VGM Ethio
Open in Telegram
1 686
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5030 days
Posts Archive
1 686
Repost from የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
በዱራሜው መስጅድና በጥቅሉ በገጠሩ የሀገራችን ክፍል ህዝባችንን ከአክፍሮተ ሀይላት በመከላከሉ ረገድ ኡስታዝ አቡ ሐይደር ስለሚሰራቸው ፕሮጀክቶች ከሀሩን ሚዲያ ጋር ያደረገውን ቆይታ ተከታተልኩት። በቆይታው በተለይ በገጠሩ ክፍል መሠራት ስላለባቸው ስራዎች አጽንኦት ሰጥቶ ተናግሯል። በግሉም የከተማ ዳዕዋ ከሞላ ጎደል እንዳቆመና ትኩረቱን ገጠር ላይ እንዳደረገ ገልጿል። የከተማው ሰው ከሶሻል ሚዲያ ጀምሮ እስከ ሳተላይት ቴሌቭዥን ድረስ በቂ አማራጮች ስላሉት ዳዕዋው ያልደረሰበት ቦታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚያስፈልግ መክሯል።
..
እውነት ለመናገር ኡስታዝን በቅርበት እንደማወቄ መናገር የምችለው ነገር ባለፉት ሶስት አመታት በገጠሩ የሰራቸው ስራዎች በቃላት የሚገለጹ አለመሆኑን ነው። በተፈጥሮው የሰራውን ማውራትና ያደረገው እንዲነገርለት ስለማይፈልግ እንጅ ለብዙ አካል አርአያ መሆን የሚችሉ ስራዎችን ሰርቷል። ኡስታዝ ዳዕዋየን ገጠር አድርጌያለሁ ሳይሆን ኑሮየን ገጠር አድርጌያለሁ ቢል ይቀለዋል። በስራዎቼ ዙሪያ ብዙ እንድል ስለማያስፈልግ በመጠኑ ይህንን ካልኩ የመጨረሻ መልዕክቴን ግን ላስተላልፍ፦
..
በገጠሩ ስለሚሰሩ የዳዕዋና የአክፍሮተ ሀይላት ስራዎች በሱ በኩል የያዛቸውን ፕሮጀክቶች መደገፍ እጅግ በጣም ብዙ ለውጥ የሚፈጥር እርምጃ ነው። ሁላችንም በአቅማችን ልክ በተለይም ከሰሞኑ በጀመረው በተለያዩ አካባቢዎች ኡስታዞችን የመቅጠር ስራ ላይ እንገዘው፤ አትጠራጠሩ በርካታ ፍሬዎችን ከአመታት በኃላ በአሏህ ﷻ ፍቃድ የምታዩበት ፕሮጀክት ነው።
..
ቪዲዮውን ለማየት
https://youtu.be/PaVK-x2GFw4
የኡስታዝ አቡ ሐይደር አካውንት፦
1. COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA
1000317507589
SADIK MOHAMMED AHMED
2. ABYSSINIA BANK
83047178
SADIK MOHAMMED AHMED
3. ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645
SADIK MOHAMMED AHMED
ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ መደወል ትችላላችሁ
0911103231
___
© የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://t.me/+A9f1rDgYDRYzYTY0
1 686
የጎንደር ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳይ ምክርቤት ሚያዝያ 18/2014 በጎንደር ሙስሊሞች ላይ የተፈጸመው የሽብር ጥቃት አስመልክቶ የፍትሕ ሚንስቴር በ7/11/2014 ባቀረበው የሪፖርት ውጤት ላይ በመቃወም የቅሬታ ደብዳቤ ለፍትሕ ሚኒስቴሩ ጽሕፈት ቤት ጻፈ። የደብዳቤው ግልባጭ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ቤት፣ ለሰላም ሚኒስቴር፣ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት፣ እና ለአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ተልኳል።
የከተማዋ እስልምና ጉዳይ ምክርቤት የፍትሕ ሚኒስቴር በጎንደር ሙስሊሞች ላይ ስለተፈጸመው አስነዋሪ ጥቃት አስመልክቶ ባቀረበው ሪፖርት ላይ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ቅሬታ እንዳለው ማብራሪያ እንዲሰጠው ጠይቋል:-
1) በጎንደር ሙስሊሞች ህይወት፣ መስጊዶች እና ንብረት የደረሰው ውድመት ጥቃት ብሎ በመግለጽ አሳንሶ ማየቱ።
የፍትሕ ሚኒስቴሩ በዚህ ራሱ ባቀረበው ሪፖርት ላይ 11 መስጊዶች መጎዳታቸው፣ 20 ዜጎች መገደላቸውን እና ከፍተኛ ንብረት መውደሙ ተጠቅሷል ። ሆኖም ግን ይህ በዚህ መጠን ያክል በሰዎች ህይወት እና በንብረት ላይ ውድመት የደረሰበት ድርጊት የፍትሕ ሚኒስቴር "ጥቃት" ብሎ አሳንሶ ማየቱ ቅር አስብሏል።
2) በወቅቱ በንግድ ቦታዎች ላይ የተፈጸመው ጥቃት በሙስሊሞች የንግድ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበረ እየታዋቀ ሪፖርቱ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ንግድ ቦታዎች ላይ በሙስሊሞች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተደርጎ ተጠቅሷል። ምክርቤቱ ይህ በፍትሕ ሚኒስቴሩ ሪፖርት ላይ የተጠቀሰው ድርጊት በየትኛው ክ/ከተማ፣ ወረዳ እና ቀበሌ እንደተፈጸመ ንብረት ወደመባቸው የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነጋዴዎች ስም እንዲጠቀስ ጠይቋል።
3) ፍትሕ ሚኒስቴሩ በሪፖርቱ ላይ ካካተታቸው በወቅቱ በሌሎች የአገሪቱን አካባቢዎች የደረሱት ከሃይማኖትና እና ከብሄር ጋር የተያያዙ ጥቃቶች ያቀረበበት ዘርዘር ያለ አቀራረብ በጎንደር ሙስሊሞች የደረሰው ውድመት ለማቅረብ አልተከተለውም።
✔️በጎንደር ሙስሊሞች ጥቃት ያደረሱትን አካላት እና ጥቃት ለማድረስ የተጠቀሙት መሣሪያዎች አልጠቀሰም።
✔️የተዘረፉ ንብረቶች የት እንደተከማቹ አልተገለጸም
✔️በወቅቱ ከተፈጸመው ጥቃት ጋር ተያይዞ ኋላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮች ተጠያቂ ስለመደረጋቸው እና ተደርገውም ከሆነ በሪፖርቱ አልተካተተም
4) ሪፖርቱ በወቅቱ የከተማው እስልምና ጉዳዮች ሳያውቅ በከተማ አስተዳደሩ በኩል ስለተቀበሩት ሟቾች አልጠቀሰም።
5) ሪፖርቱ የድርጊቱ መንስኤ ምክንያት በቀብር ስነስርዓቱ የተፈጠረው ድንገተኛ ግጭት እንደሆነ አድርጎ በማቅረብ ድርጊቱ ቀድሞ ታስቦበት እንዳልተፈጸመ አድርጎ አቅርቦታል። ይሁን እንጂ የድርጊቱ ባህሪ እና ከዛ በፊት የነበሩ ሁኔታዎች እንደሚያሳዩት ድርጊቱ ድንገት የተፈጸመ ሳይሆን ቀደም ብሎ የታቀደ እና የጥላቻ ቅስቀሳ ውጤት መሆኑን ነው።
እና ሌሎች ጉዳዮች ገልጿል።
1 686
ስለትግራይ እና ማህበረሰቡ ስላለበት አዘቅት አብሮኝ ተምሮ ትግራይ ተመድቦ ይሰራ ከነበረ ዶክተር ጓደኛዬ የሰማሁትን አሰቃቂ እውነታ ጥቂቱን ላካፍላችሁ።
• ውኃና መብራት ጦርነቱ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ እንደተቋረጠ ነው። እሱ በነበረበት ከተማ ማህበረሰቡ ውኃ የሚቀዳው የሚሽን(NGO) ድርጅት ለራሱ አስቆፍሮት ከነበር የጉድጓድ ውኃ ነው። እንዲህ ዓይነት አጋጣሚዎች የሌሉባቸው አካባቢዎችስ እንዴት ነው ሚጠቀሙት? አስቡት ያለውኃ እንዴትነው የሚኖረው? በምን ምግብ ያበስላል? ምንስ ይጠጣል? ሰውነቱን፣ ልብሱን፣ የሚመገብበትን ሁሉ በምንስ ያጥባል?
