en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
በዛሬው ሰልፍ የተሰማው የጠለምት አማራ ግልፅ አቋም‼️ #የማንነት ጥያቄያችን በበጀት ክልከላ አይገታም! #ሴራና የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ድጋሜ እልቂትን እንጅ ሰላምን አያመጣም! #አማራነታችንና ኢትዮጵያዊ መንፈሳችን በክፋት መዶሻ ቢወገርም አይደበዝዝም! #ጠለምት ሰሜን ጎንደር እንጅ ትግራይ አይደለም። # አማራ ነን አልን እንጅ አማራ እንሁን አላልንም! #በማንነትና ርስታችን አንደራደርም! #ከጠለምት ተፈናቅሎ ወደ ትግራይ የሄደ ተፈናቃይ የለንም! #ማንነታችን ደም፣ ታሪክ፣ የተፈጥሮ ችሮታ እንጅ ለምርጫ ሊቀርብ አይገባም! #የጠለምት አማራ ማንነት ጥያቄ የፍትሕ ወዳድ ኢትዮጵዬውያን ጥያቄ ነው! #ማንነታችን አማራ፣ ድንበራችን ተከዜ ነው። #የማይገባንን አልፈን አንጠይቅም። የራሳችን አሳልፈን አንሰጥም። #ለእንግዶች እንጅ ለወንጀለኞች ቦታ የለንም! #አማራነታችንና ኢትዮጵያዊ መንፈሳችን በክፋት መዶሻ ቢወገርም አይደበዝዝም! #የዋልድባ መነኮሳትን ጭፍጨፋ አንረሳውም! #በመንግስት ኃይል ታጅቦ ለህወሓት የሚቀርብ የሎጅስቲክ ድጋፍ በአስቸኳይ ይቁም! #ጊምባሚድያኒትዎርክ ➨ለፈጣን መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ !!

