en
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Open in Telegram
1 474
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2130 days
Posts Archive
Urban renewal, when guided by memory, inclusion, and equity, becomes a corridor of consensus. In the case of Addis Ababa, it is a pathway through which a society reclaims its past, reimagines its present, and negotiates its collective future. It demonstrates that justice need not reside solely in courtrooms or commissions, but can also be paved into streets, planted in parks, and built into the very spaces where everyday life unfolds." #addisababa #smartcity #transformation #PMOEthiopia

የመደመር ዕሳቤ ከተሞች በስርዓት እንዲመሩ በማድረግ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ ዕድል ከፍቷል አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 18/2018 (ኢዜአ)፡- የመደመር ዕሳቤ አዲስ አበባን ጨምሮ ሁሉም ከተሞች በስርዓት እንዲመሩ በማድረግ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ ዕድል መክፈቱን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት በአዲስ አበባ በመደመር ዕሳቤ የተካሄዱ የልማት ስራዎች ነዋሪዎችን በተጨባጭ ዘላቂ ተጠቃሚ ማድረግ አስችለዋል። የመደመር ዕሳቤ ከተሞች በስርዓት እንዲመሩ ማድረግ፣ አካታች የስራ ዕድልና፣ አረንጓዴ እና ለነዋሪዎች ምቹ ከተሞችን መፍጠር የሚያስችል አቅጣጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ከለውጡ በፊት በመዲናዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ነዋሪውን በሚገባው ልክ ተጠቃሚ አለማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል። በዚሁ መነሻነት ከለውጡ በኋላ በመደመር ዕሳቤ በመዲናዋ የተከናወኑ የልማት ተግባራት ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የከተማዋን ዕድገት በተጨባጭ እያረጋገጡ መምጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡ የልማት ስራዎቹ አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና በፈጣን እድገታቸው ተጠቃሽ ከሆኑ ከተሞች ተርታ እንድትሰለፍ ማስቻላቸውንም ተናግረዋል። መዲናዋ በዲጂታል መሰረተ ልማት በመታገዝ በፕላን የምትመራ፣ ሁሉን አቀፍ አገልግሎት መስጠት የምትችል፣ የአየር ንብረት ተጋላጭነቷ ዝቅተኛና አካታች እንድትሆን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በመደመር ዕሳቤ የመዲናዋን ደረጃ ማሳደግ በመቻሉ ዜጎች የተሻለ ኑሮ እንዲኖራቸው ለማድረግ ተችሏል ነው ያሉት። መዲናዋን ስማርት ሲቲ ከማድረግ አንፃርም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ከመገንባት ጀምሮ ስኬታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ነው የጠቀሱት። በዚህም ጽዱ፣ ውብና አረንጓዴ ከተማ መገንባት መቻሉን ጠቅሰው፤ የመደመር ዕሳቤ ከተሞች ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ መንገድ መክፈቱን አንስተዋል። በቀጣይም ዘመናዊና ሁሉንም ያሟላች ከተማ ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

ከመንገድ መብራት ጋር ተያይዞ ይነሱ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ መሆኑ ተገለፀ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከመንገድ መብራት ጥገና ጋር ተያይዞ ይቀርቡ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ምላሽ እያገኙ መሆኑን የባለስልጣኑ ኦፕሬሽንና ጥገና ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ እንከንየለሽ አለሙ ገለጹ፡፡ ወ/ሮ እንከንየለሽ በክፍለ ከተማው የተከናወኑ የመንገድ መብራት ጥገና ስራዎችን ከአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ጉብኝተዋል፡፡ ባለስልጣኑ በክፍለ ከተማው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ የመንገድ መብራቶች ላይ ጥገና እና የመሰረተ-ልማት የማሟላት ስራ በማከናወን ከጭለማ ወደ ብርሀን ማምጣት መቻሉን ም/ዋና ዳይሬክተሯ በተደረገ ማጠቃለያ ውይይት ላይ ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የመንገድ መብራቶቹ ተጠግነው ለህብረተሰቡ አገልግሎት ማብቃት መቻሉ፤ ጨለማን ተገን በማድረግ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን በመከላከልና ለእግረኛና ተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ብሩህ፣ ምቹና ሰላማዊ ማድረግ እንዳስቻለ አንስተዋል፡፡ በተጨማሪም ከተማዋን እንደ ስሟ አዲስ፣ ውብና ማራኪ ማድረግና የንግዱ ማህበረሰብ አገልግሎቱን ለህብረተሰቡ ምሽቱንም ጨምሮ እንዲያቀርብ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በክፍለ ከተማው ከሰባ ሁለት ወደ ሃያት አደባባይ፣ ከሰሚት ኮንዶሚኒየም 2ኛ በር - መስቀለኛ፣ ሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ ሰሚት ኮንዶሚኒየም እሳት አደጋ፣ 72 መስቀለኛ መንገድ ቡና ቦርድ፣ከ ሲኤምሲ ሚካኤል - ፊጋ፣ ከሰሚት ኮንዶሚኒየም - 3ኛ በር፣ ከሰሚት አደባባይ - ለሚ አደባባይና በሌሎችም በርካታ መንገዶች ላይ ያሉትን የመንገድ መብራቶች በመጠገን ብርሀን ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ ዘመናዊ መብራት፤ ለብሩህ አዲስ አበባ! ታህሳስ 18/2018 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ለከተማዋ ነዋሪዎች የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት ያስችል ዘንድ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጅ ለማዘመን ከማእከል እስከ ወረዳ ድ… See more

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመሠረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ ር ግዛቸው አይካና አባላቱ ጋር በመሆን በቅርቡ ሥራ የጀመረውና ለሃገሪቱ የመጀመርያ #የተቀናጀ_የወሳኝ_ኩነት_ምዝገባ ስርዓትን ያካተተው #የCivil_Registration_and_Vital_Statistics ID ሲስተም አሰራር ያለበትን ደረጃ እየተመለከቱ ይገኛሉ። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ በጉብኝታቸው ይህ #የቴክኖሎጂ_መስረት_ልማት ዝርጋታ በከተማው አገልግሎት ላይ እየፈጠረ ያለውን ከፍተኛ ጫና እና መስተጓጓል ለመቅረፍ እና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ወሳኝ ግብአት ሆኖ ያገለግላል ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። Gizachew Ayka Albe የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council

ለመዲናችን ነዋሪዎች በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽነትና ፍትሀዊነትን የተላበሱ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አመርቂ ውጤት የተመዘገባባቸውና ተጠናክሮ ሊቀጥሉ የሚገባቸው ናቸው ሲሉ የመሠረተ ልማትና የማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ አስገነዘቡ። የአዲስ አበባ ከተማ ም/ ቤት የመሠረተ ልማትና የማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ ይህን ያስገነዘቡት በትናንትናው እለት ህዳር 16/2018 አ.ም ቋሚ ኮሚቴው ላለፉት ቀናት በስራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና ተጠሪ ተቋማቱ ያካሄዱትን የ6 ወራት የስራ አፈጻጸም የመስክ ምልከታ አጠናቀው ግብረ መልስ በሰጡበት ወቅት ነው። በዚሁ መድረክ ላይ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታና የጽ/ቤቱ አመራሮች፣ የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና የከፍለ ከተማና የወረዳ መዋቅሮች የተገኙ ሲሆን የምክርቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና አባላቱ የመስክ ምልከታ ሪፖርትና ግብረ መልሳቸውን አቅርበው ውይይት ከተካሄደበት በሁዋላ የጋር ተደርጓል። በመድረኩም የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢው ዶ/ር ግዛቸው አይካ እንደተናገሩት ቋሚ ኮሚቴው ለጽ/ቤቱ ተጠሪ በሆኑት የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ፣የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፣ የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን፣በፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲና በአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያለፉት 6 ወራት አገልግሎት አሰጣጥና ሌሎች የስራ እንቅስቃሴዎች ላይ ባካሄድነው የመስክ ምልከታ በተቋማቱ የነዋሪውን የመልካም አስተዳደር ችግር ፈቺ የሆኑ ተግባራት መከናወኑን ተገንዝበናል ብለዋል። አክለዉም በተቋማቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱ በቴክኖሎጅ መዘመኑ፣ሥራዎችን ከሌሎች ተቋማት ጋር ተናባቢ በሆነ መልኩና ቅንጅታዊ አሠራርን ባጠናከረ መልኩ በመፈጸሙ እምርታዉ ለዉጥ ማምጣት የተቻለበት ስራ መሠራቱን ገልፀዉ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ስሉጥ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በማረጋገጥ ረገድ የመጣዉን ለዉጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዚሁ መድረክ ላይ ባለፋት ስድስት ወራት በሁሉም ተጠሪ ተቋማቶቻችን ሰፋፊ ስራዎች የተከናወኑበት ነው ሲሉ ገልጸው እነዚህም በተለይም ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ከህብረተሰቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት የቻልንበት፣ የምንሰጣቸውን አገልግሎቶች በይበልጥ ከቴክኖሎጂ ጋር አስተሳስረን ማዘመን የቻልንበትና በዚህም እምርታዊ ለውጥ ያመጣንበት ነው ሲሉ አመልክተዋል። አክለዉም የከተማዋን ፅዳት ከፍ ወዳለ ደረጃ በማድረስ ረገድ፣የመንገድ ዳር መብራት መሠረተ ልማት ዝርጋታን ከማስፋፋት እንዲሁም የቅድመ አደጋ መከላከል ስርአትን ከማጠናከርና የአደጋ ጊዜ ስጋትን ከመቀነስ አ እና የሲቪል ምዝገባ የአገልግሎት አሰጣጥን ወደ አዲስ ምእራፍ ከማሸጋገር አንጻር አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። በመጨረሻም በቀጣይ የበጀት አመቱ ቀሪ ስድስት ወራት ቅንጅታዊ አሰራርን በይበልጥ በማጠናከርና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትን በዲጂታል ቴክኖሎጅ የማስደገፍ ስራዎችን በማጎልበት ለስሉጥ ከተማ የሚመጥን ስሉጥ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ስኬት በሁሉም ተጠሪ ተቋማትና በስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት ልዩ የትኩረትና የርብርብ ማእከል በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ለቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢውና አባላት ተገልጾላቸዋል። Gizachew Ayka Albe የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የመሠረተ ልማትና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ.ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካና የቋሚ ኮሚቴው አባላት ከአዲስ አበባ ከተማ የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰብስብ ሁሴን ጋር በመሆን #በኮሊደር_ልማት ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል #የዘመናዊ_መንገድ_መብራት ሥራዎች ያሉበትን ሁኔታ የመስክ ምልከታ አካሄዷል። Gizachew Ayka Albe የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የመሠረተ_ልማትና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ የተመራው የቋሚ ኮሚቴ አባላት ቡድን በዛሬው እለት #በአዲስ_አበባ_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት #የምዕራብ_ቅርንጫፍ በመገኘት በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጡን እና የቀላል ኃይል ማስተላለፊያ ምሶሶዎች ያሉበት ሁኔታ ላይ የመስክ ምልከታ አካሄዷል። Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት Gizachew Ayka Albe የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት Addis Ababa City Council

ዘመናዊ አገልግሎት፣ ዘመናዊ አገልጋይ፣ ዘመናዊ ተገልጋይ: አዲስ አበባ ከተማችን አዲስ አበባ ዘመናዊ የአገልግሎት ማዕከል እየሆነች ትገኛለች! በከተማችን ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው አንኳር የህዝብ ጥያቄዎች መካከል የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተጠቃሽ ነው። የችግሩን ውስብስብነት በጥልቀት በመረዳት መሰረታዊ መፍትሄ ለመስጠትም ተቋማዊ ሪፎርምን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች ተወስደዋል ፤ ብዙ ቢቀረንም ተጨባጭ ውጤቶችም መመዝገብ ጀምረዋል። ተቋማትን በአሰራር ፣ በአደረጃጀት ለማጠናከር ከሚደረጉ ጥረቶች በተጨማሪ በስነ ምግባሩ የተመሰገነ ስራውን በእውቀት እና በክህሎት የሚከውን የሰው ሀይል ለመገንባት ብርቱ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ:: ለሰራተኞች ምቹ የስራ ከባቢ ለመፍጠር በየተቋማቱ አበረታች ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን በየጊዜው የደመወዝ ማስተካከያዎች እየተደረጉ መሆናቸውም አይዘነጋም። አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተጀማመሩ ተግባራትም በሲቪል ምዝገባ እና በነዋሪዎች አገልግሎት እንዲሁም በሌሎችም ተቋማት የነበሩ ውስብስብ ችግሮች ማቃለል ችለዋል። በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ እመርታዊ ለውጥ ለማስመዝገብ እንደ ሀገርም መተግበር ከጀመሩ አዳዲስ አሰራሮች መካከል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ ነው። የፌዴራል እና የከተማችን ተቋማት አገልግሎታቸውን በተቀናጀ መልኩ እንዲሰጡ የሚያስችለው ሞሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የጊዜ እና የሀብት ብክነትን እያቃለለ ይገኛል። በከተማችን በአራዳ ክ/ከተማ ከሚገኘው ዋናው የሞሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተጨማሪ በቦሌ ክፍለ ከተማ በተገነባው ሞሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቅ/ፅ/ቤት ከሁሉም የከተማችን አካባቢዎች ለሚመጡ ተገልጋዮች ስታንዳርዱን የጠበቀ ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በሌሎች ክ/ከተሞችም ለማስፋት ብርቱ ጥረቶች ተጀምረዋል። በአመራሩም በባለሙያውም ዘንድ የተሟላ አቅም በመገንባት የአገልጋይነት መንፈስን ለማሳደግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት ባሻገር ልግመኝነትን እና ሌብነትን ለመተጋገል በፓርቲ አቅም የተጀማመሩ ስራዎችም ይበልጥ ተጠናክረው ይቀጥላሉ። አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ በማዘመን የህዝባችን እርካታ ለማሳደግ እንትጋ! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት #aa_prosperity #smart_addis_ababa #linkaddis #Ethiopia #addisababa #serviceexcellence

አስተዳደሩ ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ ነው አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲጂታል ማንነትን መሰረት ያደረገ ዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት እየዘረጋ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት፤ ዲጂታል 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መገንባት ቁልፍ የስትራቴጂው ግቦች እንደሆኑ አስረድተዋል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ አስተዳደሩ የሚሰጣቸው የመንግስት አገልግሎቶች ሙሉ ለሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ነው። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በፈጠረው መደላድልም ተቋማትን የማገናኝትና እንዲናበቡ የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማዘጋጀትም የተገልጋዩን የአገልግሎት እርካታ ማሳደግ የሚያስችል አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን አብራርተዋል። በመሆኑም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በመዲናዋ በሁሉም ተቋማት ዲጂታል ማንነትን ማሰረት ያደረጉ አገልግሎቶች የሚሰጡበት የተሟላ ስርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ነው የገለጹት። ከተማ አስተዳደሩ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አኳያ ራሱን በመቃኘት የነዋሪዎችን የዲጂታል መታወቂያ መረጃን የማዋሀድ ስራ እንደሚሰራም ነው የጠቀሱት። በመዲናዋ የተለያዩ ተቋማት በሚሰጡ የኤሌክትሮኒክ አገልግሎቶች ነዋሪው ባለበት ሆኖ የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ በማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው የገለጹት። በዋናነትም የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎትም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር እንዲያያዝ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት መደላድል መፈጠሩን አብራርተዋል። የስማርት ሲቲ መገለጫ ዲጂታል አገልግሎትን በተሟላ መልኩ መስጠት ነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ የነዋሪነትና የሲቪል ምዝገባ ስርዓቱ ፍትሐዊ፣ ተጠያቂነት ያለበት፣ ተደራሽና ዘመናዊ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠናቀቂያ በአጠቃላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሙሉ ለሙሉ የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ ይደረጋል ነው ያሉት። የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታል እንዲሆኑ መደረጉ ብልሹ አሰራርን ለማስቀረትና ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑንም አንስተዋል። #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