en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
ሰዓሊተ ምህረት ወደ ፍየል ቤት የመንገድ መብራት ጥገና ተጠናቆ ርክክብ ተደረገ ባለስልጣኑ ከሰዓሊተ ምህረት ወደ ፍየል ቤት ባለው መንገድ ላይ ያሉትን መብራቶች በኤል.ኢ.ዲ የመቀየር፣ አዲስ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና ሌሎች የጥገና ስራዎችን በማከናወን ወደ አገልግሎት በማስገባት ለክ/ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና ለወረዳ አመራሮች ርክክብ አከናውኗል። ባለስልጣኑ የህብረተሰቡን የምሽት እንቅስቃሴ ምቹና ሰላማዊ ለማድረግ የመንገድ መብራት ጥገናውን በተለያዩ አካባቢዎች አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ጥገና ተከናውኖ የበሩትን የመንገድ መብራቶች ከስርቆትና ህገ-ወጥ ተግባራት ተጠብቀው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለአስተዳደር አካላት የማስረከብ ስራ እያከናወነ ይገኛል። ህብረተሰብ የመንገድ መብራት መሠረት ልማቶች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በመጠበቅና በ9101 አስተያየትና ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ባለስልጣን መ/ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል። ዘመናዊ መብራት፤ ለብሩህ አዲስ አበባ! ታህሳስ 12/2018 አ.ም ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ጽዳት በአካል ብቻ ሳይሆን በአእምሮ ውስጥ መታተም ያለበት እሴት መሆን አለበት!" አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ከአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከተማ አቀፍ በተቀናጀ የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ስርአት ዙሪያ በተማሪዎች መካከል የጥያቄና መልስ ውድድር መርሀ-ግብር አመራሮችን ጨምሮ ተማሪዎችና መምህራን፣ የፅዳት አምባሳደሮች እና አርቲስቶች በተገኙበት በድምቀት አካሂዷል። በመርሀግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ እንደገለፁት ከተማዋን የብልጽግና እና የውበት ተምሳሌት ለማድረግ “ትውልድን መቅረጽ” ላይ ያተኮረ መጠነ-ሰፊ የግንዛቤና የንቅናቄ ስራዎች እተሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል። ጃፓን የጽዳት ባህሏን የገነባችው ከተማሪዎች ጀምራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ገዛኸኝ ይህንኑ ልምድ በመቀመር በአዲስ አበባ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች “ዘውትር ዓርብ” ተማሪዎች አካባቢያቸውንና ትምህርት ቤታቸውን የሚያጸዱበት መርሃ-ግብር እየተካሄደ እንደሆነ አስረድተዋል። ጽዳት በአካል ብቻ ሳይሆን በአእምሮ ውስጥ መታተም ያለበት እሴት በመሆኑ፣ አእምሮ ላይ የመስራት ተግባር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ አቶ ገዛኻኝ አብራርተዋል። የከተማዋን ጽዳት ለመጠበቅ የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት አለመሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ ከትምህርት ቢሮ በተጨማሪ ከ12 የመንግስት ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው ከመማር ማስተማሩ ሂደት ጎን ለጎን ተማሪዎች የአካባቢ ንፅህናን የመጠበቅ ባህል እንዲያዳብሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በትምህርት ቤቶች ውስጥ የአካባቢ ንፅህና ክበባትን በማቋቋም ተማሪዎች ስለ ፅዳትና ውበት በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ም/ኃላፊው ይህ አሰራር ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ ውጤታማ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም በላይ፣ በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመቅረጽ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው አብራርተዋል። የፅዳት ግንዛቤው በትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ብቻ የሚወሰን ሳይሆን፣ ተማሪዎች ወደ መኖሪያ አካባቢያቸውና ወደ ቤተሰቦቻቸው በማሸጋገር የለውጥ ሐዋርያ እንዲሆኑ ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ም/ኃላፊው አክለው ገልፀዋል። በጥያቄና መልሱ ውድድር ላይ ከ1ኛ-3ኛ ለወጡ ትምህርት ቤቶች የዋንጫ ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ለተማሪዎች ደግሞ የትምህርት አጋዥ መፅሀፍቶችን ተሸልመዋል። ታህሳስ 12/2018 አ.