ይሄ ነው ትክክለኛ አማራዊ ሙዚቃ 🙏👇 subscribe and like አድርጉ https://youtu.be/MlW-MrPCY3I

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው “የባሎች ትምህርት ቤት” ተከፈተ * ትምህርት ቤቱ ለወንድ የቤተሰብ አባላት ስልጠና በመስጠት ላይ ነው ተብሏል * ማሰልጠኛው በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥም ለ8 ሺህ ሰዎች ስልጠናዬን እሰጣለሁ ብሏል #Ethiopia  | በሲዳማ ክልል በህፃናት አድን ድርጅት ድጋፍ ባሎችን በልጆች አያያዝ፣ ምግብ ማብሰል ፣ንጽህና አጠባበቅ እና ሌሎች አገልግሎቶች ላይ ያተኮረ ትምህርት ቤት ተከፍቷል። የህጻናት አድን ድርጅት ለአል ዐይን እንዳለው ወንዶች ቤተሰባቸውን በማስተዳደሩ ሂደት ሚናቸውን በሚገባ ተገንዝበው በልበ ሙሉነት እና በብቃት እንዲወጡ ለማስቻል ለወንድ የቤተሰብ አባላት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ብሏል። ድርጅቱ አክሎም በሲዳማ ክልል በሚተገበረው የአመራር ክህሎት እና የኢኮኖሚ አቅም ማጎልበት ፕሮግራም ወጣት ሴቶችን በጥቃቅን እና አነስተኛ የንግድ ስራዎች እንዲሰማሩና ቤተሰቦቻቸውን እንዲረዱ ብሎም በማህበረሰባቸው ውስጥ የለውጥ ወኪሎች እንዲሆኑ የሚያስችሉ የተለያዩ የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑን ጠቅሷል። ለሴቶች ከሚሰጡ ስልጠናዎች እና ድጋፎች በተጨማሪ በማእከላቱ ከ519 በላይ የሚሆኑ የወንድ አጋሮቻቸው እና የቤተሰብ አባሎቻቸው ደግሞ በባሎች ትምህርት ቤት የስልጠና መርሃ ግብር እንዲካተቱ ተደርጓል ተብሏል። በህጻናት አድን ድርጅት በህጻናት አድን ድርጅት የሀዋሣ አካባቢ ቢሮ ሼል አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ካዬሣ “በእነዚህ ማእከላት በምግብ ማብሰል፣ በቤት ፅዳት እና በንጽህና አጠባበቅ፣ በልጆች እንክብካቤ እና ሌሎች የቤት ውስጥ ስራዎች ዙርያ ለወንድ የቤተሰብ አባላት (በቀዳሚነት ለባሎች) ስልጠና በመስጠት ላይ ነው” ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊ ባሎች በስልጠናው ወቅት የቤት ውስጥ ስራዎችን እንዲለማመዱ በማድረግ ለአሰልጣኞቻቸው ስራዎቻቸውን እንዲያሳዩ የሚደረግ ሲሆን ስልጠናው በተግባራዊ ልምምድ የታገዘ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል። በባሎች ስልጠና እንዲካተቱ የሚደረጉት ሁሉም ወንድ የቤተሰብ አባላት (ባል፣ አባትና ወንድም) ሲሆኑ በቀዳሚነት ለባሎች ሆኖ እንደ አማራጭ በክህሎት ማሳደግ ፕሮግራም ውስጥ የታቀፈቸው ሴት ሰልጣኝ ያላገባች ከሆነች ስልጠናው የሚሰጠው ለአባቷ/ወንድሟ እንዲሆን እናደርጋለን›› ብለዋል። እንደ ሼል አስኪያጁ ገለጻ፣ የባሎች ትምህርት ቤት በሚል ስያሜ ስልጠና መስጠት ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት በአብዛኛው የማህበረሰባችን ክፍል ዘንድ የቤት ውስጥ ሾል እና የልጅ እንክብካቤ የሴቶች ሾል ነው ተብሎ ስለሚታሰብ እና በተግባርም የሚስተዋል በመሆኑ ነው። የባሎች ትምህርት ቤት ስልጠናም ዋነኛ የትኩረት ነጥብም ይሄው ወንዶችን በቤተሰብ አስተዳደር ዙርያ ቀዳሚ ተዋናይ ማድረግ መሆኑን ሾል አስኪያጁ ተናግረዋል። በቀጣይ ሦስት አመታት በአመራርነት ክህሎት እና የኢኮኖሚ አቅም ማጎልበት ፕሮግራም አማካኝነት በመደበኛው የሴቶች የአቅም ማጎልበት ስልጠና ተሳታፊ ከሚሆኑት ሴቶች በተጨማሪ የቤተስብ አጋሮቻቸውን እና ባሎቻቸውን ጨምሮ በሚሰጡ ስልጠናዎች የተጠቃሚዎችን ኣሃዝ ከስምንት ሺህ በላይ ለማድረስ አቅደናል‹‹ ሲሉ አቶ ኤልያስ ተናግረዋል። አል-ዐይን #ጊምባሚድያኒትዎርክ ➨ለፈጣን መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ !! https://t.me/GimbaMediaNetwork