• መሰረታዊ ሸቀጦችንም ሆነ አስቤዛ ለመግዛት በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። ምክንያቱም ክፍት ሱቅ ማግኘት ዘበት ነው። አብዛኞቹ ተዘርፈው ባዷቸውን ቀርተዋል። ሌሎች ደግሞ እንዳይዘረፉ ከፍተኛ ስጋት ስላለባቸው የማያውቁትን ሰው አያስተናግዱም። የሚያውቁትን ሰው ብቻ በሩን ሳይከፍቱ ያስተናግዳሉ። ሸቀጣ ሸቀጦችና የተለያዩ እህሎች ወደ ትግራይ መግባት ካቆመ ረዘም ያለ ጊዜ በመቆየቱና የንግዱ እንቅስቃሴ በመቆሙም ሱቆች መጀመሪያውኑ የነበራቸውን እንጂ አዲስ ማስገባት አይችሉም። ይህም ማህበረሰቡ ላይ ከፍተኛ ችግር ፈጥሯል።
• የካሽ ፍሎው እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የለም። ምንም ያህል ሀብታም የሚያስብለው ንብረቶች ያሉት ሰው እንኳን በከፍተኛ ደረጃ የካሽ ገንዘብ እጥረት አለበት። ባንኮች ብር በበቂ ሁኔታ አይገባላቸውም። ደሞዝተኞች ደሞዝ ከተከፈላቸው ረጅም ጊዜ ሆኗል። በንግድ ባንክ በኩል የሚመጣው ገንዘብ እጅግ ውስን በመሆኑ ለሁሉም ደሞዝ ለመክፈል አይዳረስም። በመሆኑም ደሞዝተኛው ደሞዙ አስር ሺም አምስት ሺም ምንም ያህል የነበረ ቢሆን ከአንድ ሺ ብር በላይ እየተከፈለው አይደለም። ምክንያቱ ደግሞ ባንክ ላይ ያለው የካሽ እጥረት ነው። አንድ ሺዋንም የሚያገኘው ወረፋ ጠብቆ ነው። በጡዋት እየሄዱ ባንክ እየተሰለፉ ወረፋው እስከ አስራ አምስት ቀናት ሊፈጅ ይችላል። የዚህን ያህል ቀናት ተመላልሶ ወረፋ የጠበቀ ሰው ተራ ደርሶት ደሞዙን ሳይቀበል ካሽ አልቋል የሚባልበት አጋጣሚም ብዙ ነው።
• ሌላው የትግራይ ማህበረሰብ የተቸገረው ነዳጅ ነው። አንዲት ጠብታ ነዳጅ ከማደያ ማግኘት የማይታሰብ ነው። በመሆኑም ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርቴሽን ችግር አለ። በሀያ ኪሎሜትር እርቀት ላይ ወደምትገኝ ከተማ እቃ ማስጫን ከ20 እስከ 30 ሺ ብር እየተጠየቀ ነው። ወሎና አፋር ላይ በነበረው ጦርነት ህውኃት ከሁለቱ አካባቢዎች የዘረፈው ከፍተኛ የሆነ የነዳጅ ክምችት አለው። ነገር ግን ለትግራይ ህዝብ ነው የምታገለው የሚለው ህውኃት የዘረፈውን ነዳጅ ለህዝብ አገልግሎት አላዋለውም። ሌላው ቀርቶ ምጥ የያዛት እናት ለጫነ አምቦላንስ እንኳ ነዳጅ አይፈቀድም። ህውኃት ነዳጅ እንዲጠቀሙ ፍቃድ የሰጣቸው ለራሱ የጦር መኪኖች ብቻና ብቻ ነው። ከዚህ በተረፈ የተጎዳ የህውኃት ወታደር ለጫነ አምቡላንስ የተወሰነ መጠን ነዳጅ እንዲቀዳ ይፈቀድለታል።
ከመሆኑም ጋር እነዚህ ሁሉ ችግሮች ያማረሩት ነዋሪ ከትግራይ ልውጣ ቢል መውጫው በሞት የታጠረ ነው። ጓደኛዬ በUN በኩል ደብዳቤ አፅፎ ነው ወደ ቤተሰቦቹ መምጣት የቻለው። ሰሞኑን አንድ ሚዲያ ላይ በትግራይ እራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች ቁጥር እንደተበራከተ ሰማሁ። ያለውን አሰቃቂ ችግር አስቀድሜ የሰማሁ በመሆኑ ዜናው ብዙም አልደነቀኝም። እንዲህ ዓይነት ጨለማ ውስጥ ያለ ማህበረሰብ እራሱን ቢያጠፋ ምን ይገርማል? እንዲያም ሆኖ ህውኃትን ያማረረና የረገመ፣ መጨረሻው ደመከልብ መሆን ነው።