ም ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በመዲናዋ በተሽከርካሪ ጎማዎች ንግድ በተሰማሩ ነጋዴዎች ላይ በተካሄደ የታክስ ኦፕሬሽን በ11 የንግድ ድርጅት ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተሸከርካሪ ጎማ በሚሸጡ የንግድ ድርጅቶች ላይ ባካሄደው የኦፕሬሽን ተግባር ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ የተገኙ 15 ግለሰቦችን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል፡፡ በዛሬው ዕለት ቢሮው ያካሄደው ድንገተኛ የኦፕሬሽን ተግባር ለረጅም ቀናት በተካሄደ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉት 15 ከፍተኛ እና መካከለኛ የመኪና ጎማ የሚሸጡ ነጋዴዎች ናቸው፡፡ ግለሰቦቹ የመንግስትን ግብር ለመሰወር ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲፈፅሙ እጅ ከፍንጅ ተገኝተው በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆናቸውን የገለፀው ቢሮው የኦፕሬሽን ተግባሩ መርካቶን ጨምሮ በተመረጡ 12 የከተማዋ የጎማ መሸጫ ቦታዎች ላይ ማከናወኑን ተገልፆል፡፡ ቢሮው የኦፕሬሽን ተግባሩን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ያካሄደ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ግለሰቦቹ በአሁኑ ወቅት የመንግሰትን ጥቅም ለማሳጣት ከግብር ህግ ጋር በተፃረረ መልኩ ያለደረሰኝ ሽያጭ በመፈፀም በተፈፀመ ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፖሊስ ተይዞ ለፍርድ የሚቀርቡ ይሆናል ብሏል፡፡ ቢሮው የኦፕሬሽን ተግባሩ በቀጣይ ቀናት በሌሎችም ዘርፎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን የንግዱ ማህበረሰብ ግብይቶችን በደረሰኝ ብቻ እንዲፈፅም ህብረተሰቡም በ7075 ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም መሰል ወንጀሎችን እንዲያጋልጥ ተጠይቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008ዓ.ምመሰረት በከተማችን የሚፈፀሙ ህገ-ወጥ ግብይቶችን የመቆጣጠር ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው እለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አስጀምረናል። ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች ናቸው። እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው። Itoophiyaa Dijitaalaa 2025 sadarkaa guutumaan guutuutti jechuun danda'amuun galma ka'ameef milkeessee xumurameea. Guyyaa har'aas Itoophiyaa Dijitaalaa 2030 ifatti jalqabsiifneerra. Qaqqabamummaa babal'isuu, lammiileef carraa walqixxee uumuu akkasumas lammiileefi dhaabbilee gidduutti waliif amanamuu gabbisuun karoorawwan ijoo bu'uraa tarsiimoo kanaati. Karoorawwan kunneen akka milkaa'anis keessumaa misooma bu'uraa dijitaalaa uummataa babal'isuu irratti hojii guddaan kan hojjetamu yoo ta'u, kunis teknooloojiin dijitaalaa namarratti xiyyeeffatee jireenya lammiilee akka fooyyessu humna guddaa ni uuma. Walumaagalatti hojiiwwan Itoophiyaa Dijitaalaatiin hojjetaman galma Mootummaan Ida'amuu biirookiraasii salphaa ta'een hojiiwwan gurguddoo dhugoomsuuf tarsiimoo keewwate waliin kan walitti hidhatanidha. Digital Ethiopia 2025 has been completed after achieving its intended goals to an almost full extent. As of today, we have officially launched Digital Ethiopia 2030. Expanding accessibility, creating equal opportunities for citizens, and strengthening trust between citizens and institutions are among the key foundational pillars of the strategy. To ensure these pillars are realized, significant efforts will be made, particularly in expanding public digital infrastructure. This will create strong capacity for digital technology, with a people-centered approach, to improve the lives of citizens. Overall, the initiatives being implemented under Digital Ethiopia are aligned with the goals of the Medemer State to realize major strategies through streamlined bureaucracy.

