en
Feedback
SCHOOL OF INDIANA (JEMO BRANCH)

SCHOOL OF INDIANA (JEMO BRANCH)

Open in Telegram

What We Do School Matters empowers schools and districts to build capacity and reach desired results through evidence-based practices, collaboration, and continuous improvement.   We provide customized support in five key areas that advance learning:

Show more
1 412
Subscribers
-124 hours
+37 days
-830 days
Posts Archive
photo content
+1

ክቡራን የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ:- የትምህርት ቤታችን የስፖርት ክበብ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመኑን የስራ ክንውን እጅግ ደማቅ በሆነ መልኩ ዛሬ አጠናቋል! ክበቡ ዓመታዊ የስራ እንቅስቃሴውን ለማጠቃለል ባዘጋጀው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ፣ ተማሪዎች እና የት/ቤቱ ሠራተኞች የተሳተፈበት የማስ ስፖርት (Mass Sport) እቅስቃሴ እና የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮችን ያካሄደ ሲሆን የመርሃ ግብሩን አጠቃላይ ሁኔታ ፎቶግራፎች ከታች እንዲመለከቱ እንጋብዛለን። የስፖርት ክበቡ በዓመቱ ውስጥ ለነበረው ስኬት አብራችሁን ለነበራችሁና ድጋፍ ላደረጋችሁልን በሙሉ ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል!                     የስፖርት ክበብ!

የማክበር ሰላምታችን እያቀረብን ትምህርት ቤታችን የተማሪዎችን ቁጥር ተመጣጣኝ አድርጎ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለመስጠት እንዲያስችለው፣አዲስ ጀማሪ እህት/ወንድም ያላቸውን ተማሪዎች አስቀድሞ የመለየት ስር ይሰራል፡፡ በመሆኑም፣ ለ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቅድመ አንደኛ (ኬጂ) ተመዝጋቢ ተማሪዎች ያሏችሁ ወላጆች ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link) በመጠቀም (ጀሞ 1 ከለላ ህንጻ 2ኛ ፎቅ በሚገነው የት/ቤቱ ፋይናንስ ቢሮ በመሄድ) አስፈላጊውን መረጃ በመስጠት ቅድመ ምዝገባ እንድታከናውኑ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ቅፁን መሙላት የሚችሉት በተቋማችን እየተማሩ ያሉ ወንድም/እህት ያላቸው ተማሪዎች ወላጆች ብቻ ናቸው፡፡ ማሳሰቢያ፡- ዋናው ምዝገባ ከመድረሱ በፊት የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች እንዲያሟሉ አደራ እያልን በምዝገባ ወቅት የተሟላ መረጃ ያላቀረቡ ወላጆችን የማናስተናግድ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ 👉የልደት ሰርተፍኬት (ከወሳኝ ኩነት ቢሮ የሚሰጥ መሆን አለበት) 👉የክትባት ካርድ 👉ሁለት የተማሪው/ዋ ጉርድ ፎቶ 👉የወላጆች አንድ ፎቶ (የእናት አንድ የአባት አንድ)https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfq8oKHcKilYFL_a0CGGnp3BgH8uCO9pzpfiuoPP8RwHFwIqQ/viewform?usp=sharing&ouid=104627125276150953700

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ የት/ቤታችን ማህበረሰብ እንኳን ለ1447ኛው ሂጅራ የኢድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ እያልን፤በዓሉ ከቤተሰቦቻችሁ እና ከወዳጅ ዘመዶቻ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ የት/ቤታችን ማህበረሰብ እንኳን ለ1447ኛው ሂጅራ የኢድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ እያልን፤በዓሉ ከቤተሰቦቻችሁ እና ከወዳጅ ዘመዶቻችሁ ጋር የደስታ፣ የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።                          የት/ቤቱ!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡ (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡     (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡   በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና  ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡     ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199  የመፈተኛ ጣቢያዎች  እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች  ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡     ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc