1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
በተያዘው በጀት አመት ሁሉም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
ባለፈው አመት 6 ሚሊየን ለሚደርሱ ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ የመስጠት ተግባር የተከ… See more
ከመዲናዋ እድገት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የዲጂታል አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ነው።
ከመዲናዋ እድገት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የዲጂታል አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ መሆኑን በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ዋና ሥራ አስኪያጂ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ፡፡
ዋና ሥራ አስኪያጁ ከተማዋ በፍጥነት እያደገች መሆኗን ገልጸው ከንግድና አገልግሎት ፍላጐት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት ወቅቱ የሚጠይቀውን አሰራር መከተል ይገባል ብለዋል፡፡
ለዚህም ሰዎች አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተቋም ሳይመጡ ባሉበት ሆነው አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ ለማድረግ በወረቀት ላይ የተመሠረተውን አሰራር ወደ ዲጂታል ለማሸጋገር እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በስማርት ሲቲ ኢኒሸቲቭ የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል ለመቀየር ባለፉት 3 ዓመታት ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ኢንጂነር ወንድሙ አብራርተዋል፡፡
እስካሁን የፋይዳ መታወቂያን ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ሥራ በአጠቃላይ ከ7 ሚሊዮን 2 መቶ 6ዐ ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተመዝግበዋል፡፡
ለከተማዋ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ለንግድ እንቅስቃሴ ከሌሎች ክልሎች ለሚመጡ ዜጎችም ዲጂታል መታወቂያ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የመንግስት አገልግሎቶችን ከወረቀት ሥራ ወደ ዲጂታል ለመቀየር በጀመረው ተግባር የሲቪል ምዝገባና የዜጎች አገልግሎት የአሰራር ሥርዓቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታል በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የፋይዳ መታወቂያ ከመንግስት አገልግሎቶች ጋር የማሰተሳሰር ሥራም እየተሰራ ሲሆን፤ የትምህርት ቤት ምዝገባ ላይ አስገዳጅ እንዲሆን በማድረግ ባለፈው ዓመት ከ850 ሺህ በላይ ተማሪዎች በዲጂታል እንዲመዘገቡ ተደርጓል ብለዋል፡፡
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረትም ሁሉም የፋይናንስ ተቋማት አካውንቶቻቸውን ከዲጂታል መታወቂያ ጋር እንዲያስተሳስሩ መጠየቃቸውንና ይህም ሁለት ማንነት ይዞ የሚንቀሳቀስ ሰውን በመለየት ወንጀልን ለመካላከል እንደሚያግዝ አብራርተዋል።
የፋይዳ መታወቂያ መውሰድ በራሱ አስገዳጅ ባይሆንም አገልግሎት ለማግኘት ግን አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱን ዋና ስራ አስኪያጁ ኢንጂነር ወንድሙ አስገንዝበዋል።
ይህም ከውልደት እስከ ሞት ድረስ ማንነቱ የሚታወቅ ዜጋ ለመፍጠር የስማርት አዲስ አበባ እና የዲጂታል ኢትዮጵያን ራዕይ ለማሳካት ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
ታህሳስ 10/2018 አ.ም
AMN-Addis Media Network
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የአለምአቀፍ ተሞክሮ ምን ይመስላል? "የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በእኛ አገር በቅርብ ጊዜ ይጀመር እንጂ በሌሎች ሀገራት ከተጀመረ ቆይቷል።ከአነዚህም አንፃር ተልቅ ተሞክሮ ሊሆን የሚችለው የህንድ ተሞክሮ ነዉ። … See more
የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ "በአብይ ጉዳይ" የዜና እወጃው የፋይዳ መታወቂያ አስፈላጊነትና ከዚህም ጋር ተያይዞ ሁሉም የከተማዋ ነዋሪዎች መታወቂያው እንዲኖራቸው ምን እየተሰራ ነው በሚለውና በአዲስ አበባ ደረጃ ፋይዳ መታወቂያን ለዜጎች ለማዳረስ የተያዙ እቅዶች፣ እንዲሁም አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ፣ የፋይዳ መታወቂያ ሁሉም ዜጋ ይኑረው ሲባልስ ከዚህ አንጻር ያለው አለምአቀፍ ተሞክሮ ምን ይመስላል በሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሰጡትን ማብራሪያ በቀጣዩ ቪዲዮ ይከታተሉ።👉👉
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስፈላጊነት፡- የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ወንድሙ ሴታ
#Ethiopia
#AddisAbaba
#linkAddis
#AMN
#media
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስፈላጊነት፡- የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ወንድሙ ሴታ … See more
አዲስ አበባ፥ ወንዞቿን በማከም የውበቷ መቀነት፣ የህዝቧ ጤና በረከት በማድረግ ላይ ያለች ከተማ!