#ትኩረት ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር በሚወስደው መንገድ ላይ "አሊዶሮ" ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ቁጥራቸው ቢያንስ 30 የሚሆኑ በአብዛኛው ሹፌሮች እና ተጓዦች ዛሬ ጠዋት በ "ታጣቂዎች" ታግተው እንደተወሰዱ የአይን እማኞች ያደረሱኝ መረጃ ይጠቁማል። እገታው በመሀል መንገድ ላይ በርካታ ደቂቃዎችን ፈጅቶ ሲፈፀም የደረሰ አንድም የፀጥታ ሀይል እንዳልነበር፣ "መንግስት ኦነግ ሸኔ የሚላቸው" ናቸው ብለው ምንጮች ያደረሱኝ ታጣቂዎች ሲፈልጉ ወደሰማይ ደጋግመው ሲተኩሱ እና ዘና ብለው ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ገልፀዋል። አዲስ ማለዳ እንደዘገበው በተመሳሳይ እሁድ ሰኔ 4/2015 ዕለት ከሌሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ባቱ (ዝዋይ) ከተማ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከዚሁ ሀይል ጋር ባደረጉት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ የአራት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ከሟቾቹ መካከል አንዲት ሴትን ጨምሮ ሦስቱ የመንግሥት የጸጥታ አካላት መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ አንዱ ደግሞ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን አባል ነው ተብሏል። የተገደለው የታጣቂ ቡድን አባል እግሩን ተመትቶ መሸሽ ባለመቻሉ፤ የታጣቂ ቡድኑ አባላት መረጃ እንዳያወጣ በማለት ገድለውት እንደሸሹ ተጠቁሟል። ለተከታታይ ሁለት ሰዓታት በላይ ሲደረግ ነበር የተባለው የተኩስ ልውውጥ ዓላማው እስረኛ ለማስፈታት እንደሆነ ተገልጿል። የታጣቂ ቡድኑ አባላት አሉ ወደተባለበት ኦኢቱ አካባቢ የመንግሥት የጸጥታ አካላት በተደጋጋሚ ቢያቀኑም "በሕይወት ተርፈው የሚመለሱት ጥቂቶች ናቸው" ሲሉ ነዋሪቹ ተደምጠዋል ብሎ ሚድያው ዘግቧል። በሌላ በኩል፣ በቅርብ ቀናት በሱሉልታ ከተማ እና አካባቢው በርካታ እገታዎች እየተፈፀሙ፣ የታገቱት ሰዎችን ለመልቀቅ ደግሞ እስከ ሚልዮኖች እየተጠየቀ እንደሆነ ታውቋል። #EliasMeseret #ጊምባሚድያኒትዎርክ ➨ለፈጣን መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ !! https://t.me/GimbaMediaNetwork

ጠንካራ እንጅ ተሸናፊ አይደለንም። ምዕራባዊያንን በየቀኑ እያከሰርን በየቀኑ የተንኮል ቆባቸውን እየገፈፍን እራቁታቸውን እያስቀረናቸው ነው። እኛ ከኔቶ አገራት ስብስቦች የበለጠ የኒዩክለር ሚሳይሎች አ
ጠንካራ እንጅ ተሸናፊ አይደለንም። ምዕራባዊያንን በየቀኑ እያከሰርን በየቀኑ የተንኮል ቆባቸውን እየገፈፍን እራቁታቸውን እያስቀረናቸው ነው። እኛ ከኔቶ አገራት ስብስቦች የበለጠ የኒዩክለር ሚሳይሎች አሉን። የምዕራቡ ዓለም ይህንን ቁጥር እንድንቀንስ ይፈልጋሉ። እኛ ደግሞ ብትፈልጉ ሲኦል ግቡ እንጅ ( Go to hell )መሳሪያችንን አንቀንስላችሁም ነው የምንላቸው።  የሩሲያው ፕሬዚዳንት በዓመታዊው የፒተርስበርግ የኢኮኖሚ ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ የተናገሩት ነው። ብቻውን ሆኖ የአለም በዝባዥ እምነትና ባህል አጥፊዎችን የገጠመ ሰው ነው። የዘመኑ ቸ ጉቬራ ነው። አለምን ከምዕራባዊያን ሀያልነት ለማላቀቅ የሚፋለም የታላቋ አገር ራሽያ መሪ ነው። እምነት ፅናት እውቅት ጀግንነት ሀይልን ጥበብን ይዞ የገጠመ ሰው ነው። #ጊምባሚድያኒትዎርክ ➨ለፈጣን መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ !! https://t.me/GimbaMediaNetwork

< የሸራ ቤቶች የፈረሱት በከንቲባ አዳነች አቤቤ ትዕዛዝ ነው > - የአካል ጉዳተኞች ማህበር‼️ < የአዲስ አበባን ጎዳናዎች ተከትለው የተወጠሩ ትንንሽ የሸራ ቤቶች የፈረሱት ከከንቲባዋ በወረደ ትዕዛዝ መሆኑን > የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር በጋራ በመሆን ሰኔ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ አድርገዋል። ማህበራቱ በመግለጫቸው < ከሸራ ቤቶች ፅዱ የሆነ  ከተማ መገንባት ስላስፈለገ ብቻ በተለያዩ ማህበራት ተደራጅተን  ለንግድ የተቀበልናቸው የንግድ ቤቶቻችን ያለምን ቅደመ ሁኔታ እንዲፈርሱ ተደርገዋል>  ብለዋል። <  ፁዱና ማራኪ ከተማ ግንባታ ስም የፈረሱ የአካል ጉዳተኞች የስራ ማህበራት ስድስት ሲሆኑ ከነዚህም መካከል  ሰላም ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች ንግድ አክሲዮን ማህበር የንግድ ቦታ  ይገኝበታል > ተብሏል። ማህበሩ < ባለፉት አስራ አምስት አመታት በሁሉም መስኮች በተለይ በልማት ዘርፍ ከመንግስት ጎን በመሆን አገራዊ ግዴታውን ሲወጣ እንደከረመ > አስታውሶ <  አሁን  ላይ ግን ከከንቲባ አዳነች አቤቤ የወረደ ነው በሚል ትዕዛዝ መፍረሱ ነው > የተመላከተው። በተመሳሳይ እንዲፈርሱ ከተደረጉ አካል ጉዳተኞች ንግድ አኪሲዮን ማህበር ሾል ቦታዎች መካከል ጽናት ለፍሬ ሌላኛው ነው። < ማህበሩ እንደሌሎች ማህበራት ሁሉ በስሩ ከ31 አባላት በላይ ያቀፈ ሲሆን አሁን ላይ ሁሉም አባላቱ ከስራ ፈጣሪነት ወደ ልመና መሰማራታቸውን > ጠቁመዋል። < የ2010 ለውጥ ተከትሎ የመጣው የአገሪቱ መንግስት አካታችነቱ ላይ የጎላ ክፍተት እንዳለበት >  የሚያነሳው መግለጫው <  አካል ጉዳተኞቹ ካለባቸው አካላዊ አቅም አንፃር እቃቸውን አስረው በሄዱበት አፍታ አፍራሽ ግብረ ኃይሉ በመምጣት  የንግድ ቦታውን አፍርሶ እቃቸውን ሁሉ ጭኖ መውሰዱን ነው > የገለፁት። የስራ ቦታቸው የፈረሰባቸው እና እቃቸው የተወሰደባቸው የአካል ጉዳተኞቹ  ይህ መግለጫ እስከተሰጠበት ቀን ድረስ የሚላስ የሚቀመስ በማጣታቸው ቀድሞ ትተውት ወደ ነበረው የልመና መስክ መሰማራታቸውን አመላክተዋል። የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር ጉዳዩን በህግና አሰራር መሠረት ለመፍታት ከሚመለከተው አካል ጋር  ላለፉት 30 ቀናት ደብዳቤ የፃፈ ቢሆንም ጉዳዩን እልባት የሚሰጠው ባለማግኘቱ መግለጫ ለማውጣት መገደዱን ገልጧል። በመግለጫው መጨረሻ ላይ አቋሙን በግልፅ ያስቀመጠው የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር በህግ መንግስቱ  አንቀፅ 45 ንዑስ አንቀፅ 5 የተደነገገው ድንጋጌ እንዲከበር በፅኑ ጠይቋል። አክሎም መንግስት በከተማ ግንባታ ስም ከስራ የተፈናቀሉ እና የስራ ቦታቸው የፈረሰባቸውን  የመዲናዋ አካል ጉዳተኞች በሚመለከት አፋጣኝ ጊዚያዊ መፍትሔ እንዲሰጥ አክሎ ጠይቋል(አሻም ቲቪ)። #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

ኢትዮ ኮከብ ኢንተርቴይመንትን ሰብስክራይብ ያድርጉ አድስ ነገር https://youtube.com/@ethiokokebentertainment

በሞጆ ከተማ ጥቁር ዶሮ አርደው ሲቀብሩ የተገኙት ታሰሩ በሞጆ ከተማ ዛሬ ሰኔ 9/2015 ዓም ሁለት ግለሰቦች ጥቁር ዶሮ አርደው ሲቀብሩ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን #ፋስት_መረጃ ከሞ
+2
በሞጆ ከተማ ጥቁር ዶሮ አርደው ሲቀብሩ የተገኙት ታሰሩ በሞጆ ከተማ ዛሬ ሰኔ 9/2015 ዓም ሁለት ግለሰቦች ጥቁር ዶሮ አርደው ሲቀብሩ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ሾር መዋላቸውን #ፋስት_መረጃ ከሞጆ ከተማ ኮሙኒኬሽን ሰምቷል። ሁለቱ ግለሰቦች የሰሌዳ ቁጥሩ "A66590" በሆነ መኪና ከአዲስ አበባ ከተማ በመነሳት ሞጆ ከገቡ በኋላ ሞጆ  ከተማን በመኪና በመዞር የፍጥነት መንገድ መግቢያ አከባቢ "ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት" ፊት ለፊት ማህበረሰቡን የሚያስቆጣ ድርጊት ጥቁር ዶሮ በማረድ እየቀበሩ እያለ በህብረተሰቡ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ሾር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ እንደሆነ ተገልጿል።

አሁን ላይ ህዝቡ ዱባይን ከመምሰል ይልቅ የሚያሳስበው...! በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ስራ አግኝቶ መስራት፣ በልቶ ማደር እና በነፃነት መኖር ነው። ዱባይን አንጋጠን እያየን በርሀብ ህዝብ እየሞተብን ያ
አሁን ላይ ህዝቡ ዱባይን ከመምሰል ይልቅ የሚያሳስበው...! በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ስራ አግኝቶ መስራት፣ በልቶ ማደር እና በነፃነት መኖር ነው። ዱባይን አንጋጠን እያየን በርሀብ ህዝብ እየሞተብን ያለን ሀገር ሆነናል።

ጦርነቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራያ ላይ ስለ ኢትዮጵያ ተናግረዋል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የሱዳን ተወካይ በሀገሪቱ ባለው ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት የሱዳን ተወካይ አል ሀሪስ ኢድሪስ በስብሰባው ላይ፤ በሱዳን ሰሜናዊ ክፍል ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት አካባቢ ስላለው ሁኔታ አንስተዋል። በዚህም የሱዳን ጦርና አር.ኤስ.ኤፍ መካከል ጦርነት ከተከሰተ ወዲህ ሱዳን በሰሜን በኩል ከኢትዮያ ጋር በሚያዋስናት አካባቢ የተረጋጋ መሆኑን ምንም ችግር እንዳልተከሰተበት እና የተረጋጋ መሆኑን አስታውቀዋል። ተወካዩ ኢትዮጵያ ድንበሯን ጦርነቱን ሸሽተው ለተሰደዱ ሱዳናውያን ድንበሯን ከፍታ መቀበሏንም ጭምር አስታውቀዋል። በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት የሱዳን ተወካይ አል ሀሪስ ኢድሪስ አክለውም ቻድ በድንበሯ ላይ የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አማጽያንን አስራለች ሲሉም ተናግረዋል። የሱዳን ጦር ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ስለ ኢትዮጵያ ምን አለ? የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች በአዲስ አበባ የፊት ለፊት ውይይት እንደሚያደርጉ ተገለጸ ጦርነቱን ተከትሎ ጦርነቱን ሸሽተው የተሰደዱ 113 ሺህ ሱዳናውያን ቻድ ደርሰዋል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ከዳርፉር የተፈናቀሉ 350 ሺህ ሱዳናውያን በሀገር ውስጥ መጠለያ ካምፖች ውስጥ ይገኛሉ ብለዋል። ለፈጥኖ ደረሽ ኃይሉ የፀረ አውሮፕላን የጦር መሳሪዎች በብዛት በድብቅ እየተላለፉ እንደሆነ ደርሰንበታል ሲሉም ተወካዩ ተናግረዋል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በኤል ጄኒና፣ በዛሊየንጊ እና ናይላ በተባሉ ስፍራዎች የሚያፈጽመውን ጥቃት ቀጥሎበታል ሲሉ ተናግረዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በፈጥኖ ደራሽ ኃይል ላይ ጫና እንዲያሳድር የጠየቁት የሱዳን የተመድ ተወካይ፤ ታጣቂ ኃይሉ ማስታጠቅ እንዲቆም ማእቀብ እንዲጣልም ተማጽነዋል።

ወደ ኢትዮጵያ የገባዉ ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን ኩባንያዉ አስታወቀ 👉🏼የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር መኪኖቹ ወደ ሀገር እንዳይገቡ አግዷል ከ
+1
ወደ ኢትዮጵያ የገባዉ ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን ኩባንያዉ አስታወቀ 👉🏼የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር መኪኖቹ ወደ ሀገር እንዳይገቡ አግዷል ከቅርብ ግዜ ወዲህ በኢትዮጵያ በስፋት እየታየ ያለዉ ቮልስ ዋገን ID.6 የተሰኘዉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን ኩባንያዉ በአዲስ አበባ የጀርመን ኤምባሲ በኩል ለትራንስፖርት ሚኒስቴር በላከዉ መግለጫ ተናግሯል። ተሽከርካሪዎቹ በቻይና ሀገር ተገጣጥመዉ ወደ ኢትዮጲያ እየገቡ ነዉ ያለዉ ኩባንያዉ  የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ስለሆነም ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ  የታገደ መሆኑን ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ማሳሰቡን ብስራት ራዲዮ ሰምቷል፡፡ #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

በአዲስ አበባ ከተማ ቀይ ሽንኩርት በአንድ ሳምንት ውስጥ የ40 ብር የዋጋ ጭማሪ አሳየ 👉 በኪሎ ከ 70 እስከ 80 ብር እየተሸጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ የቀይ ሽንኩርት ዋጋ በአንድ ሳምንት ውስጥ
በአዲስ አበባ ከተማ ቀይ ሽንኩርት በአንድ ሳምንት ውስጥ የ40 ብር የዋጋ ጭማሪ አሳየ        👉 በኪሎ ከ 70 እስከ 80 ብር እየተሸጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ የቀይ ሽንኩርት ዋጋ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን ሸማቾች ቅሬታቸዉን ለብስራት ሬዲዮ ገልጸዋል፡፡ሽንኩርት በኪሎ ከ70 እስከ 80 ብር እየተሸጠ መሆኑን የተናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ በተለይ በአንድ ሳምንት ውስጥ የ40 ብር ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል። በአሁኑ ሰአት ገቢያቸው እና ኑሮው እየተመጣጠነ አለመሆኑ እና የሚፈልጉትን ሸምተው መኖር አለመቻላቸው ኑሮአቸውን  እንዳከበደውም ነዋሪዎች አክለዋል ።ብስራት ሬዲዮ በተለያዩ የገበያ ስፍራዎች ተዘዋውሮ ለማየት እንደሞከረው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ከመኖሩ ባሻገር አቅርቦቱ ከእለት እለት እየቀነሰ መሆኑን ሃሳባቸውን ለጣቢያችን ከገለጹ ነጋዴዎች ለመገንዘብ ችለናል ። ብስራት ሬዲዮ ጉዳዩን በተመለከተ ምክንያቱ ከምን የመጣ ነዉ የሚለዉን ለማጣራት የከተማዉ ንግድ ቢሮ የሚመለከታቸውን አካለት ለማናገር በተደጋጋሚ የስልጥ ጥሪ ቢያደርግም ምላሽ ማግኘት አልቻለም፡፡እንዲሁም በአካል ተገኝታችሁ ጠይቁ የተባለ በመሆኑ በቀጣይ በሌላ ዘገባ ምላሻቸዉን አካተን ይዘን እንመለሳለን፡፡ ጆይን 👉 @Gimbamedianetwork

ኬንያ የአፍሪካ ሀገራት የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ በራሳቸው ገንዘብ ክፍያ መፈጸም እንዲጀምሩ ጠይቃለች:: ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በጂቡቲ ፓርላማ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው “በዶላር ላይ ጥገኝነቱ ይብቃ” ያሉት። “ከጂቡቲ እቃ ገዝተን በዶላር የምንከፍለው ለምንድን ነው? ለምን? ምንም ምክንያት የለም” ያሉት ፕሬዝዳንት ሩቶ፥ ጂቡቲም ሆነች ኬንያ የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ የአሜሪካ ዶላር መጠቀም አያስፈልጋቸውም ብለዋል። “እኛ የአሜሪካን ዶላር እየተቃወምን አይደለም፤ በነጻነት ግብይት መፈጸም ስለፈለግን እንጂ” ሲሉም አብራርተዋል። #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

እንዲህም እያለ ይቀጥላል። ዶፍ ዝናብ እየጣለ፣ ረመጥ እሳት እየተፋ መድፍ ባሩድ እያዘነበ ነው ሱዳናዊ የሆንኩት አለች አንዲት እናት በጥይት ተመታ ሀኪም ቤት ከገባች ቡኋላ ለሚዲያዎች ስትናገር። እኛም አገር እንዲህ አይነት ታሪክ እየተደገመ ነው። በሰውየው ላይ አንዲትም የሰውነት ግርማ ሞገስ የለም። እዝነት ዕርህራሄ የሰው ፍቅር የሚባል ነገር አይነበብበትም። የዚህን የሰው ንግግር እያቁነጠነኝ ሆዴን እያረደኝና ልቤን እየፋቀኝ ነው የሰማሁት። መቸም ዘመን የማያሳየን የለም። ሸገር የሚሏት የደሀ ጠል ከተማ ብዙ እያሳየችን ነው። በተቃራኒው ግን መንግስት እንዲስተካከል ህልም አለን ለምን ጥቂት ገብሰበላ ጅሎች የማንቂያ ደውል ነው። እኔ ጠቅላይ ሚኒስቴሩን ብሆን ለአየር መንገዱ የቦርድ ሀላፊ አልነበረም የስልጣን ስንብት የምፅፈው። ለዚህ የፊራኡን አክስት ልጅ ነበር እቢሮ ጠርቸ ስማማ ወዳጀ ከቶ ከየትኛው መፀሀን ወተህ ነው ድሀ አሎድም ድሮም ህገወጥ ድሀ ናቸው አሁን ግን ህጋዊ ደሀ አደረግናቸው የምትላቸው ሰዎችኮ 117ሺ ዜጎች እኔን አምነው ለኔ ድምፅ ሰተው መንግስቴ ብለው የመረጡኝ ዜጎቸ ናቸውና በል አህያህን ጠብቅ ብየ ከስልጣኑ የማስነሳው። ዳሩ ግን እንዲሀ አደለም። አልታደልንም። በቃ እኛ እንዲህም እያልን መቀጠላችን ይመስላል። በዚህ ከረማ ቢስ ሰውየ አባባል 48 ሚሊየን የሀገሪቱ ደሀ ህዝብ ህገወጥ ደሀ ነው ማለቱ ነው። ሰወየው የስአረቱን ማንነትና በህዝብ ላይ የተሰራውን ነጭ ክህደት ነው የነገረን። ይች እህታችን በበደሏ የኮራቸው ኩርት ብላ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች የሰውነት ግርማ ሞገስ አላት። በተቃራኒው ግን የሸገሩ ተቀላቢ ደሀ ጠሉ ጥቁሩ አነር ግን በፊቱ ላይ እየሳቀ እንኳን የ18 ቀን ሀዘንተኛ የ2 ወር መንገደኛ ነው የሚመስለን። ወንጀሎኞች ፈገግታ ይርቃቸዋል የሚለው የሀይማኖት መፀሀፍ ስናስበው ይህንን ግለሰብ ይመስላል። መቸም ይሄ ዶክትሬት የሚባል ማዕረግ ስብዕናውን ቢመርጥ ኑሮ ይህንን ሰውየ ዶክትሬቱን የሰጠው ተቋም ገፎ ለዚች በደለኛ እህታችን ይሰጠው ነበር። መማርና ማወቅ ደሀን መጥላትና ማሳደድ ከሆነ ድንቁርና ፅድቅ ነው። የጭንቅላት ዕጢ በወረሳቸው ሰዎች 48 ሚሊየኑን ህዝብ ህገወጥ ድሀ ነው ብሎ ሲሳደብ ከማየት በላይ ሞት የለም። ሱሌማን አብደላ #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

⬆️ አንድ የአይናችን ማረፊያ፣ የባንዲራችን ተሸካሚ፣ የጥቁር ህዝቦች የስኬት ምልክት እና የውጭ በር ከፋቻችን የሆነው አየር መንገዳችን ላይ ደግሞ ምን ታስቦ እንደሆነ አልገባኝም። ዛሬ በደረሰኝ የተረጋገጠ መረጃ መሰረት የአየር መንገዱ የቀድሞው ስራ አስፈፃሚ፣ እስከ ሁለት ቀናት በፊት ደግሞ የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩት አቶ ግርማ ዋቄ ካለፍላጎታቸው በመንግስት ከስራቸው እንዲነሱ ተደርገው በምትካቸው የአየር ሀይል ጀነራል ተሹመዋል። አቶ ግርማ በደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ለአመራርነት በ20 ሺህ ዶላር የወር ደሞዝ ሲጠሩ "እኔ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ አባል ነኝ፣ የጥቅም ግጭት ሊፈጠር ስለሚችል ይቅርብኝ" ብለው ሀገራቸውን ያስቀደሙ በአቪዬሽን ዘርፍ እጅግ የካበተ ልምድ ያላቸው ግለሰብ መሆናቸውን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፣ በስማቸውም በየአመቱ ሽልማት ይሰጣል። የጦር ጀነራልን ንግድ ላይ መሾም ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል በሜቴክ ታይቷል፣ በዛ ላይ የቦርድ ሰብሳቢ ከአውሮፕላን ግዢ እስከ ሰፋፊ የስትራቴጂ እቅዶች ላይ ውሳኔ የሚሰጥ ቁልፍ አካል ነው። በአየር መንገድ እና በአየር ሀይል መሀል ሊኖር የሚችል የማኔጅመንት መሳሳብ እና የጥቅም ግጭት በራሱ ማሰብ ይቻላል። ሲጀምር፣ በቅርቡ በነበረው አስከፊ ጦርነት ወቅት በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ስሙ በብዙ የሚነሳ ተቋምን ሀላፊ የስኬታማ አለም አቀፍ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ አርጎ መሾም ምን ይፈይዳል? ሲቪል ሆኖ ብቃቱ እና ልምዱ ያለው ሌላ ሰው ጠፍቶ ነው? ሲቀጥል፣ ከአፄ ሀይለስላሴ እስከ ደርግ፣ ብሎም እስከ ኢህአዴግ ባሉት መንግስታት ጣልቃ ገብነት ሳይኖርበት ላለበት ስኬት የበቃ ተቋምን አንዴ ስራ አስፈፃሚውን፣ አሁን የቦርድ ሰብሳቢውን (... ወደፊት ደግሞ በእርግጠኝነት ሌላ እናያለን) "ማተራመስ" አላማው ምን እንደሆነ ግልፅ ባይሆንም ዝም ማለት ግን ይከብዳል። ጋዜጠኛ #EliasMeseret #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

የአርበኛ ዘመነ ካሴ አስቸኳይ መልዕክት! ለሁሉም አማራ በአስቸኳይ ይዳረስ!