ይሞግታሉ።ጨለማ የነበረ እንጂ የተፈጠረ አይደለም ምክንያቱም "ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ" ይላልና ይላሉም።ለእነዚህ ሰዎች ማስታወስ ያለብኝ ነገር የዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ አንድ ዓላማ "እግዚአብሔር በስድስት ቀናት ውስጥ ፍጥረታትን እንደፈጠረ ጥቅል መረጃ መስጠት እንጂ ዝርዝር መረጃ መስጠት አይደለም ስለኾነም "ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ ማለት ጨለማ ያልተፈጠረ ነው ማለት አይደለም። #በዘፍጥረት_አንድ፦ ❓ውኃን እግዚአብሔር እንደፈጠረው አይናገርም ስለዚህ እግዚአብሔር ውኃን አልፈጠረም ማለት ነውን? ❓ስለ ነፋስና መዛግብታቸው፣ ስለመላእክትና ስለ አለቆቻቸው ዘፍጥረት አይናገርም ስለዚህ ነበሩ እንጂ አልተፈጠሩም ልንል ነው? እሳትስ መቼ ነው የተፈጠረው? ነው አልተፈጠረም? 👉በተጨማሪም ጊዜ ፍጡር ነው።የተፈጠረውም በእግዚአብሔር ነው።ምድራችን ባለ ሃያ ዐራት ሰዓት አቆጣጠር ያላት ናት።ጨለማ ደግሞ ሌሊት ወይም ከሃያ ዐራት ሰዓቱ ውስጥ 12 ሰዓቱ ማለት ነው።ስለዚህ ጨለማ አልተፈጠረም ማለት ጊዜ አልተፈጠረም ማለት ነው።"ጨለማውንም ሌሊት ብሎ ጠራው" ዘፍጥ.1:5 👉ቅዱስ አውግስጢኖስም እንዲህ ይላል፦ "እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር በጊዜ ውስጥ ሳይኾን ከጊዜ ጋር ነው" ለዛ ነው ፀሐይና ጨረቃ በሌሉበት ቀን መቆጠር የተጀመረው።ጨለማም የጊዜ አካል ነውና በእግዚአብሔር የተፈጠረ ነው። 👉ደግሞስ ጨለማ የሚባል ልክ እንደ ብርሃን ህልውና ያለው ፍጡር  "ነበር" እንጂ "አልተፈጠረም" እንዴት ይባላል? ካልተፈጠረ ጨለማ ከየት መጣ? ሰማይንና ምድርን ፈጠረ ማለት ሰማይንና ሠራዊቱን፣ ምድርንና ሠራዊቷን ፈጠረ ማለት በመኾኑ ምድርን ሲፈጥር፦ በምድር ያሉ ፍጥረታት ኹሉ ተፈጥረዋል፣ ጨለማን ጨምሮ።  👉ከእግዚአብሔር በቀር ኹሉም የተፈጠረ በመኾኑ ጨለማም በእግዚአብሔር የተፈጠረ ነው።እንዲህ ይላል ቃሉ፦ “ብርሃንን ሠራሁ፥ #ጨለማውንም_ፈጠርሁ…… እነዚህን ሁሉ ያደረግሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ።”   — ኢሳይያስ 45፥7 👉ብርሃንን የሠራ ጨለማንም የፈጠረ እግዚአብሔር ነው።ታዲያ ለምንድን ነው አንዳንዶቹ "ጨለማን አልፈጠረም የሚሉን" ካልን ሳይንሱ "ጨለማ የብርሃን አለመኖር ነው ስላላቸው" የተሸወዱ ይመስለኛል።ኹለተኛ ደግሞ በተፈጥሮአዊው ጨለማና በምሳሌነቱ መካከል ግልጽ ልዩነት እንዳለ ስላልተረዱ ነው። 👉 (ጨለማውን=ሌሊት) (ብርሃኑንም=ቀን) ብሎ ጠራቸው ይላል።ስም ያወጣላቸው ኹሉ በእግዚአብሔር የተፈጠሩና ገዢያቸው ራሱ እግዚአብሔር መኾኑን ያመለክታል።ለዚህም ማስረጃ የሚኾነን "አዳም ለእንስሳት ኹሉ ስም ማውጣቱ…ገዢነቱን ያመለክታል" ስለዚህም የተፈጥሮአዊው ጨለማ ማለትም የሌሊት ገዢ ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።የጨለማው ገዢ ተብሎ ከተገለጸው ከዲያብሎስ ጋር በፍጹም ተነጻጻሪ አይደለም። 👉የተፈጥሮአዊው ጨለማና የመንፈሳዊው ጨለማ ልዩነት እንደሚከተለው ነው፦ ✍03/09/2015 የጌታ ዓመት

#መዝሙርን_መረዳት        🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ዝማሬ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ነው።መጽሐፍ ቅዱስ ዝማሬ አምልኮ በመኾኑ አድራሻውን እግዚአብሔር አድርጎ በማስተዋልና በመረዳት የሚቀርብ መስዋዕት መኾን አለበት።ለአንዳንድ ሰዎች አሳሳቢው ነገር ድምቀቱና የዜማ መሣሪያው እንዲሁ አዚያዚያሙ ነው…ለእግዚአብሔር ግን ጉዳዩ ዝማሬው የሚቀርብበት ልብ ነው።የሚቀርብበት ልብ ማለትም እምነትና ንጽሕና ማለቴ ነው። 👉ለአንዳንዶች ደግሞ መዝሙር የፕሮግራም መሸጋገሪያና ማድመቂያ ነው፣ ለአንዳንዶችም ማነቃቂያ ነው።ነገር ግን ዝማሬ ለንጉሡ ለእግዚአብሔር በእውነትና በመንፈስ፣ በእምነትና በንጽሕና የሚቀርብ መስዋእት ነው። 👉ለአንዳንዶች ደግሞ መዝሙር መዝሙር ሚኾነው ችክችካ ሲበዛውና ዝላይ ሲኖረው ነው።ሲዘሉና ሲፈነጥዙ ዳዊትን የኾኑ ይመስላቸዋል (ዳዊት አንድ ቀን ቢዘልም እድሜ ልኩን ሲዘል የኖረ ያስመስሉታል።) ስጋቴ ያዘለለን በጌታ ፊት የኾነልንንና ያደረገልንን አስበን ወይስ በሙዚቃው ኃይል ተነክተን ነው? ወይስ የሚዘሉ ሰዎች አሳቅቀው እያዘለሉን ይኾን? እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል፦ “እግዚአብሔር ለምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤ #በማስተዋል_ዘምሩ።”— መዝሙር 47፥7 👉ለአማኞች ዝማሬ እርስ በእርስ የኢየሱስን ውለታ እያሰብን የምንነጋገርበት ቋንቋችን ነው። መላእክቱም እንዲሁ እርስ በእርስ በዝማሬ ያወጋሉ፦ “ #አንዱም_ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።”— ኢሳይያስ 6፥3 እኛም እንዲህ ተብለናል፦ “ #በመዝሙርና_በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ #እርስ_በርሳችሁ_ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤”   — ኤፌሶን 5፥19 👉ዝማሬ ለእግዚአብሔር ለአምላካችን የሚቀርብ አምልኮ በመኾኑ በጥንቃቄና በክብር ልንሰዋው ይገባል። “እንግዲህ #ዘወትር_ለእግዚአብሔር_የምስጋናን_መሥዋዕት፥ ማለት #ለስሙ_የሚመሰክሩ_የከንፈሮችን_ፍሬ፥ #በእርሱ_እናቅርብለት።”— ዕብራውያን 13፥15 “ #ለስሙም_ዘምሩ፥ #ለምስጋናውም_ክብርን_ስጡ።”— መዝሙር 66፥2 ✍ 13/08/2015 የጌታ ዓመት

#የኢየሱስ_ዐርብ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት ንግግሩ ቁጥብ ነው።ጮሆ ሲናገር ማንም ሰምቶት አያውቅም።መናገር ሲጀምር ከአንደበቱ ሞገስ ይፈሳል።ቃላቱ ለልብ እንጂ ለአእምሮ አይገቡም።መልእክተኛ ብቻ ሳይኾን እርሱ ራሱ መልእክት ነበር።ቀንተው ክፉ ከሚያወሩበት በቀር በሕጉ መሠረት ነቀፋ አይገኝበትም።ቅዱስ ነው፣ ግን ለረከሱት ወዳጅ ነው።ንጹሕ ነው፣ ግን በኃጢአት ላደፉት ይራራል። ተአምራትን ያደረገው የተቸገሩትን ለመርዳት እንጂ ብቃቱን ለማሳየት በፍጹም አልነበረም።የተራቡትን የመገበው በመንገድ ዝለው እንዳይወድቁና እንዳይጎዱ እንጂ ከእነርሱ ምስጋናን ሽቶ እንኳን አልነበረም።ሲጠሩት ይሄዳል፣ ለኢየሱስ ጠሪ አክባሪ ነውና።ሠርግ ቤት፣ በስምዖንና በዘኬዎስ ቤት በፍቅር ተገኝቶአል። ኢየሱስ የሕዝቡን ችግር ፈታ እንጂ ለሕዝቡ ችግር አልነበረም።ፈውሳቸው እንጂ ሕመም አልነበረም።ለጠፉ በጎች እረኛ እንጂ ምንደኛ አልነበረም።የሕዝቡ አገልጋይ እንጂ መንግስትን የሚሻ ፖለቲከኛ አልነበረም።የሚያጅበው ብዙ ቢኾንም የሚከተሉት ግን ጥቂቶች ነበሩ።የሚያደንቁትና የሚደነቁበት ብዙ ይኹኑ እንጂ ማን እንደኾነ ያወቁት ግን ጥቂቶች ብቻ ነበሩ። በመጨረሻው ቀንም…… ወደ አብ የሚኼድበት ቀን ሲደርስ፣ የመጣበትንም ዓላማ ሊፈጽም ባለ ጊዜ።ዐርብ።ዐርብ ማለት መካተቻ መግቢያ መጥለቂያ ማለት ነው።በዛ ቀን ያ ያገለገለው ሕዝብ ፊቱን አዞረበት።ብቻውን በጲላጦስ ፊት ቆመ።ጠበቃ አልነበረውም።ንጹሕ ነው ፍቱት ብሎ የተሟገተለትም የለም።ያ ከእጁ የተመገበ ሕዝብ፣ ከለምጹና ከበሽታው የዳነ ሕዝብ፣ ከአጋንንት እስራት የፈታቸው ሰዎች አብረውት አልቆሙም።በኢየሱስ ዐርብ ኢየሱስ ብቻውን ነበር።ኢየሱስ አንዱ ፤ ስለ ኹሉ ብቻውን ሞተ።ታዲያ ብቻውን ሊመለክና ሊዘመርለት አይገባምን? ብቻውን ላዳነ ብቻውን ክብር አይገባውምን? ብቻውን ነፍሱን ለሰጠ ብቻውን ዝማሬ አይገባውምን? 🤲ብቻህን ለሞትክልኝ ክብር ለአንተ ብቻ 🤲ብቻህን ለተሰዋህልኝ ብቻህን መስዋእቴ ይገባሃል 🤲ብቻህን ለታረድክልኝ ብቻህን አምልኮ ይገባሃል አሜን ወአሜን ✍ 06/08/2015 የጌታ ዓመት

#አልተከፈለም 🗣አገልጋይ ብርሃኑ ታምራት የብልጽግና ወንጌል የተሳሳተ የሰው ትምህርት ሳይኾን የአጋንንት ትምህርት ነው።ብዙዎች በስሜ ይመጣሉ እንደሚል ቃሉ "በኢየሱስና በመስቀሉ ሥራ ስም" የመስቀሉን ሥራ የማውረድና የማክፋፋት ትምህርት ነው።አይተኬ የኾነውን የመስቀል ሥራ ተራ ሥራ ማድረግ ነው። ሰው በትክክል ችግሩ ምንድነው? ኢየሱስን ከሰማይ ያወረደውና ለመስቀል ያበቃው ችግራችን ምንድን ነው? ድህነት ነበር እንዴ ችግራችን? ጤና ማጣት ነበር ወይ ችግራችን? በፍጹም አይደለም።የእኛ መሠረታዊ ችግር ኃጢአትና ኃጢአት ብቻ ነው።በኃጢአታችንም ምክንያት ሞት።ከዚህ ውጭ የኢየሱስን ከሰማይ ሰማይ መውረድ፣መሰቀልና መሞትን የሚጠይቅ የሰው ችግር የለም። ኢየሱስ የሞተልን በማንምና በምንም ዓይነት መንገድ ለማናገኘው ነገር ነው።እርሱም የዘላለም ሕይወት ብቻ።ማንም ሰው ሠርቶ፣ደክሞ፣በእገሌና በእገሊት በኩል የዘላለም ሕይወት አይገኝም።ጤናና ሀብት ግን የኢየሱስን የመስቀል ሥራ አይጠይቅም። ሰው ቢያንስ በሦስት መንገድ ባለጠጋ ይኾናል። አንደኛ ጠንክሮ በመሥራት(በጽድቅና በትክክለኛው መርኅ) ኹለተኛ በውርስ (ምንም ሳይለፋ ከወላጆቹ ሀብትን መውረስ ይቻላል) ሦስተኛ፦ በዘረፋ (ሙስና፣ ዕፅ በማዘዋወርና የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈጸም ሰው ሀብታም ይኾናል። በዛ ላይ ሀብት ማግኘት በሂደት እንጂ በቅጽበት ፈጽሞ አይኾንም።በመስቀሉ ያገኘነው የዘላለም ሕይወት ግን ባመንበት ቅጽበት የተቀበልነው የማይጨምር የማይቀንስ ብልጽግናችን ነው። ጤናም ቢኾን በአመጋገብ፣ ጤናማ ለመኾን የሚጠይቀውን ነገር በማድረግ ጤናማ መኾን ይቻላል።ያለ ክርስቶስ ሀብታምና ጤነኛ የኾኑ ሰዎችን በምን ልታታልሏቸው ነው? በየመድረኩ ባለጸጋ ኾነሃል ሲባል አሜን የሚልና አእምሮውን የተቀማው ሰው ብዛትስ? እግዚኦ።ከኾንክ ለምን አይደለህም አኹን? ታመህ ተኝተህ ተፈውሻለሁ ምትለው ለማለት ያህል ነው ወይስ ስለተፈወስክ? ራስህን ለምን ታታልላለህ? መታመምህን ብታምን እኮ ወይ ይጸልይልሃል ወይ ትታከማለህ።ታመህ ተፈውሻለሁ …ከዛ አውጀህ አውጀህ አልኾን ሲልህ ተደብቆ መታከምን ምን አመጣው? ኢየሱስ ለብልጽግናና ለጤናችን ሲል እንደሞተልን አንድም ቦታ አልተጻፈም።እደግመዋለሁ አንድም ቦታ አልተጻፈም።በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያልተጻፈውን፣ የሕይወትም ማረጋገጫ የሌለውን የአሮጊቶች ተረት ከመስማት ፈቀቅ በል። ድሃ ከኾንክ እግዚአብሔርን አምነህ ጠንክረህ በመሥራት ታሪክህን መቀየር ትችላለኽ።ጤና የምትፈልግ ከኾነ ጸልይ፣ስፖርት ሥራ፣ አመጋገብህን አስተካከል።አለቀ።አታመናፍስ።

#የተሐድሶ_አገልግሎትና_አገልጋዮች 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት ክፍል ኹለት የተሐድሶ አገልግሎት ሊያተኩርበት ይገባል ብዬ የማስባቸው ርእሰ ጉዳዮች አሉ።እነዚህ ጉዳዮች የኹሉም አብያተክርስቲያናት ተልእኮዎችም ሊኾኑ ይገባል። 1⃣ባሕልና ትውፊት(culture and tradition) ትውፊትና ባሕልን በተመለከተ ያለው ጉዳይ ብዙም አሳሳቢ ባይኾንም ቅሉ አኹን በሚታየው በብዙው የተሐድሶ አገልግሎት ነባሩ መልክ እየተለወጠና በሌላ እየተተካ እየመጣ እንደኾነ ምልክቶች ይታያሉ።ከጥንታዊት ቤተክርስቲያን ልናስቀጥለው የሚገባ ባሕልና ትውፊት እንዳለ ይሰማኛል።ነጠላና ቀሚሱ፣ አቀማመጥና የዜማ መሣሪያ ብቻ በቂ አይደለም።በሐዋርያት ዘመንና በተከታዮቻቸው የነበረው የታወቁ ወጎች፣ባሕልና ትውፊቶችን በመለየት ማስቀጠል አስፈላጊ ነው።ስናድስ እንዳናፈርስ ማለት ይኼውም አይደል።ይኼም በዋነኝነት አስተዳደራዊና የአምልኮ ሥርዓት አፈጻጸምን ይመለከታል። 2⃣ተተኪ ደቀመዛሙርትን ማፍራት አንዳንድ የተሐድሶ አገልግሎቶች የሚቀጥሉ እንዳልኾኑ ከአያያዛቸው ተነሥተን መናገርና መተንበይ ይቻላል።ተተኪ ከዐዲሱ ትውልድ ማፍራት አስፈላጊ ነው።ስለኾነም ለዛ የሚያበቃ ትምህርቶችና ሥልጠናዎች፣ ፕሮግራሞችና የፓናል ውይይቶች ያስፈልጋል። 3⃣የወንጌል አገልግሎት የትኩረት አቅጣጫዎችን ማጤን ስለ ወንጌል ሦስት ኃላፊነቶች አሉብን።በወንጌል ማመን፣ ወንጌልን ላልዳኑት መመስከር፣ ወንጌልን ከስሕተት ትምህርት መጠበቅ ናቸው።ታዲያ የተሐድሶ አገልጋዮች ሚናቸውንና ጥሪያቸውን በመለየት ማን ምስክርነት ላይ ይሥራ፣ ማን ዕቅበተ እምነት ላይ ይሥራ የሚለውን እንደገና ማጤንና መሠማራት አስፈላጊ ነው። 4⃣በየመድረኩ የሚሰጡ ትምህርቶች ዓላማ ተኮር ቢኾኑ እገሌ ዛሬ ይስበክ፣ ቀጥሎ እገሌ ከማለት ይልቅ፣ ለዚህ ጉባኤ ይኼን ትምህርት ማስተማርና በዚህ ጉዳይ ማስታጠቅ አለብን በማለት "ዓላማችን" ነው ሊያንቀሳቅሰን የሚገባው።ርእስና ሰባኪ እየቀያየሩ መስበክና ማሰበክ ብዙ ርቀት አያስጉዝም።ትምህርት ቀጥሎ ተልእኮ።ትምህርት ቀጥሎ ውይይት፣ ትምህርት ቀጥሎ ውጤት መመዘን እያሉ "ራእይ ተኮር" ተልእኮን መወጣት። 5⃣እያንዳንዱ የተሐድሶ አገልግሎት በፋይናንስ ራሱን እንዲችል ቢሠራ ብዙ አገልጋዮች ወደ ዓለም፣ ወደ ሥራ፣ ወደ ኦርቶዶክስና ወደ ፕሮቴስታንት የሚፈልሱበት አንዱ ምክንያት በፋይናንስ ምክንያት ነው።አገልግሎቱ በፋይናንስ ራሱን የሚችልበትን እቅድና ፕሮጀክት አዘጋጅቶ መንቀሳቀስ አለበት።አስራትና ባለሐብትን ማመን የምንችልበት ጊዜ ላይ አይደለንም። ………………… ✍ 25/07/2015 የምሕረት ዓመት

#የተሐድሶ_አገልግሎትና_አገልጋዮች       🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት ክፍል አንድ 👉የተሐድሶ አገልግሎት በተለያዩ ሰዎች የተለያየ ሀሳብ የሚሰነዘርበት አገልግሎት ነው።የሚደግፉትም የሚቃወሙትም ብዙ ናቸው።ኦርቶዶክሳውያን እንኳን ሳይቀር ሲደግፉትና ሲቃወሙት ማየት እንግዳ ነገር አይደለም።ትንሽ ለየት የሚያደርገው ኦርቶዶክሳውያን ደጋፊዎቹ ድጋፋቸውን በይፋ አለመግለጻቸው ብቻ ነው።በወንጌላውያን በኩልም ድጋፍ አለው ተቃውሞም እንዲሁ።ተቃውሞውን ለየት የሚያደርገው እንዲሁ በይፋ አለመኾኑ ነው። 👉አንዳንዶች አገልግሎቱ ግቡ ምን እንደኾነ ይጠይቃሉ።"ይኼን ይኼን አደረጋችሁ ከዛስ ?" ይላሉ።በነገራችን ላይ የተሐድሶን ግብ በውጭ የሚመለከቱ ብቻ አይደለም የሚጠይቁት።ውስጥም ያሉትም ጭምር ናቸው።"ቅርጽና መልክ ያለው፣ እዚህ ስንደርስ ነው ሩጫችንን ጨርሰናል የምንለው" የሚልን ነገር ብዙ አማኝ መስማት ይፈልጋል። 👉የተሐድሶ አገልግሎት ከየት ተነሥቶ የት መድረስ እንደሚፈልግ አንድ የሚያግባባ ድምፅ ልንሰማ ያስፈልጋል።ተሐድሶአውያን "ዝም ብለው ወንጌልን በመስበክ ብቻ መጠመድ የለባቸውም" ስለ አገልግሎቱ ራእይና ግብ፣ እንዲሁም መዳረሻ ሊያስታጥቁና ሊያስተምሩ ይገባል።ዝም ብሎ ተሰብስቦ የሚበተን አገልግሎት፣ ፕሮግራም ተኮር ጉባኤ ምንም ፋይዳ የለውም። 👉አገልጋዮች አማራጭ ቢኖራቸው እንኳን አማራጭ እንደሌለው ሰው ዋጋ ሊከፍሉለት የሚገባ አገልግሎት ሊኾን ይገባል።"ተሐድሶ ማለት…" እያሉ ቃል ሲተነትኑና ለኹሉም ቤተእምነት ያስፈልጋል እያሉ የቤት ሥራን ማብዛት የትም አያደርስም።አስር ዳቦ ከመላስ አንድ ዳቦ መብላት።ለማን ነው የተላኩት? አገልግሎቴ ምንድን ነው? ከማን ጋር ነው ምሠራው? የት መድረስ ነው የፈለኩት? በየትኛው መንገድ ብሄድ አሳካዋለሁ? ምን ምን እድሎች አሉኝ? ምን ስጋት አለብኝ? ምን ላስተካክል? እያሉ የተመረመረን አገልግሎት ማገልገል…ግንዛቤ መፍጠርና ራእይን ማካፈል ተገቢ ነው። ………… ✍24/07/2015 የምሕረት ዓመት

በድንግል ማርያም ዙሪያ የሚሰጡ የኦርቶዶክስ ትምህርት በየመድረኩና በአንዳንድ ምላሾቻቸው "እኛ የምናመልከው እግዚአብሔርን ብቻ ነው ፣ቅዱሳንን ግን እናከብራለን" የሚሉ ሀሳቦችን ብንሰማም እውነታው ግን እንደሚሉት አይደለም።ድንግል ማርያም ከፍጡራን ብቻ ሳይኾን ከፈጣሪም በላይ ናት።መጽሐፍ ቅዱስ ስለእርስዋ የሚሰጠን መረጃ ጥቂት ብቻ ቢኾንም ያን ለመበቀል ይመስላል አዋልድ መጻሕፍት ከግማሽ ፐርሰንቱ በላይ ስለድንግል ማርያም የሚናገሩ ናቸው።የሚናገሩትም የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረው አይደለም። "መምህራኑ" የሚያስተምሩትን ትምህርት ቁጭ ብለው ለመመዘን ጊዜ ያላቸው አይመስልም።ማስተዋላቸውን የተቀሙ ኾነዋል።ምን ያኽል ማስተዋላቸውን እንደተቀሙ የሚያሳይ ጥቂት ምሳሌዎችን ላሳያችሁ። አንደኛ፦ ኢየሱስንና ማርያምን በትምህርታቸው መሠረት እናነጻጽራቸው፦ ኢየሱስ ፍጹም ሰው ኾነ፣ ስለዚህ ከኃጢአት በቀር በነገር ኹሉ እኛን ይመስላል።እየበላ እየጠጣ መጣ።እንግድነት ሄዶ ያቀረቡለት በልቷል ጠጥቶአል። ድንግል ማርያም ግን ፍጡር ሰው ናት።ኾኖም ግን ሰው የበላውን ምግብ በሕይወቷ በልታ አታውቅም።ምግቧ ኹሌም ከሰማይ ነው ሚመጣው።ማስረጃ ለምትፈልጉ ቅዳሴ ማርያም ላይ ታገኙታላችሁ። ወደ ጥንተ አብሶ ደግሞ እንለፍ……… ድንግል ማርያም የአዳም ኃጢአት አልነካትም።ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ በንጽሕና ጠበቃት።ለምን ጠበቃት? ስንላቸው "ጌታ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ስለሚካፈል ኃጢአት የሌለበት ሥጋና ነፍስ እንዲካፈል" ይላሉ። እኛም በማስከተል እንዲህ ብለን ብንጠይቃቸው የሚሉትን እንዲያስተውሉ እንረዳቸው ይኾናል፦ ጥንተ አብሶ ካለባቸው ሐናና ኢያቄም ጥንተ አብሶ የሌለባት ድንግል ማርያም ከተወለደች፣ ጥንተ አብሶ ካለባት ድንግል ማርያም ጥንተ አብሶ የሌለበት ኢየሱስ እንዴት ሊወለድ አይችልም ትላላችሁ?" ኹለቱን ቀላል ምሳሌ ብቻ በማየት ኦርቶዶክሳዊው የነገረ ማርያም ትምህርት አግድም አደግ የቃለ እግዚአብሔር ድጋፍ የሌለው መኾኑን እንረዳለን። …………………

#ትዝብት_1 🗣አገልጋይ ብርሃኑ ታምራት #ኧረ_ሰባኪዎች_በሕግ_አምላክ 👉ክርስቶስ አምኖን እድል ሲሰጠን ምነው ብንታመን።ስበክልኝ ብሎ መንጋውን ሲሰጠን "ቃሉን መስበክን" ትተን ስለራሳችንና ስለፖለቲካ፣ ስለሰማነው ዜናና ስለሀገራዊ ሁኔታ ይህን ምስኪን ሕዝብ ጊዜውን ስንበላበት አያሳዝናችሁም? ኧረ በሕግ አምላክ ሕዝብ ቢያንስ ስለኢየሱስ የሚሰማበት አንድ "ቅዱስ ስፍራ" ይኑረው እባካችሁ። 👉አንዳንዱ ሰባኪ ደግሞ motivational speakerን ይመስላል።ለሰማያዊው ጥሪ "አንቁልኝ" ብሎ መድረክ ቢሰጠን ለምድሩ "አነቃቅተን" እንልከዋለን።እባካችሁ ወይ እንደ ንግድ ፈቃድ "ዘርፍ" ቀይሩ።አነቃቂ መኾን ነውር አይደለም፣ ኃጢአትም አይደለም።ግን ቦታ ቀይሩ።በእግዚአብሔር ቤት የእግዚአብሔርን ዐሳብ ብቻ ንገሩን።እያነቃቃችሁ ሰውን የራሱ አምላክ እንዲኾን አታድርጉት።በአምላኩ ልቡን የሚያበረታ የተልእኮ ሰው ፍጠሩ እንጂ ያልተሰጣችሁን ተልእኮ አትፈጽሙ። 👉ከአነቃቂው ወዲህ ማዶ ደግሞ እጅና እግር የሌለው ስብከት የሚሰብኩን ደግሞ አሉን።ስለምን እየሰበከ እንደኾነ አይታወቅም።አስር ቦታ ይረግጣል።ማእከላዊ ነጥብ የለውም።ሳይዘጋጅ ይመጣና ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ሕዝቡን ሲያንከራትተው አንድ ነገር ሳያስጨብጥ ይወርዳል። ስለኮሜዲያን ሰባኪዎች ምን ማለት እችላለሁ? ✋ — ሕዝቅኤል 34፥10 ሕዝቅኤል 34⁹ ስለዚህ እረኞች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ ¹⁰ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እኔ በእረኞች ላይ ተነሥቻለሁ፤ ስለ መንጋዬ እጠይቃቸዋለሁ፤ ከእንግዲህ እረኞች ራሳቸውን መመገብ እንዳይችሉ፣ መንጋዬን እንዳያሰማሩ አደርጋለሁ። መንጋዬን ከአፋቸው አስጥላለሁ፤ ከእንግዲህም ምግብ አይሆናቸውም። ✍10/07/2015 የጌታ ዓመት

#የጀመርነውን_በትጋት_ስለመጨረስ_አስደናቂ_መጽሐፍ_በማይታመን_ዋጋ #የመጽሐፉ_ርእስ ፦ ሩጫችንን በድል እንጨርስ ይኾን? #የገጽ_ብዛት፦ 387 ገጽ #ጸሐፊ ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ #የመጽሐፉ_ዋጋ፦ 150
#የጀመርነውን_በትጋት_ስለመጨረስ_አስደናቂ_መጽሐፍ_በማይታመን_ዋጋ #የመጽሐፉ_ርእስ ፦ ሩጫችንን በድል እንጨርስ ይኾን? #የገጽ_ብዛት፦ 387 ገጽ #ጸሐፊ ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ #የመጽሐፉ_ዋጋ፦ 150 ብር ብቻ 👉ይኼን መጽሐፍ ለማግኘት፦ ወደ 0978276942 ይደውሉ። 👉ብዙዎች ትምህርት ጀምረው አቋርጠዋል፣ ትዳር ተጀምሮም በፍቺ የተቋጩ ብዙ ናቸው፣ ከብዙዎች ጋር የጀመርነው ወዳጅነትም ተቋርጧል፣ በመንፈሳዊ አገልግሎትም ጥሩ አገልግሎት ጀምረው መሐል ላይ አቋርጠው ወጥተዋል። 👉መጽሐፍም “ #የነገር_ፍጻሜ_ከመጀመሪያው_ይሻላል፤…።” — መክብብ 7፥8 👉ክርስቲያናዊ ሕይወትም ፍጻሜን እያዩ መሮጥ ነው፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 9 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁴ በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።…  ²⁶ ስለዚህ #እኔ_ያለ_አሳብ_እንደሚሮጥ_ሁሉ_እንዲሁ_አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤ ✍ይኼ መጽሐፍ ፦ ☝️በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሩጫቸውን የጨረሱትንና ያልጨረሱትን ምሳሌ በማቅረብ ይጀምራል 2⃣በመቀጠልም የሩጫችን አደናቃፊዎች ምን ምን እንደኾኑ 3⃣በመጨረሻም እስከመጨረሻው ለመሮጥ የሚያስችሉን አስፈላጊ ነገሮችን በመጥቀስ ትምህርቱን ሕይወት ይዘራበታል። #የገጽ_ብዛት፦ 387 ገጽ #ጸሐፊ ፦ ዶ/ር መለሰ ወጉ #የመጽሐፉ_ዋጋ፦ 150 ብር ብቻ 👉ይኼን መጽሐፍ ለማግኘት፦ ወደ 0978276942 ይደውሉ። Let there be light book delivery

#አኹን_በዚህ_ጊዜ #የ50_ብር_መጽሐፍ_ይገኛል? ያውም ድንቅ መጽሐፍ ሕይወት የምርጫና የውሳኔ ውቅር ናት።ውሳኔን የማይጠይቅ ጉዳይ ምንድን ነው? ለውሳኔ ዘግይተን ያመለጠን ዕድል አለ።ባለማስተዋል ወ
#አኹን_በዚህ_ጊዜ #የ50_ብር_መጽሐፍ_ይገኛል? ያውም ድንቅ መጽሐፍ ሕይወት የምርጫና የውሳኔ ውቅር ናት።ውሳኔን የማይጠይቅ ጉዳይ ምንድን ነው? ለውሳኔ ዘግይተን ያመለጠን ዕድል አለ።ባለማስተዋል ወስነንም ውሳኔአችን ጎድቶናል። መወሰንም አለመወሰንም ጥቅምና ጉዳት አለው።ውሳኔ የስኬት ቁልፍ ነው። ዶክተር መለሰ ወጉ ሲናገሩ "አኹን የኾንኩትን የኾንኩት ትናንት በወሰንኩት ውሳኔ ነው።" ይላሉ። የውሳኔ ሰው እንድትኾኑ በውሳኔ አሰጣጣችሁም እንድታድጉ ይኼንን መጽሐፍ ማንበብ ይኖርባችኋል።ይኼ መጽሐፍ፦ 👉እግዚአብሔር ሕይወታችሁን በውሳኔአችሁ እንድትኖሩት አድርጎ እንዴት እንደፈጠራችሁ 👉ትክክለኛ ውሳኔ እንዴት መወሰን እንደምትችሉ 👉ችግር በውሳኔአችሁ ላይ እንዴት ተጽእኖ እንደሚፈጥር 👉ውሳኔአችሁን ስለሚያበላሹ ምክንያቶች 👉ውሳኔ ለምን ትእግስትን እንደሚጠይቅ እድገታችሁ እንዴት በውሳኔ አሰጣጣችሁ እንደሚለካ ይነግራችኋል። ከዶክተር መለሰ ወጉ ትምህርትን ብቻ ሳይኾን ልምድንም ተካፈሉ። መጽሐፉን ማግኘት የምትፈልጉ ወደ ብርሃን ይኹን ቡክ ዴሊቨሪ ይደውሉና ይውሰዱ። ክፍለሀገርና ውጭ አገር ላላችሁም በቀላሉ መላክ ይቻላል 📞+251978276942 ብርሃን ይኹን

#ቢዚ_የኾንነው_ቢዚ_ስለኾንን_አይደለም!!        🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት አንድ በእግዚአብሔር መኖር የማያምን ሰው ለጓደኞቹ "በእግዚአብሔር መኖር ማመን እንደሚፈልግ" ይነግራቸዋል።እነርሱም፦ "ለምን በፈጣሪ መኖር ማመን ፈለክ" ይሉታል፤እርሱም " በሕይወቴ በሚገጥሙኝ ችግሮች ተጠያቂ የማደርገው አካል እፈልጋለሁና ለዛ ነው" አላቸው።  እኛ ሰዎች ሲበዛ ሰበበኞች ነን።ባልተሳኩ ነገሮቻችን ላይ ተጠያቂ የምናደርገው የኾነን አካል እንፈልጋለን። ሰይጣን፣ እግዚአብሔር፣ ወላጆች፣መንግስት፣ ያለንባት ሐገር ፣ያደግንበትን ማኅበረሰብ፣ ጓደኞቻችንን ወዘተ ተጠያቂ ማድረግ እንፈልጋለን። መጽሐፍ የጠቢብ ዐይኖች በራሱ ላይ ናቸው ይላል።አስተሳሰባችንን፣ ጊዜ አጠቃቀማችንን፣ ጠባያችንን፣ ገንዘብ አጠቃቀማችንን፣ሶሻል ሚዲያ አጠቃቀማችንን ወዘተ መመርመር አንፈልግም።ችግሮቻችንን ወደ መልካም አጋጣሚ መቀየርን አልተማርንም።ባለራእይ እንድንኾን የደከመልን የለም።የተማርነውም መማር ስላለብን ወይም ወጥተን ምንገባበት ሥራ ለማግኘት ነው።"ዓላማ ተኮር" የኾኑ ፕሮግራሞች የሉንም። ሲበዛ ቢዚ ነን።ቢዚ የኾንነው ግን ቢዚ ስለኾንን አይደለም።ጊዜ የሌለን ጊዜ ስላጣንም አይደለም።ጊዜ አጠቃቀም ስላልቻልን ነው።ሃያ አራቷን ሰዓት ከፋፍሎ፣ ፕሮግራም አውጥቶ ላወጣውም ፕሮግራም ታማኝ ኾኖ ለመንቀሳቀስ ገና ነን።በስልክ፣በቻት፣በፊልም፣በቲክቶክ፣በወሬ የምናጠፋው ጊዜ፣ ጊዜ አሳጣን እንጂ ቢዚስ አይደለንም።ጉዳዩ ቅድሚያ የመስጠትና ያለመስጠት ኾኖ ነው እንጂ ጊዜ የማጣትስ አይደለም።የእጅ ሰዓቶቻችን ጌጦች እንጂ ሰዓት መቁጠሪያዎች አልኾኑልንም።አላርም ለስሙ ይሞላል እንጂ የጮኸ አላርም አጥፍተን መተኛቱስ አልቀረም። ታክሲ ለመያዝ ተሰልፈንም ኾነ ረጅም ርቀቱን የታክሲ ጉዞ ምንም አናደርግበትም።ወይ ሶሻል ሚዲያ ላይ ነን፤ ወይ ደግሞ ኤርፎናችንን አድርገን በመስኮት አጮልቀን የምናውቀውን አገር መጎብኘት ነው።ታዲያ ስኬት እንዴት አይጠየፈን? ዐሳባችን ባለበት ኹሉ እኛ አለን።የዐላማ ሰው ስንኾን ቢዚ የምንኾነው ቢዚ ልንኾን በሚገባበት ጉዳይ ይኾናል።ጊዜ ጨካኝ ነው፣ አንዴ ከሄደ ተመልሶ አይመጣም።ጊዜ በጣም ደግ ነው፣ ከተጠቀምንበት ይጠቅመናል።ጊዜ ያካበደሉትን ሲያከብድ፣ ያቀለሉትን ሲያቀል ዐይተናል።ብዙ በሮጠ ሳይኾን በማስተዋል የተራመደ ሲቀድም ታዘብን።አብረን አንድ ክላስ ተምረን እኩል ትምህርቱ አልገባንም።ትኩረት የሰጠነው ነገር ይወርሰናል።መዝናናት ላይ አተኩረን ጊዜ በፋንታው ቀለደብን።ዓላማ ላይ ያተኩሩትን ጊዜ አደላላቸው።ዓላማ ተኮር ሕይወትን እንምራ። 👉ቢዚ የኾንነው ቢዚ ስለኾንን አይደለም።ቢዚ ኾነን ቢዚ እንኹን። “There is a time for everything, and a season for every activity under heaven:”— Eccl 3፥1 (NIV) “የሰው መከራ እጅግ ቢጫነውም፣ ለሁሉም ነገር ትክክለኛ ጊዜና ተገቢ አሠራር አለው።”— መክብብ 8፥6 (አዲሱ መ.ት) ✍ 30/06/2015 የምሕረት ዓመት