en
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

Open in Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

Show more
447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
መቅደም ሲያቅት መጥለፍ በዶክተር መለሰ ወጉ የተጻፈ አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ የምትፈልጉ ሰዎች ልታናግሩኝ ትችላላችሁ እኔ ጋ ታገኙታላችሁ
መቅደም ሲያቅት መጥለፍ በዶክተር መለሰ ወጉ የተጻፈ አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ የምትፈልጉ ሰዎች ልታናግሩኝ ትችላላችሁ እኔ ጋ ታገኙታላችሁ

#ስለ_እምነት_እርግጡን_ማወቅ(ሉቃ.1:1-4) 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ሮማዊውና የተከበረው ሰው ቴዎፍሎስ በክርስቶስ አምኗል።ስለ ክርስቶስ ማን እንደነገረውና እንዴት እንዳመነ ባይታወቅም ባለመድኃኒቱ ሉቃስ እንደ ስሙ ትርጓሜ የአምላክ ወዳጅ ለኾነው ለከበረው ቴዎፍሎስ ስለተማረው ቃል እርግጡን እንዲያውቅ ይጽፍለታል። 👉በወቅቱ ስለ ክርስቶስ ከሐዋርያት እኩል ነገር ግን ከሐዋርያት ተቃራኒ የሆነ መልእክትን የሚሰብኩ፣ የእውነትን ቃል የሚያጣምሙ፣ የስሕተትን ትምህርት የሚዘሩና አማኞችን የሚያናውጡ ጥቂቶች አልነበሩም።አማኞች ስለ ክርስቶስ የሚሆነውን ቅንነት ጥለው ልዩ ኢየሱስ የተሰበከላቸው ብዙ ናቸው።ብዙ የክርስቶስ አገልጋዮች መጽሐፍ የጻፉ ቢሆንም በተመሳሳይ ኖስቲሳውያንና ሐሰተኛ ወንድሞች በሐዋርያቱ ስም መጻሕፍትን እያዘጋጁ ይበትኑ ነበር።ይሄ የስሕተት ትምህርት ነፋስ እንዳያገኘው የሰጋው ሉቃስ ስለተማረው ጤናማ ትምህርት እርግጡን እንዲያውቁ በሁለት ቅጽ መጽሐፍን ይጽፍለታል።እንዲህም አለው፦ “የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”— ሉቃስ 1፥1-4 👉ሐኪሙ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈለት "ስለተማረው ቃል እርግጡን እንዲያውቅ" ነው።እርግጠኛው ትምህርት የሚገኘው ከየት ነው? አንድን ትምህርት እውነተኛና እርግጠኛ ትምህርት ምንለው መቼ ነው? ሉቃስ ይሔንኑ ጥያቄ በአግባቡ ይመልስለታል። #እርግጡ_ትምህርት_የሚገኘው፦ ፩ኛ ከዐይን እማኝ ፪ኛ ከእውነተኛ የቃሉ አገልጋዮች (ከሐዋርያት) 👉ሉቃስ ወንጌሉን በጥንቃቄ እንዳዘጋጀው ተናግሯል።ትልቁ ጥንቃቄውም ቴዎፍሎስ "ስለ ክርስቶስ እርግጡን" እንዲያውቅ መርዳት ነው።ለዚህም ከመንፈስ ቅዱስ ግልጠት በተጨማሪ "የዐይን እማኞችን፣ የቃሉ አገልጋዮችን ምስክርነት፣ በእነርሱም ዘንድ ስለተፈጸመው ነገር" እንደ እማኝ ተጠቅሟል።ስለዚህ የሚነግረው ነገር ምን ያህል አስተማማኝ እንደሆነ እንረዳለን። 👉በእኛም ዘመን ስለ ክርስቶስ ሰው እርግጡን ቢፈልግ የምንጠቁመው ወደ ነቢያትና ሐዋርያት መጽሐፍ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው።መጽሐፍ ቅዱስ የሃይማኖት ዶሴ ሳይኾን ግልጠተ መለኮት ነው።መጽሐፍ ቅዱስ የቃሉ አገልጋዮችና የዐይን ምስክሮች የምስክርት ትሩፋትና ከላይ ከሰማይ በወጣ ትእዛዝ የተጻፈ ነው። 👉ስለ ክርስቶስ እርግጥ የኾነው ትምህርት ሁሌም የሚገኘው በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው። 🛑ገላትያ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ። ⁸ ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። ⁹ አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። ✍ 03/01/2016 ዓ/ም

❤️የዓመቱ መጨረሻ መልእክቴ❤️ ጳጉሜን 5/2015 የምሕረት ዓመት #ለ2016_እንዲህ_ብናቅድስ፦ 🗣አገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ሰላም ለእናንተ ይሁን! በምሕረቱ የጠበቀንና ወደ 2016 በሕይወት ያሸጋገረን አምላክ ያሕዌ የተባረከ ይሁን።ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው። 👉እግዚአብሔር በእኛና ለእኛ የዘላለም እቅድና ሀሳብ አለው።በሰው ልብ ብዙ ሀሳብ ቢኖርም የእግዚአብሔር ሀሳብ ነው የሚፈፀመው።ከእግዚአብሔር በታች እንደ ብርሃን ልጆች እቅድን እናቅዳለን።ስለዚህም፦እግዚአብሔር ቢፈቅድና በሕይወት ብንኖር ለ2016 እንዲህ ብናቅድስ፦ #1 መፅሐፍ ቅዱስን አንብቤ እጨርሳለሁ ስለዚህ ከመስከረም አንድ እጀምራለሁ። #2 ቋሚ የፀሎት ሰአት መድቤ ቢያንስ በቀን ሁለቴ በአምላኬ ፊት እሆናለሁ። #3 በተደጋጋሚ ምወድቅበት ኃጢአት ላይ የፀሎትና የምክርም እገዛ በማግኘት በጌታ ፀጋ አሸንፈዋለሁ። #4 ………በክፍት ቦታው ቁጥር በማስቀመጥ ለእነዚህን ያህል ሰዎች ወንጌልን እመሰክራለሁ።ከመሰከርኩላቸው ሰዎች ቢያንስ ይሄን ያህሉ እንዲድኑ እተጋለሁ። #5 በቤተክርስቲያን አባልነት ያልተያዛችሁ ደግሞ በዚህ ዓመት ለቃሉ እውነት ወደ ምታደላ ቤተክርስቲያን አባል እሆናለሁ።በአሥራቴም እታመናለሁ።በሉ። #6 ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን በፆምና በፀሎት እጋደላለሁ #7 ………በክፍት ቦታው ቁጥር በመሙላት።እነዚህን ያህል መፃሕፍትን አነባለሁ። #8 ድሆችንና የተቸገሩትን ከማገኘው ነገር ላይ አስባለሁ። #9 ቤተክርስቲያኔ ባወጣችው እቅድና ባዘጋጀችልኝ ፕሮግራም ሁሉ በንቃት እካፈላለሁ #10 በመጨረሻ ሲንግሎች ፍቅረኛ ያዙ፤በቂ የመጠናናት ጊዜ የወሰዳችሁ ተጋቡ፥የተጋባችሁ ውለዱ……የልባችሁን መሻት ይፈፅምላችሁ……ስለትዳር በማሰብ ግን ልባችሁ አይክበድባችሁ።ሉቃ.21:34 👉ማቀድ ከእቅዳችን ይበልጣል። 📖ኤፌሶን 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ¹⁷ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ። ❤️መልካም አዲስ ዓመት።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን "መናፍቅ ነው" ብላ አውግዛ ትለያለች እንጂ "ተመለስኩ" ያለን ሰው "አምናው" አትቀበለውም።ምክንያቱም ከኦርቶዶክስ ሰው መውጣቱ የተለመደ ሲኾን "መመለሱ"
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን "መናፍቅ ነው" ብላ አውግዛ ትለያለች እንጂ "ተመለስኩ" ያለን ሰው "አምናው" አትቀበለውም።ምክንያቱም ከኦርቶዶክስ ሰው መውጣቱ የተለመደ ሲኾን "መመለሱ" ግን እንግዳ ነገር ስለኾነ ነው። ዘማሪ አሸናፊ ገ/ማርያም፣ ሰሎሞን አቡበከር፣ እዝራ ኃይለሚካኤል፣ አእመረ አሸብር ተመልሰዋል።ነገር ግን "ተመለሱልን" ብሎ ማንም አያምናቸውም።በዐይነ ቁራኛ ይከታተሏቸዋል እንጂ ማንም ስለእነርሱ መመለስ እርግጠኛ መኾን አይችልም።ተአምር ሚኾነው "አምነው ቢቀበሏቸው" ነበር። የተመለሰው ከልቡ ነው ወይስ ያልጨረሰውን ሥራ ሊጨርስ ነው የመጣው? ከመባልና በመሳሳታችሁ ዋጋ ከምትከፍሉ ትክክል ኾናችሁ ዋጋ ክፈሉ ብዬ እኔ ወንድማችሁ እመክራችኋለሁ።

#ወንጌል_ይህ_ነው ሮሜ.1:1-17 ላይ የመሠረተ ጥናት 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት #ሐዋርያው_ስለ_ሚሰብከው_ወንጌል_ምንነት #ያስተማረው፦ #የወንጌል_ባለቤት_ማን_ነው? 👉ጳውሎስ ስለተለየለትና ስለሚያገለግለው ወንጌል ሲናገር "…ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየሁ" ይላል።(1:1) ወንጌል ባለቤት አለው እርሱም እግዚአብሔር ነው።ወንጌል ሰው ሠራሽና ዘመን አመጣሽ አይደለም።የወንጌል ባለቤት እግዚአብሔር እስከኾነ ድረስ በእግዚአብሔር ብርታት ይሰፋል እንጂ በሰው ድካም፣ በጠላት ሴራ አይቆምም።በዚህ ክፍል የእግዚአብሔር ወንጌል ሲል ወንጌሉ የአብ ነው ማለቱ ነው(ሮሜ.15:15-16/1ተሰ.2:2 & 8-9/1ጴጥ.4:17)።ዝቅ ብሎ ደግሞ "የልጁ ወንጌል" ይላል።ወንጌል ስለ ክርስቶስ ብቻ ሳይኾን የክርስቶስም ነው።መልእክቱም ኾነ መልእክተኛ ላኪው ክርስቶስ ነው።(ሮሜ.1:9-10/15:18-19/1ቆሮ.9:12/2ቆሮ.4:4/ገላ.1:7)።ወንጌል የአብ ነው፣ የወልድም ነው።ይኼም አንድነታቸውን አመልካች ነው። #ወንጌል_መሰበክ_የተጀመረው_መቼ_ነው? 👉ወንጌል የእግዚአብሔርና የልጁ እንደ መኾኑ መጠን ከጥንት ጀምሮ ይሰበክ ነበር።ከዘፍጥረት አንድ ጀምሮ እስከ ዮሐንስ ራእይ 22 ድረስ ወንጌል ነው።በታወቀና ግልጽ በኾነ መንገድ ግን እግዚአብሔር ከአዳም ውድቀት ጀምሮ ስለ ልጁ መስበክ ጀምሮ ነበር።ይኼንን በአጭር ቃል ጳውሎስ እንዲህ ሲል ገልጾታል፦ “……በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ።”— ሮሜ 1፥1-2 በገላትያ መልእክቱም፦ “መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ፦ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።”— ገላ.3፥8 ወንጌል የጥንትም የአኹንም ነው።ወንጌል መጤ አይደለም። #ወንጌል_ስለ_ማንና_ስለምንድን_ነው? 👉ወንጌል ስለ እግዚአብሔር ልጅ ስለ ኢየሱስ ነው።ስለ ኢየሱስ ማንነትና ሥራ ያወራል።እነዚህ ነጥቦች ዋና የወንጌል ማእከላዊ ሀሳቦች ናቸው፦ ☦የኢየሱስ ሰውነት ☦የኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ☦የኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅነት ☦የኢየሱስ ክርስቶስነት ናቸው።(ሮሜ1:3-4) #ወንጌል_ለእነማን_ነው_የሚሰበከው? 👉ወንጌል ሰው ለተባለ ኹሉ አስፈላጊ መልእክት ነው።ስለዚህም "ለአሕዛብ፣ ለአይሁድ፣ለባሪያ፣ለጨዋ፣ለተማረና ላልተማረ፣ለወንድም ለሴትም" ይሰበካል።በክርስቶስ አምኖ ለዳነም ወንጌል ይሰበካል።(ሮሜ.1:14-15) “በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።”— ሮሜ 1፥16 ✍ 18/09/2015 የጌታ ዓመት

#ጳውሎስና_ወንጌሉ               (የሮሜ ጥናት 1:1-17) 🗣 በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቱን ለእነማን እንደኾነና ስለ ራሱ እንዲሁም ስለሚሰብከው ወንጌል ምንነት ከቁጥር አንድ እስከ አስራ ሰባት ድረስ ይናገራል።(1:1-17)                    #ስለ_ራሱ_ምን_አለ? #ሐዋርያ_ሊኾን_የተጠራ_መኾኑን_ይናገራል። ሐዋርያነቱን መግለጹ ለትምክህት ወይም ለጉራ ሳይኾን የሚጽፈውና የሚሰብከው ወንጌል የእርሱ አለመኾኑን ለመግለጽ ነው።ሐዋርያ ማለት በላኪው ስልጣን መልእክት ይዞ የሚላክ ማለት ነው።ስለዚህም የሐዋርያውን መልእክት አለመቀበል የላከውን ኢየሱስን አለመቀበል መኾኑ ግልጽ ነው።በዚህም ምክንያት ሁሌም ሐዋርያነቱን በማስተዋወቅ ይጀምራል።   “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፥ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።”— ሉቃስ 10፥16 #የኢየሱስ_ባሪያ_መኾኑን_ስለመግለጹ ፦ ባሪያ የጌታውን እንጂ የራሱን ፈቃድ አያደርግም።ጳውሎስም ደስ ብሎት ቢያገለግል ሽልማቱን፣ ባያገለግል ደግሞ ቅጣቱን አስቦ ተጠምዶ ማገለገሉን ያመለክታል።(1ቆሮ.9:16) ደግሞ ለጌታው ደስታ የሚሠራ፣ ሰው ያዝንብኛል ብሎ የማይፈራ መኾኑን ለማመልከት ተጠቅሞበታል።(1:1/ገላ.1:10/ቲቶ.1:1-2/2ቆሮ.4:5/ፊልጵ.1:1) ልክ እንደ ጳውሎስም ሌሎች ሐዋርያትም ራሳቸውን የኢየሱስ ባሪያዎች ብለው ጠርተዋል።የጌታ ወንድም ያእቆብ(ያዕ.1:1) ሐዋርያው ጴጥሮስ (2ጴጥ.1:1) ይሁዳ (ይሁዳ.1:1) እንደ ምሳሌ መጥቀስ እንችላለን። #የአገልግሎቱ_የትኩረት_አቅጣጫ_ምን_እንደ_ኾነ? 👉ጳውሎስ ሐዋርያ ተደርጓል።ጸጋንም ተቀብሏል።ይኼም የኾነበት ምክንያት በአሕዛብ ሁሉ ዘንድ ወንጌል በመስበክ "ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ" እንዲገኝ ነው።የወንጌል የትኩረት አቅጣጫ አለመታዘዝን መበቀል ነውና።(ሮሜ.1:5/ሮሜ.16:19/2ቆሮ.10:5-6) #ስለ_ሮሜ_ቤተክርስቲያን_የነበረው_ዐሳብ? ለረጅም ጊዜ ወደ ሮም ቤተክርስቲያን ሄዶ እንዲያገለግል ብዙ ቢጸልይም በጌታ ተከለከለ።የጳውሎስ የአገልግሎት ፍጻሜም የኾነው በሮምና በሮም ቤተክርስቲያን አገልግሎት ነበር።ይኼኛው ነበርና የጌታ እቅድ።ጳውሎስ ወደዚህች ቤተክርስቲያን ሄዶ ጸጋን ሊያካፍላቸው፣ሊጸልይላቸው፣ወንጌልን ሊሰብክላቸው ይመኝ ነበር። ✍ 17/09/2015 የጌታ ዓመት