en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
የፌደራል ኅብረት ስራ ኮሚሽንና የአዲስ አበባ ኅብረት ስራ ኮሚሽን በጋራ ዘላቂ የገጠር ትስስር በመፍጠር የገጠር ከተማ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትስስር እናረጋግጣለን በሚል መርህ የገበያ ትስስር መድረክ አዘጋጅተዋል። በመድረኩ ላይ የክብር እንግዳ የሆኑት የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ እንደተናገሩት የኦሮሚያ ክልል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በርካታ ምርቶችኝ ለከተማ አስተዳደሩ እያቀረቡ እንደሆነ ገልጸው በቀጣይም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት ምርቶችን በስፋት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው የህብረት ስራ ማህበራት የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ ሚናቸው ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል። መንግስት ካስቀመጣቸው ግቦች አንዱ የመቀነስ ግብ እንደሆነ የገለጹት ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የመሰረተ ልማት ማቅረብ፣ ማምረት እና መግዛት ዋና ዋናዎቹ መፍትሄዎች እንደሆኑ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ይህን ለማሳካት የመሰረተ ልማት አቅርቦት በማሳደግ፣ የገበያ ማዕከላትን በመገንባት እንዱሁም የሰንበት ገበያዎችን በማስፋት ለህብረት ስራ ማህበራት ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አቶ ጃንጥራር አክለውም ማህበራትን ከክልል ዩኔኖች ጋር በማስተሳሰር መጠነ ሰፊ ምርቶች ወደ ከተማችን አዲስ አበባ ማስገባት እንደተቻለ ገልጸው በቀጣይ ወራትም ህብረት ስራ ማህበራት ምርቶችን በብዛትና በጥራት ለህብረተሰቡ አንዲያቀርቡ አሳስበዋል። የአዲስ አበባ ኅብረት ስራ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ሽታየ መሀመድ በበኩላቸው በአምራችና በማህበራት መካከል የገበያ ትስስር በመፍጠር ምርቶችን በብዛት፣በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ ማቅረብ እንደተቻለ ገልጸው በቀጣይም በህብረት ስራ ማህበራት በኩል ምርቶችን በስፋት ለማቅረብ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት የ6 ወር ጉባኤውን አካሄደ። በደንብ ቁጥር 191/2017 መሠረት ''ሰብዐዊ ድጋፍ በራስ አቅም'' በሚል መርህ በክፍለ ከተማዉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት ከዚህ ቀደም የተቋቋመ ሲሆን በዛሬው እለትም ምክር ቤቱ በደንቡ መሠረት የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በተገኙበት ጉባኤዉን አካሄዷል። በጉባኤዉ ላይም የክፍለ ከተማዉ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ምስክር ነጋሽ፣የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ጥላሁን ቶላ፣ የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ተስፋዬና ሌሎችም አመራሮችና የምክር ቤቱ አባላት ተገኝተዋል። ምክር ቤቱ ባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራትንና የምክር ቤቱን አባላት ተሳትፎን በስፋት የገመገመ ሲሆን በተለይም ለድንገተኛ አደጋ የሚሆን ግብዐት ማሰባሰብና የመጋዘን ግንባታን በተመለከተ ሰፊ ዉይይት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫም አስቀምጧል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲስ አበባን እንደ ስሟ ተመራጭ፣ተወዳዳሪ፣ ፅዱ፣ውብና ለኑሮ ተስማሚ የማድረጉን ተግባር አጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉ በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ።… See more

ውጤታማ ክትትልና ድጋፍ ለተቋም እምርታ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የመሰረተ ልማትና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ በእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በየካ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የመስክ ምልከታ አደረጉ። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ በቅርንጫፋ ጽ/ቤት በመገኘት አጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የመልካም አስተዳደር ተግዳሮቶች፣ እየተሰሩ ያሉ የሕዝብ ተደራሽነት እንዲሁ የአደጋ ቅድመ መከላከልና የግንዛቤ ስራዎችን አጠቃላይ የስራ እንቅቃሴዎችን በመመልከት ክትትልና ድጋፍ አድርገዋል። ታህሳስ 14/2018 አ.ም #AAFDRMC ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanage

በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 05 የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት በመገኘት ምልከታ አካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ እንደተናገሩት ቋሚ ኮሚቴው በሚከታተላቸው አስፈጻሚ ተቋማትን በ2018 በጀት አመት በስድስት ወራት ተቋማቶች ያሉበትን የአፈጻጸም ደረጃ በሱፐርቪዥን በማየት ተገቢ የሆነ የክትትል እና የድጋፍ ስራ ለመስራት እንደሆነ ገልጸው፤ ምልከታው ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት ግልጽ፣ ቀልጣፋ ፍትሀዊና የነዋሪውን የመልካም አስተዳደር ችግር ፈቺ መሆኑን ለመከታተልና ለመደገፍ እንዲሁም ለሚያጋጥሙ ችግሮች ከአስፈፃሚው አካል ጋር በመነጋገርና ምክረ ሀሳብ በመስጠት የዋና ዋና ግቦች ሳይሸራረፉ በቀሪ ወራት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል። ቋሚ ኮሚቴው የወረዳውን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት እና በወረዳው በመገንባት ላይ ያለውን የቢሮ ማስፋፊያ ግንባታ የሰነድና የመስክ ምልከታ ያደረጉ ሲሆን አጠቃላይ በዘርፉ ያለውን የስራ እንቅስቃሴ በተመለከተ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሻረው ደፋሩ እና የወረዳ 05 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዮሴፍ ወረታው በኩል ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በምልከታው የነዋሪዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት በቴክኖሎጂ የተደገፈ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን፤ የደንበኞችን ፍላጎት ማሳደግና መለየት፣ እንዲሁም አገልግሎትን የማዘመን ሥራዎችና ከሌሎች ተቋማት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሠራር አወንታዊ ነጥቦች ያስመዘገበ መሆኑ እና ለማህበረሰቡ የሚሰጠው አገልግሎት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ከመወጣት አኳያ በቀጣይነት መደገፍና መከታተል ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው አባላት አሳስበዋል። ታህሳስ 14/2018 Bole Communication- ቦሌ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ቋሚ ኮሚቴ በሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት በመገኘት ምልከታ አደረገ። በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ቋሚ ኮሚቴ የ2ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን መሠረት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት በመገኘት ምልከታ አድርጓል። በምልከታው የአገልግሎት አሰጣጥን እና የቴክኖሎጅ አጠቃቀምን እንዲሁም የመረጃ አደረጃጀትን በማዘመን አገልግሎት አሰጣጥን ፍትሀዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ፣ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች የታዩ ሲሆን በተጨማሪም መቅርቡ ወደ አገልግሎት የገባው የተቀናጀ የሲቪል እና የነዋሪነት አገልግሎት ምዝገባ ስርዓት ሲስተም ተግባራዊ ስለመደረጉ ቋሚ ኮሚቴው ተመልክቷል። በጽ/ቤቱ የተሻለ፣ፈጣን ፣ፍትሐዊ አገልግሎት ለመስጠት እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ዙሪያ የቦሌ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ሰቦቃ ለቋሚ ኮሚቴው ገለፃ አድርገዋል፡፡ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ግዛቸው አይካ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት፣አዲሱን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባ ስርዓት ሲስተም ወደ ስራ በማስገባት በኩል እንዲሁም ምቹ የስራ አካባቢ ከመፍጠር አንፃር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልፀው ፈጣን እና ፍትሐዊ አገልግሎት በመስጠት የከተማዋን ነዋሪ የአገልግሎት እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

አዲስ አበባን ጽዱ እና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ፡፡ በዘርፉ የተጀመሩ የኢንሼቲቭ ተግባራቱ የነዋሪዉን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር ከፍተኛ አበርክቶ እየተወጡ መሆኑም ተመላቷል፡፡ #Ethiopia #AddisAbaba #linkAddis #AMN #media

አዲስን እንደ አዲስ በሚል መርህ የተጀመሩ የኢንሼቲቭ ተግባራት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በውጤት ታጅበው መቀጠላቸው ተገለፀ:: በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር በራስ አቅም በመርካቶና በተለያዩ ወረዳዎች የተሰሩ የብሎክ ስታንዳርዳይዜሽን ማስጠበቅ ስራዎችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ ሃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴዎችና አመራሮች ተዘዋውረው ጎበኙ:: በጉብኝቱ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ፣ የአዲስ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ የአዲስ አባባ ጽዳት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዘሪሁን ኮርሜ፣ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰና እንዲሁም ሌሎች የከተማ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አስተባባሪዎችና አመራሮች በመርካቶና በተለያዩ ወረዳዎች የተሰሩ የተቀናጁ የብሎክ ስታንዳርዳይዜሽን ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል:: በእለቱ መልዕክት ያስተላለፉት ኢ/ር ወንድሙ ሴታ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ የብሎክ ስታንዳርዳይዜሽን ማስጠበቅ ተግባር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቅሰው በአዲስ ከተማ የተሰራው ውጤታማ ተግባር ለሌሎችም ዓርዓያ መሆን የሚችል ድንቅ ተግባር ነው ብለዋል:: የአዲስ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው አዲስን እንደ አዲስ በሚል መርህ የተጀመሩ የኢንሼቲቭ ተግባራት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በውጤት ታጅበው መቀጠላቸው ገልፀው በራስ አቅም እየተሰራ ያለው የብሎክ ስታንዳርዳይዜሽን ተግባርን በማስፋት ለኑሮ ምቹና ስማርት ከተማን መገንባት ያስችላል ሲሉ ገልፀዋል:: የአዲስ አባባ ጽዳት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ በበኩላቸው የብሎክ ስታንዳርዳይዜሽን ማስጠበቅ ስራ አካባቢን ጽዱና ውብ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ነው ብለዋል።የጸጥታ አካላትም የብሎክ ስታንደርዳይዜሽን የጎዳና ላይ መብራት እየተተከለበት በመሆኑ የፀጥታ ስራችንን እያቀለለልን ይገኛል ሲሉ በውይይቱ የተሳተፉ የፀጥታ አካላት ተናግረዋል:: የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዘሪሁን ኮርሜ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው በራስ አቅም እየተተገበረ ያለው የስታንዳርዳይዜሽን ማስጠበቅ ተግባር ውጤታማ ሆኖ መቀጠሉን ገልፀው ስራው በሌሎች አካባቢዎችም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል:: ታህሳስ 13/2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በአዲስ አበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የአለም የነጭ ሪቫን ቀንና የኤች አይቪ ኤድስ ቀን ተከብሮ ዋለ። በጽ/ቤቱ የነጭ ሪባን እና የኤች አይቪ ኤድስ ቀን አመራሮችና ሁሉም የፅ/ቤቱ ባለሙያዎች በተገኙበት በዛሬው እለት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል። በዚሁ ወቅት በአለም ለ34ኛ ጊዜ በአገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ በመከበር ላይ ያለውን የነጭ ሪባንና የኤች አይቪ ኤድስ ቀን አስመልክቶ "ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትዉልድ ግንባታ!" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ አመጣጡን፣የሚከበርበት አላማ፣ መርሆዎችና ጽንሰ ሃሳቦች እንዲሁም ለሴቶች እኩል ተጠቃሚነት እንደ ሃገር እና በከተማም ደረጃ ምን ምን ስራዎች እንደተከናወኑ የሚገልፅ ሰነድ በፅ/ቤቱ የፀረ ሙስና ከፍተኛ ባለሙያ በአቶ አለማየሁ ሙላት እንዲሁም የኤችአይቪ ኤድስንበተመለከተ በዶ/ር እንዳለው ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። በስልጠናው ላይ በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታድሰ እንደገለፁት የነጭ ሪቫንንና የኤች አይቪ ቀንን ለተቋሙ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶች በዚህ መልክ መካሄዱ የባለሙያውን ግንዛቤ በማስፋትና የአመለካከት ለዉጦችን ለማምጣት የበለጠ አቅም ለመፍጠር የሚያስችል ነዉ ሲሉ ገልፀዋል። አክለዉም የኤችአይቪ ኤድስና የሴቶች ጥቃት መስፋፋትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንደ አገርም እንደከተማም አበረታች ጥረቶች እየተደረጉ እንዳለ ጠቁመው ይሁን እንጅ ጥረቱ ሙሉ በሙሉ ውጤታማ የሚሆነው ሁሉም አካል በሽታውን በመከላከል ረገድ በሚያመጡት የባህሪ ለውጥ ሲታገዝ ጭምር ነው ሲሉ አሳስበዋል። አያይዘዉም ሴቶች እራሳቸዉን በኢኮኖሚ በማህበራዊ እኩል በመድረግ ረገድ በከተማችን የተሰሩት ስራዎች ለዉጥ ያመጡ መሆናቸውን ጠቅሰዉ በቀጣይነትም የሴቶችን ጥቃትም በጋራ በመቃወምና ቀኑን ከማክበር ባለፈ ወደ ተግባር በመቀየር ሁሉም አካላት እንዲሁም ተቋማት ተቀራርቦ በመስራት ለዉጥ ማምጣት ያስፈልጋል ሲሉ አስገንዝበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የሰጡት ማብራሪያ | Pm … See more ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ሲጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉዳዩ ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ… See more