የአዲስ አበባ ወንዞች ከፍተኛ ብክለት የነበረባቸው፣ በክረምት ለጎርፍ አደጋ የሚያጋልጡ፤ ለዕይታም ለጤናም አደገኛ እንደነበሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው::
ከተማ አስተዳደራችን “ከተማን ማልማት፥ ሁለንተናዊ ልማት ነው” በሚል ተሻጋሪ እሳቤ፣ ለነዋሪው የጤና ጠንቅ፥ የከተማዋን ውበት ያጠለሹ ወንዞችን በማከም፣ ወደ ቀደመው ተፈጥሮአዊ ማንነታቸው እንዲመለሱ ከማድረግ በተጨማሪ፤ የውበተ መቀነት፥ የህዝቧ የጤና በረከት በማድረግ፣ ውብና ለነዋሪዎች ምቹ ብሎም አለም አቀፍ ተወዳዳሪና ተመራጭ የቱሪስት ከተማ እንድትሆን አድርጓል፡፡፡
በተጨማሪም ወንዞቿ፥ በወንዞች ተፋሰስ ልማት ከጤና ጠንቅነት ወደ ጤና መድህንነት ተሻግረዉ፣ ደስተኛ እና ጤናማ ማህበረሰብን በመፍጠር፣ ለነገ ጠንካራ እና አምራች ትዉልድ በመገንባት፣ ለከተማ ብሎም ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግና ድርሻ እንዲኖራቸዉ እየተከናወነ ያለዉ ስራ፣ እና የተመዘገቡ ዉጤቶች ተጨባጭ እና ህያዉ እዉነታዎች ናቸዉ፡፡
አዲስ አበባ፥ ሁሉን አቀፍ በሆኑ የልማት ስራዎቿ የቆሸሹትን እያፀዳች፥ እያስዋበች፣ እንደ ስሟ ውብ እና ማራኪ የሆነ ገጽታን ለነዋሪዎቹ ማቅረቡን ትቀጥላላች፡፡
የአለም አቀፍ ደረጃ (ISO) ሰርቲፋይድ ለመሆን ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ጋር የዉይይት መድረክ ተካሄደ።
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ተጠሪ ተቋማት ወደ ቀጣይ የተግባር ምዕራፍ ለማሻገርና ተቋማቱ የአለም አቀፍ ደረጃ (ISO) ሰርቲፋይድ ለመሆን እንዲችሉ ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ወደ ቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ለመግባት የሚያስችል የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት በዛሬዉ እለት የዉይይት መድረክ ተካሂዷል።
በዉይይት መድረኩም ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸው በምን መልኩ መመራት እንዳለበትና በተጨማሪ የሚሰጡ አገልግሎቶች ለተገልጋዮች ቀላል ቀልጣፋ እንዲሁም ምቹ ከማድረግ አንፃር ተቋማት ምን መምሰል እንዳለባቸዉ የአለም አቀፍ ደረጃ (ISO) ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ተቋም አካላት ገለፃ ተደርጓል።
በዚሁ መድረክ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ እንደገለፁት ተቋማቶች የሚሰጡትን አገልግሎቶች ጥራታቸዉንና የተገልጋዩ ፍላጎትን የሟሉ ለማድረግ እንዲሁም የሚሰጡትን አገልግሎቶች የዘመነ ለማድረግ በዚህ መልክ በቅርበት መስራተ መቻሉ በቀጣይ ተቋማቶችን ወደ ተግባር ምዕራፍ ለማስገባት አቅም የሚፈጥር እንደሆነ ገልጸዋል።
አክለውም የሚሰጡ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን ከፍ ለማድረግ በተለይም ወደዚህ የደረጃ ስርዓት በማስገባት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ አመርቂ የሆነ ለዉጥ ለማምጣት እንዲሁም የሚሰጡ አገልግሎቶች በተገልጋዩ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖራቸው በተጨማሪ ብልሹ አሰራርንም ከማስቀረት አንፃር ሚናዉ የላቀ ነዉ ሲሉ አስገንዝበዋል።
አያይዘዉም የተጀመረዉ የስራ ሂደት ሁሉም የተቋማት ሀላፊዎች ብሎም ባለሙያዎች በትኩረትና ስራዎችን በስታንዳርድ ልክ ለመስራት ብሎም የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጡን ደረጃ ከፍ ለማድረግና የተገልጋዩን እርካታ ከማረጋገጥ አንፃር በትኩረትና በቅንጅት በመስራት ወደ ቀጣይ የተግባር ምዕራፍ በፍጥነት መግባት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን የመስክ ምልከታ በማድረግ የሥራ መመሪያና አቅጣጫ ሰጡ፡፡
የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ የኢ/ር ወንድሙ ሴታ ረቡዕ ታኅሣሥ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የባለጉዳይ ቀን በባለሥልጣን ዋና መ/ቤት በመገኘት የመስክ ምልከታ በማድረግ የሥራ መመሪያና አቅጣጫ ሰጥተዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉትን የቢሮ እድሳት እንቅስቃሴ፣ የመረጃ አያያዝ፣ የውስጥ አሠራር ምን እንደሚመስልና የአገልግሎት አሰጣጥ ከተመለከቱ በኋላ ተገልጋዮች እንዴት እየተስተናገዱ እንደሆነ በሁሉም የሥራ ክፍሎች በመዘዋወር ተመልክተዋል፡፡
በተጨማሪም የባለሥልጣን መ/ቤቱን ብራንድ፣ አደረጃጀትና አጠቃላይ ገጽታን የሚያመላክት እንዲሁም የጥቆማ፣ የአስተያየት መስጫና የእርካታ ደረጃ ደሳሰ ሲስተምን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሠነድ ቀርቦ ከባለሥልጣን መ/ቤቱ አመራሮች ጋር ሰፊና ጥልቅ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፤ በዚህም አርቲፍሻል ኤንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂን በመጠቀም አሠራርን ማዘመንና በይበልጥ ተገልጋይን ማርካት በሚቻልበታ ሁኔታ የሥራ መመሪያና አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡
የባለሥልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሕይወት ሳሙኤል በበኩላቸው ኢ/ር ወንድሙ ሴታ ተቋሙን ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆን ከጎናችን ሆነው ያልተቆጠበ ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆኑን አድንቀው በዚህም በባለሥልጣን መ/ቤቱና ሠራተኛው ስም የላቀ ምስጋና አቅርበው የሰጡት ሐሳብና አስተያየቶች ገንቢና ለቀጣይ ሥራዎች ትልቅ መደላድል የሚፈጥር በመሆኑ ሁሉንም ተቀብለን ወደ ተግባር እንቀይረዋለን በማለት አስታውቀዋል፡፡
ክቡር የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ ፣ ለሕዝቦቿ ነፃነት እና ለሁለቱ ሀገራት ከጥንት እስከ ዛሬ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ክብር ላሳዩት ልባዊ ፍቅር ታላቅ ምስጋና ይገባዎታል።
ከትላንት እስከ ዛሬ የዓለም መገናኛ ብዙኃን አበይት ጉዳይ የጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አዲስ አበባ /ኢትዮዽያ ቆይታ ላይ ያተኮረ ሆኗል ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፤ በሁለቱ ጥንታዊ አገራት መካከል የነበረውን ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጡን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ደማቅ ታሪክ በመጻፋችሁ የላቀ ክብር ይሰማናል።
አዲስ አበባ በአለም አቀፍ ደረጃ አዎንታዊ ተፅእኖ ፈጣሪነቷ ፣ የአሰባሳቢ ትርክት ሀሳብ አመንጪነቷ በአለም አደባባይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
