en
Feedback
VGM Ethio

VGM Ethio

Open in Telegram

ስኬታማ ሰዎች አጋጣሚዎችን አይጠብቁም፣ አጋጣሚዎችን እራሳቸው ይፈጥራሉ እንጂ!

Show more
1 686
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5030 days
Posts Archive
sticker.webp0.03 KB

photo content

sticker.webp0.03 KB

photo content
+1

sticker.webp0.03 KB

ጡፈይል ኢብን ዓምር (ረዐ) ጡፈይል ኢብን ዓምር (ረዐ) አንቱ የተባለ ገጣሚ ሲሆን በየመን የሚገኝ የደውስ ጎሳ መሪም ጭምር ነበር። በሆነ ወቅት ወደ መካ እየሄደ ሳለ ቁረይሽ መንገድ ላይ አግኝተውት እንዲህ ሲሉ መከሩት፦ "ጡፈይል ሆይ! ወደ ሀገራችን መተሀል። ሙሐመድ በርትቶብናል፤ ህብረታችንን በታትኖታል፣ ዓላማችንን ለያይቶታል። ንግግሩ እንደድግምት ነው። አባትን ከልጅ፣ ወንድምን ከወንድም፣ ሚስትን ከባል ይነጣጥላል። በእኛ ላይ የደረሰው በላዕ በአንተ እና በወገኖችህ ላይ እንዳይደርስ ተጠንቀቀው። አታናግረው፣ ከርሱም ምንም ነገር እንዳትሰማ።" ጡፈይል እንዲህ ሲል አውስቷል፦ "በአላህ ይሁንብኝ በጣም ስላስፈራሩኝ ከርሱ (ከሙሐመድ) ምንም ነገር ላለመስማት ወሰንኩ። ወደ ተቀደሰው መስጂድም ስሄድ ምናልባት ድንገት ቃላቶቹ ጆሮዬ እንዳይገቡ በመስጋት ጆሮዬን በጥጥ ደፈንኩት። ማልጄ ወደ መስጂድ ስሄድ ካዕባህ ዘንድ ቆሞ ሲሰግድ አየሁት። ሳልፈልግ የሚያነበንበው ነገር ጆሮዬ ገባ። አላህ በጥቂቱ እንድሰማ አደረገኝ። የሰማሁት ውብ ነው። በራሴም በአላህም እምላለሁ! የተዋጣልኝ ገጣሚ ነኝ። ጥሩና ክፉውንም መለየት እችላለሁ። ይህ ሰው የሚናገረውን እንዳልሰማ የሚከለክለኝ ነገር የለም። ጥሩ ከሆነ እቀበለዋለሁ፥ መጥፎ ከሆነ ደግሞ እተወዋለሁ። ወደቤቱ ሲሄድ ጠብቄ ተከተልኩት እና ቤቱ ሲገባ ተከትዬው ገባሁ። ሰዎች ምን ያህል እንድጠነቀቀው እንዳስፈራሩኝ፣ በዚህም የተነሳ ወሬውን ላለመስማት ጆሮዬ በጥጥ መድፈኔን፣ ሳልወድ በግድ ከሚያነበንበው ጥቂቱን እንደሰማው፥ አጫወትኩት። ጉዳይህን ንገረኝ አልኩት። እስልምናን አብራራልኝ፥ ቁርዓንም አነበበልኝ። በአላህ እምላለሁ ከዚህ ይበልጥ ያማረ ቃል፣ ከዚህ የበለጠ እውነተኛ መልዕክት ሰምቼ አላውቅም። ወዲያው እስልምናን ተቀበልኩ። በወገኖቼ ዘንድ ተሰሚነት ያለኝ ሰው ነኝ። አሁን ወደዛው እመለስና ወደ እስልምና እጠራቸዋለሁ። አላህ አንዳች ተዓምር ይሰጠኝ ዘንድ ዱዓ አድርግልኝ አልኩት እና ዱዓ አደረገልኝ።" አላህም በጡፈይል ፊት ላይ የሚያበራ ብርሃን አደረገለት። ጡፈይልም እንዲህ አለ፦ "ህዝቦቼ፥ ይህ መርገምት ነው ስለሚሉ ሌላ ቦታ ላይ እንዲያደርግልኝ አላህን ተማፀንኩት። ብርሃኑንም አለንጋዬ ላይ አደረገልኝ።" ከዛ ቡኃላ ጡፈይል ወደ ህዝቦቹ ተመልሶ የሐዲስ ሊቁን አቡ ሁረይራህን (ረዐ) ጨምሮ በርካታ ሰዎችን እስልምናን እንዲቀበሉ ሰበብ ሆኗል። የኢስላም ጠላት ቁረይሾች በቅጥፈት የጥላቻ መርዝ በመርጨት እስልምናን ለማጥፋት ቢሞክሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። ጡፈይልንም በቅጥፈት ከኢስላም ሊያርቁት ቢሞክሩም ከመስለም ግን ሊያስቆሙት አልቻሉም። በዚህ ዘመንም በውጭም በሀገራችንም የኢስላም ጠላቶች እስልምናን ጥላሸት ለመቀባት የማይቀጣጥፉት ቅጥፈት፣ የማያወሩት ተረት የለም። ግና ይህ የኢስላም ጠላቶች ድርጊት ብዙዎች ስለእስልምና እውነታውን እንዲመረምሩ ሰበብ እየሆነ ነው። በመሆኑም በሚገርም ፍጥነት እስልምና በመላው ዓለም እየተስፋፋ ነው። يُرِيدُونَ أَن يُطْفِئُوا نُورَ اللَّهِ بِأَفْوَاهِهِمْ وَيَأْبَى اللَّهُ إِلَّا أَن يُتِمَّ نُورَهُ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ [ ሱረቱ አል-ተውባህ - 32 ] የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ለማጥፋት ይፈልጋሉ፡፡ አላህም ከሓዲዎች ቢጠሉም እንኳ ብርሃኑን መሙላትን እንጅ ሌላን አይሻም፡፡ https://t.me/Zelebet

sticker.webp0.03 KB

photo content

sticker.webp0.03 KB

sticker.webp0.03 KB

sticker.webp0.03 KB

photo content

sticker.webp0.03 KB

sticker.webp0.03 KB

photo content

ሙፍቲ የዛሬ ሶስት ዓመት ለስድስት ወር ብቻ የሚቆይ የመጅሊስ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙ ያደረጉትን ንግግር ስሙት። መጅሊሱ ጥሩ አስተዳዳሪ አግኝቶ እንደማያውቅና የዘራፊ ቤት እንደነበር ነው በአጭሩ የገለፁት። እንደሚያሻሽሉት የገቧቸው ቃሎችም አሉ። የኛ ጥያቄ (1) የተሰጣቸው ስድስት ወር አልቆ የግል ርስታቸው አድርገውት በህገወጥ መንገድ ከመንግስት ጋር በመመሳጠር ለሶስት ዓመታት ያህል በመጅሊስ ፈላጭ ቆራጭነት ሲቆዩ አሻሽለዋለሁ ብለው የገቡትን ቃል አንዱን እንኳን ፈፅመዋል ወይ? የገቢ ምንጭ እንፈጥርለታለን፣ ብዙ ቦታዎች አሉ እናለማቸዋለን ብለው ቃል ገብተው ነበር። በቃላቸው መሰረት ያለሙት ቦታ አለ ወይ? ሌላው ቢቀር አዲስአበባ መጅሊሱ ከታከለ ዑማ ላይ የወሰደውን አፍሪካ ህብረት ጋር ያለውን መሬት አዲስ አበባ መጅሊስ እንዳያለማው እንኳን እንቅፋት የሆነው እና እስካሁን የታቀደው ሳይሰራበት የቀረው በሙፍቲ በጥባጭነት አይደለም ወይ? ከቀብን ቦታ ጅብ አስከሬን እያወጣ ሲበላስ ምን ፈየዱ? እንደሚመለከተው ተቋም ምንስ ለማድረግ ሞከሩ? የክልልም ሆነ የአዲስአበባ መጅሊሶች ላይ ጣልቃ እየገባ አላሰራ ያለውስ የሳቸው በጥባጭነት አይደለም ወይ? እንኳን ሊያለሙ ሌላው እንዲያለማ እንኳን መች ፈቀዱለት? የኛ ጥያቄ (2) መጅሊሱ የዘራፊ ቤት እንደነበር ተናግረዋል። ለውጡ አውጥቶ የጣላቸውን በሙስና እና በዝርፊያ የተጨማለቁ የቀድሞ መጅሊስ ሰዎችን እነዑመር ኮምቦልቻን መልሶ ያመጧቸውና መጅሊስ ውስጥ እንዲሰገሰጉ ያደረጓቸው ሙፍቲ አይደሉም ወይ? ከቀድሞው መጀሊስ በሙስና የተባረረውን የፋይናንስ ክፍል ኃላፊ አቶ ኑርሑሴን ካሣሁንን መልሰው ሥራ አስኪያጅ አድርገው የሾሙት ሙፍቲ አይደሉም ወይ? ፍቃድ ባላቸው ገለልተኛ ኦዲተሮች የተሠራውን የኦዲት ሪፖርት ❝ጅብሪልም ቢመጣ አልቀበልም❞ ብለው ሥርቆቱ ሁሉ ተሸፋፍኖ እንዲቀር ያደረጉት ሙፍቲ አይደሉም ወይ? ታድያ ዘራፊ ብለው ከሰየሟቸው የቀድሞ መጅሊስ አመራሮችበምን ተሻሉ? ሰሞኑ የተካሄደው የመጅሊስ ለውጥ እንኳን ከሐጅ ቡኃላ እንዲሆን እንዲያስደርግላቸው መንግስትን ሲማፀኑ የነበረው ምን ስላሰቡ ነው? ከሑጃጆች የሚሰበሰበውን ብር የተለመደውን ዝርፊያ ለማካሄድ እንጂ ሌላ ምን የተለየ ኖሮት ነው? 46 ዓመታት ከቆዩበት መጅሊስ ስልጣን ላለመውረድ ሰው እስኪታዘባቸው ድረስ የታገሉት እና በ90 ዓመታቸው እንደጎረምሳ "ድም እንፋሰሳታለን" እስከማለት የደረሱት የዘራፊ ቤት ብለው የገለፁት መጅሊስ ምን ያህል ቢደላቸው ነው? ቪድዮውን በዚህ ሊንክ https://t.me/Zelebet/2186