በስራ ተቋራጮች የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ተገመገመ ባለስልጣኑ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት ላይ በስራ ተቋራጮች አማካኝነት እያከናወነ ያለውን የፕሮጀክት ስራ አፈፃፀም ገመገመ፡፡ የግምገማ መድረኩን የመሩት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰብስብ ሁሴን የስማርትና ኖርማል ፖል አቅርቦት፣ ዝርጋታና ተከላ ለማከናወን የተያዙ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት በአጭር ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ ርክክብ እንዲያደርጉ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ሀገራችን በጀመረችው የስራ ባህል ልክ 7/24 ፕሮጀክቶችን ሰርቶና መርቶ በማጠናቀቅ ከተማችን እያስዘመገበች ያለውን ውጤታማ የስማርት ከተማ ልማት ስራ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በተጨማሪም የስራ ተቋራጮች በአጭር ቀናት ውስጥ በፕሮጀክቶች ውስጥ ቀሪ ስራዎች ማጠናቀቅ እንደሚገባቸው አሳስበው፤ ይህን ሳይወጡ በቀሩት ላይ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቀዋል፡፡ በግምገማ መድረኩ ላይ የተሳተፉ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅት ፕሮጀክቶችን አጠናቆ በተባለው አጭር ቀናት ውስጥ ለባለስልጣኑ በማስረከብ ረገድ ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል፡፡ ዘመናዊ መብራት፤ ለብሩህ አዲስ አበባ! ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ኤጀንሲው 2ሺ483 የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ሰልጣኞችን አስመረቀ የሲቨል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ኢኒሼቲቭ የሆነውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ያጠናቀቁ ከማዕከል እስከ ወረዳ የሚገኙ 2ሺ483 አመራሮች እና ባለሙያዎችን አስመርቋል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ኢኒሼቲቭ የሆነውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ሁሉም አመራር እና ሰራተኛ እንድወስድ ብዙ ተሰርቷል ያሉ ሲሆን ኤጀንሲው ባለፉት ሶስት ዓመታት በቴክኖሎጅ፣በሰውኃይል፣በአሰራር በአደረጃጀት እንዲሁም ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር ላይ ትኩረት በማድረግ የሪፎርም ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና አመራርና ሰራተኛው ከቴክኖሎጅ ጋር ያለውን ቅርበት እና ትስስር በማጎልበት ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ሚነው የጎላ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ሞላ ባስተላለፉት መልዕክት የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ዘመኑን የዋጀ እና ወቅቱን የሚመለከት የሀገራችንን ብልፅግና የሚያረጋግጥ ህዝብን ለማገልገል ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ቴክኖሎጅ አገልግሎት ማሳለጫ ነው ያሉት አቶ ተፈራ ኤጀንሲው ከነበሩበት ችግሮች በመላቀቅ እና ሪፎርም በማድረግ የተሞክሮ መቅሰሚያ ማዕከል መሆኑን ጠቅሰው ፈጠራን ታሳቢ ያደረገ አዳዲስ አሰራሮችን መዘርጋት፣ማመንጨት እና ወደላቀ ደረጃ ማሸጋገር እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡የሚጎድሉ ነገሮችን በመሙላት እና በማረም አዲስ አበባን በሁሉም ዘርፎች ግንባር ቀደም ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የኤጀንሲው አመራሮች እና ሰራተኞች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ምክትል ዋና ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ስልጠናውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ከዕለቱ የክብር እንግዶች ሰርቲፊኬት ተቀብለዋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

አዲስ አበባን እንደ ስሟ ፅዱና ውብ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ውጤት እያሳየ መሆኑ ተገለጸ የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ከተማዋን ጽዱና ውብ የማድረግ ራዕይን እውን ለማድረግ በየሳምንቱ ቅዳሜ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚያካሂደው ብሎክን መሰረት ያደረገው ሁሉን አቀፍ የፅዳት ንቅናቄ መርሃግብር በሁሉም ክ/ከተሞችና ወረዳዎች ያካሄደ ሲሆን እንደ ማዕከል በተመረጠው በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ህንድ ኤምባሲ አካባቢ በድምቀት አካሂዷል። በዚሁ ንቅናቄ ላይ ተገኝተው መልዕከት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኻኝ ዴሲሳ እንዳሉት የአዲስ አበባ ከተማን ፅዳትና ውበት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል። ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት ባለፉት አጭር ጊዜያት የከተማዋን ፅዳት ለመጠበቅ በልዩ ትኩረት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው በዚህም ቀደም ሲል ከተማዋ በፅዳት ጉድለት ትወቀስ የነበረበትን ገጽታ በመቀየር በአሁኑ ጊዜ የአካባቢ ፅዳትና የውበት ስራዎች ተቀናጅተው ውጤት ማስመዝገብ መጀመራቸውን ጠቁመዋል። ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት ፅዳትን የህብረተሰቡ ባህል የማድረግ ስራ በትውልድ ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ገዛኸኝ "ተባብረን ከሰራን አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብና ሳቢ ማድረግ እንችላለን" ሲሉም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። የአራዳ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ ኡመር በበኩላቸው የአንድ ከተማ የእድገትና የብልጽግና ትልቁ መለኪያ የፅዳትና ውበት አጠባበቅ ደረጃ መሆኑን በመገንዘብ፣ ከተማ አስተዳደሩ ለአዲስ አበባ ፅዳት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ነዋሪዎች ለፅዳት ስራው ስኬታማነት እያደረጉት ያለው ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክትጀጀ" አስተላልፈዋል። በፅዳት ንቅናቄ ስራው ላይም አመራሮችን ጨምሮ የፀጥታ አካላት፣ የፅዳት አምባሳደሮች፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች፣ የስፖርት ቤተሰቦች፣ ባለድርሻ አካላት እና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። ታህሳስ 11/2018 አ.ም ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

መዲናችን አዲስ አበባ የአለም 3ኛ የዲፕሎማሲ ማእከል እንደመሆኗ መጠን ይህን ሚናዋን በብቃት እንድትወጣና ከፍ ብላ እንድትታይ የሚያደርጋትን የዘመናዊ ከተማ ገጽታ የማላበስና ሰፋፊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ በማከናወን ረገድ ስኬታማ ስራዎች … See more

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ዛሬ ታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :- 👉ከጠዋቱ 3፡30 እስከ 7፡30 ሰዓት ሰንጋ ተራ ኢትዮጵያ መንገዶች፣ ጥቁር አንበሳ ደም ባንክ፣ኤክስትሪም ሆቴል ፣ አድዋ ሙዚየም፣ ኢትዮጵያ ስታትስቲክ ኤጀንስ፣ ቀይ ባህር ኮንዶሚኒየም 👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 9፡30 ሰዓት ኬብሮን ኢንዱስትሪ ዴድክትድ መስመር፣ ቦሌ ሁላሳ ፣ ሰበታ፣ ዓለም ገና፣ አሸዋ ሜዳ ኮንዶሚኒየም ፣ ዲያስፖራ፣ ፊሊደሮ፣ አንፎ ዓለም ባንክ ጫፍ፣ ኖህ አደባባይ ፣ ኤፍ 4 ኤፍ-6 ኖክ አደባባይ ፣ካፒታል ሲሚንቶ፣ 👉ከጠዋቱ 3፡30 እስከ 9፡30 ሰዓት ዋልያ ብረታ ብረት ዴዲኬትድ ፣ ዲማ አካባቢ ያሉ ፋብሪካዎች ፣ ተፍኪ ተጂ፣ ጀሞ-2 ኮንዶሚኒየም በከፊል ፣ ፉሪ አካባቢ እና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ስለሆነም አገልግሎቱ በጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ብሏል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager