en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
ኤርትራ ከ16 አመት በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባልነቷ ተመለሰች በትናንትናው እለት በጂቡቲ በተካሄደ ስብሰባም ኤርትራ የኢጋድ መቀመጫዋን ዳግም መረከቧን የሀገሪቱ የማስታ
ኤርትራ ከ16 አመት በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባልነቷ ተመለሰች በትናንትናው እለት በጂቡቲ በተካሄደ ስብሰባም ኤርትራ የኢጋድ መቀመጫዋን ዳግም መረከቧን የሀገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። ባለፉት 16 አመታት ከምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካዊ ውሳኔዎች ተነጥላ የቆየችው ሀገር ለቀጣናው ሰላም፣ መረጋጋትና ትብብር በቁርጠኝነት እንደምትሰራም ነው ያስታወቁት። Join @Gimbamedianetwork

⬆️ #በመጨረሻም በቅርቡ ሾለ "1.5 ሚልዮን ብር አፓርትመንት ሽያጭ" ያቀረብኩት መረጃ በሚመለከተው አካል ተደርሶበታል "የግብርና እና የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ላይ መሰማራታቸውን በመግለፅ ቅንጡ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በዝቅተኛ ዋጋ መግዛት እንደሚችሉ በተለያዩ መንገዶች እያስተዋወቁና ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆናቸው መገንዘብ ተችሏል"--- የኢትዮጵያ ፋይናንስ አገልግሎት ደህንነት ሙሉ መግለጫው ⬇️ ኢትዮጵያ ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች በመሰማራት ራሳቸውን፣ ህብረተሰቡንና አገርን ተጠቃሚ የሚያደርጉበት የህግ እና የአሰራር ስርዓት ያላት ከመሆኗም በተጨማሪም ለኢንቨስትመንት ከፍተኛ ፍላጎትና ዕድል ያላት አገር መሆኗም ይታወቃል። ጤናማ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ለአገር ከፍተኛ እና የማይተካ አዎንታዊ ፋይዳ እንዳላቸው ማንም የሚገነዘበው ነው። ሆኖም አንዳንድ ግለሰቦች እና ድርጅቶች በኢንቨስትመንት እና በአብረን እንስራ ስም ተጨባጭና የተሟላ መረጃ ሳይሰጡ ከፍተኛ ገንዘብ ከህብረተሰቡ እየሰበሰቡ መሆናቸውን ለአገልግሎቱ የደረሰው መረጃ ያመለክታል። ገንዘብ ከህብረተሰቡ ለመሰብሰብም እጅግ አትራፊ የሆነ የግብርና እና የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ላይ መሰማራታቸውን በመግለፅ ቅንጡ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በዝቅተኛ ዋጋ መግዛት እንዲሁም አክሲዮን በመግዛት በአጭር ጊዜ ውስጥ ትርፋቸውን በእጥፍ ማሳደግ እንደሚችሉ በተለያዩ መንገዶች እያስተዋወቁና ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆናቸው መገንዘብ ተችሏል። ጤናማ የፋይናንስ እንቅስቃሴ እና ኢንቨስትመንት በእጅጉ የሚደገፍ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በኢንቨስትመንት ስም የሚፈፀሙና ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችንም መከላከል በዚያው ልክ አስፈላጊ ይሆናል። ስለሆነም ህብረተሰቡ ከመሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ ሊፈፀም ከሚችል መጭበርበር ራሱን እንዲጠብቅ፣ የጥንቃቄ እርምጃም እንዲወስድ አገልግሎቱ ያሳስባል። ተቋማችን የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ፣ ሽብርተኝነትንና ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎችን ብዜት በገንዘብ የመደገፍ ወንጀሎችን መከላከልና መቆጣጠር እንዲቻል ከተለያዩ አካላት የፋይናንስ ወንጀል ነክ መረጃዎች በመቀበል፣ በመሰብሰብና በመተንተን ውጤቱን ለሚመለከታቸው አካላት በማሰራጨት እንዲሁም በመሰል ጉዳዮች ላይ ከህግ አስከባሪ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛል። ህብረተሰቡም ከወንጀሎቹ ጋር በተያያዘ በአንድ  በኩል ራሱን ከወንጀል በመጠበቅ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ደግሞ እንደተለመደው ለተቋማችን ጥቆማ በመስጠት የድርሻውን እንዲወጣ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ሰኔ 06 ቀን 2015 ዓ.ም ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት

ወልደው ለመጣል 9 ወር ሙሉ መሸከም.. 😕😣😣 ባህርዳር ቀበሌ 16 ዮሐንስ ቤተክርስቲያን አካባቢ የ5 ቀን ሴት ጨቅላ ህፃን ልጅ ተጥላ ተገኝታለች ለጊዜው ህፃኗ 6ኛ ጣቢያ ትገኛለች። ህፃኗ በርሀ
ወልደው ለመጣል 9 ወር ሙሉ መሸከም.. 😕😣😣 ባህርዳር ቀበሌ 16 ዮሐንስ ቤተክርስቲያን አካባቢ የ5 ቀን ሴት ጨቅላ ህፃን ልጅ  ተጥላ ተገኝታለች ለጊዜው ህፃኗ 6ኛ ጣቢያ ትገኛለች። ህፃኗ በርሀብ እንዳትጎዳ  የፖሊስ አባሏ  ህጻኗን በዚህ መልኩ ጡት አጥብታታለች። እናትነት መልካም የህይዎት ስጦታ ነው። #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

የዕለቱ አጫጭር መረጃዎች 1)  በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን እና በሲዳማ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች በተፈጠረ ግጭት ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገለጸ፡፡ በሁለቱ ብሔር ተወላጆች መካከል የቆየ የድንበር ይገባኛል ክርክር መኖሩን እና ይህንም ተከትሎ በተለያዩ ጊዜያት ግጭት እና አለመግባባት እንደሚፈጠር በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች ተናግረዋል።በሲዳማ እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች በተለይም ጌዴኦ፣ ከማኒ፣ ገደብ እና ገርበማ በተሰኙ ሥፍራዎች በተደጋጋሚ ግጭት እንደሚከሰት እና በዚህ ሳቢያም ከሁለቱም ወገን ሰዎች ለአካል ጉዳት እንደሚዳረጉ ተነግሯል። 2)  የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የጽህፈት ቤት ሃላፊ ቴዎድሮስ ሀይለማርያም “መንግስት ስልጣን የሰጣቸው የአብን አመራሮች ፓርቲው የተመሰረተበትን ዓላማ በመተው የመንግስት ጉዳይ አስፈፃሚ ሆነዋል” ሲሉ ተናግረዋል። በአማራ ክልል መንግስትና በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል እየተደረጉ ያሉ ግንኙነቶችን አስመልክቶ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አመራሮች ለሁለት መከፈላቸውን ሃላፊው ይፋ አድርገዋል። ሀላፊው እንደሚሉት የሁለቱ አካላት ግንኙነት ሰላም እስካመጣ ድረስ መልካም ነው የሚሉ አመራሮች አሉ በአንፃሩ ደግሞ ተጠያቂነት ሳይኖር ጦርነቱን በበላይነት ሲመሊ የነበሩ አካላት የሚያደርጉት ውይይት አግባብ አይደለም የሚሉ መኖራቸውን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው አገላለፅ “ይህ መከፋፈል የመጣውም በመንግስት ሹመት ተደልለው የመንግስት ሾል አስፈፃሚ የሆኑ የንቅናቄው አመራሮች በመኖራቸው ነው፡፡” ሲሉ ተችተዋል። 3)  በኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ሥፍራዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በነበረው ጦርነት እና ግጭት ምክንያት  በአገሪቱ ከ22 ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉዳት እና ውድመት መድረሱ ተገልጿል፡፡ የአምስት ዓመት የመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ መርሐ ግብር ይፋ ሲደረግ እንደተገለጸው፣ የጉዳት እና የመልሶ ማቋቋም ፍላጎት ዳሰሳው፣ በተለያዩ ክልሎች ተካሒዷል፡፡ በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ዕቅዱን ለማስፈጸም፣ 20ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ በሥነ ሥርዐቱ የተሳተፉት የክልል ርእሳነ መስተዳድሮችም በዕቅዱ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ 4)  ኤርትራ ከ16 አመት በኃላ የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ)ን መቀላቀሏ ተገልጿል፡፡ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ መስቀል መስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ “ኤርትራ በኢጋድ ውስጥ የጀመረችውን እንቅስቃሴ ቀጥላለች እና መቀመጫዋንም ይዛለች ”ብላዋል፡፡ ሚኒስትሩ ሀገራቸው “ሰላም፣ መረጋጋትና ቀጠናዊ ውህደት” ላይ ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል። ኢጋድ በ2007፣ ኬንያ የኢትዮ- ኤርትራን የድንበር ውዝግብ እንድትመለከት ውሳኔ ሲያሳልፍ ኤርትራ ከድርጅቱ አባልነት መውጣቷ ይታወሳል፡፡ የኢጋድ ዋና ጸሓፊ ወርቅነህ ገበየሁ ኤርትራ ወደ ህብረቱ መመለሷን አወድሰውታል ሲል የአሜሪካ ኤፍፒ ዘግቧል።  በተያያዘ ዜናም የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) የወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)ን ዋና ጸሐፊነት ለተጨማሪ አራት ዓመታት ማራዘሙ ተገልጿል። 5)  በኬንያ ከእምነት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ በረሃብ ከተረፉት መካከል 65ቱ ኬንያውያን ራስን በማጥፋት ወንጀል መከሰሳቸው ተሰምቷል። መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ ራሳቸውን ያስራቡት እነዚህ የክርስትና እምነት ተከታዮች ከረሃብ ተርፈው በነፍስ አድን ማዕከል ውስጥ ቢገቡም ምግብ አንመገብም ብለው አሻፈረኝ ማለታቸው ተነግሯል። ዓቃቤ ህግ ሰኞ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ከረሃብ በህይወት የተረፉት እነዚህ ግለሰቦች የአዕምሮ እና የህክምና ምዘና እስኪደረግላቸው በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ አመልክቷል። ምግብ አንበላም በማለታቸውም የነፍስ አድን ማዕከሉ እነሱን ለማቆየት እንደማይቻለውም ተገልጿል። ለአቃቤ ህግ ጥያቄውም ፍርድ ቤቱ ከሰሞኑ ምላሽ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ፓስተሩ በሚንቀሳቀስበት የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ባለው ሰፊ የሻካሆላ ጫካ እስካሁን ድረስ ከ280 በላይ አስከሬኖች ጥልቀት በሌላቸው መቃብሮች ውስጥ ተቀብረው ተገኝተዋል። ቴሌግራም : https://t.me/GimbaMediaNetwork

"ልዩ ሀይሉን ይቅርታ ጠይቀን በአንድ ቀን መሰብሰብ እንችላለን" የአማራ አመራሮች የተናገሩት‼️ ጌታቸው ረዳ፣የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር፣የአማራ ክልል ተወካዮች እና የፌደራል ባለስልጣናት ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ በነበረው ስብሰባ ላይ የተነሱ ጉዳዮችን እንደሚከተለው ቀርቧል። 👉 ተፈናቃዮች በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ውስጥ እንዲመለሱ ጌታቸው ረዳ ያነሳ ሲሆን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር ተፈናቃዮቹን ለማቋቋም አሜሪካ እንደምትረዳ ተናግረዋል። ጌታቸው ረዳ ከተፈናቃዮች በተጨማሪ የፀጥታ ሀይል እና አስተዳደር መግባት አለበት ያለ ቢሆንም የአማራ ተወካዮች ይሄን እንዳልተቀበሉት እና ተፈናቃዮች ብቻ መግባት እንዳለባቸው ተነጋግረዋል። የፀጥታ ሀይል እና የራሳችንን አስተዳደር እናስገባለን የምትሉ ከሆነ አካባቢውን ለዳግም ጦርነት የሚዳርግ ነው ብለዋል። ይሄን የምትሉት የልዩ ሀይሉን መፍረስ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከሆነ እኛ ልዩ ሀይሉን ይቅርታ ጠይቀን በአንድ ቀን እንሰበስበዋለን" እስከማለት የደረሰ ንግግር በአማራ ተወካዮች በኩል ተሰምቷል። ሁለቱም አካላት ተፈናቃዮችን በተመለከተ የሚቆጣጠር የጋራ  ግብረ ሀይል እንዲቋቋም ተስማምተዋል። 👉ማይክ ሀመር በዚህ ስብሰባ ላይ ወደ አንድ ወገን ያደላ ንግግር ታይቶባቸዋል። 👉ከሰሞኑ በራያ እየታየ ያለው የትግራይ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ ከተፈናቃዮች ጋር አብረው በመግባት እና አካባቢውን ለመቆጣጠር እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ። ሆኖም አሁን ላይ በውይይቱ ምክንያት በአሉበት እንዲቆሙ ተደርገዋል ☑ በተጨማሪ በባህርዳሩ ስብሰባ ላይ ከተናገሩት መካከል 👇 ጌታቸው ረዳ ባህርዳር ተገኝቶ ከህዝብ ጋር ባደረገው ቆይታ በፕሮፓጋንዳ በሰራሁት ነገር ልጠየቅ ይገባል አለ‼️ "ህዝባችንን ለዚህ  ችግር የዳረግነው እኛ ፓለቲከኞች ነን። ህዝቡማ ተጋብቶና ተዋልዶ አብሮ ይኖራል። እኔ በሚዲያ ለሰራሁት የፕሮፖጋንዳ ሾል ልጠየቅ ይገባል። ይቅርታም እጠይቃለሁ።" ጌታቸው ረዳ። በእውነት ማገዶ የፈጀ ቢሆንም ለህዝቡ ሲባል ይሄ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ነው። በፖለቲከኞቹ ስህተት የሆነው ሁሉ ሆኗል። ብዙ ህይወት ጠፍቷል፣ ብዙ ሰው አልቅሷል፣ ብዙ ውድመት ደርሷል። በተለይ እነ ጌታቸው የሰሜን እዝን በመምታት በይፋ በጀመሩት ጦርነት የትግራይ ህዝብ ተጎድቷል። ሂሳብ እናወራርዳለን በማለት ወደ አማራ ክልል ገብተው ብዙ መከራ አድርሰዋል፣ ደርሶባቸዋል። ሁሉ ከሆነ በኋላ ወደ ሰላም መመለሾ መልካም ነው። የሰላም ፍላጎቱ ግን በቅንነት ላይ የተመሰረተ ሊሆን ይገባል። #ጊምባሚድያኒትዎርክ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

ባለመነፅር ስናይፐር የሰራው ወጣት!!! #ጊምባሚድያኒትዎርክ አማኑኤል አንዱአለም ይባላል የዳንግላ ከተማ ተወላጅ ነው። አማኑኤል ከድሮ ጀምሮ ከትምህርቱ ጎን ለጎን የፈጠራ ስራ በመስራት እያደገ የመጣ
+1
ባለመነፅር ስናይፐር የሰራው ወጣት!!! #ጊምባሚድያኒትዎርክ አማኑኤል አንዱአለም ይባላል የዳንግላ ከተማ ተወላጅ ነው። አማኑኤል ከድሮ ጀምሮ ከትምህርቱ ጎን ለጎን የፈጠራ ስራ በመስራት እያደገ የመጣ ታታሪ ልጅ ነው ታዲያ ይህን ልዩ ተሰጥኦውን በትምህርት እና በሳይንስ የተደገፈ አድርጎ ወደፊት ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎችን ለመስራት ወደ ዳንግላ ቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ተቋም በመቀላቀል ያለውን ተሰጥኦ እንዲጎለብት በማድረግ ትምህርቱን አጠናቋል። ወጣት አማኑኤል ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ብዙ የፈጠራ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ታዲያ በቅርቡ ደግሞ በአይነቱ ለየት ያለ ባለመነፀር ስናይፐር ሰርቶ ብቅ ብሏል:: ከዚህ ቀደም በዳንግላ ከተማ ተማሪ ሀብታሙ ድሽቃ እና ላውንቸር ሰርቶ እንደነበር ይታወሳል። ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!! https://t.me/GimbaMediaNetwork

" ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " - አቶ ጌታቸው ረዳ " ልዩነቶችን በሕግ፣ በሠላም እና በመነጋገር ለመፍታት የአማራ ሕዝብ ፍላጎት አለው " - ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ባህር ዳር የሚገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ልዑካቸው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ጋር እንዲሁም ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በዚህ ውይይት ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ " ዋጋ የማይጠይቅ የሠላም አማራጭ ሳለ በፖለቲከኞች የጠብ ርሃብ ምክንያት በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል " ብለዋል፡፡ " ልዩነቶች ቢኖሩ እንኳን ልዩነቶቹ ከአማራ እና ትግራይ ሕዝብ በታች ናቸው " ያሉ ሲሆን " አሁን የጦርነትን ምዕራፍ ዘግተን የሠላም አማራጮችን የምናይበት ጊዜ ነው " ብለዋል፡፡ " የሁከት እና ግርግር አጀንዳዎች የሚታያቸው ይኖራሉ፤ ነገር ግን ለሕዝብ ካሰብን እና ከሠራን ከሠላም ውጭ የተሻለ አማራጭ የለንም " ሲሉ ተናግረዋል። የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በበኩላቸው ፤ " ልዩነቶች ይኖራሉ  ያሉትን ልዩነቶችን ግን በሕግ፣ በሠላም እና በመነጋገር መፍታት የአማራ ሕዝብ ፍላጎት ነው ብለዋል። " የአማራ ክልል ሕዝብ እና መንግሥት ለሠላም አማራጮች ዝግጁ ነው " ሲሉም ተደምጠዋል። " የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱ ወደ ቀደመው ሁኔታው መመለሾ አለበት፣ ትራንስፖርት እና የንግድ እንቅስቃሴ መጀመር ይኖርበታል " ያሉት ዶ/ር ይልቃል " ተከባብረን እና ተደማምጠን ልዩነቶቻችን ለመፍታት መሥራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።የፖለቲካ አመራሩ የጀመረውን የሠላም ግንኙነት የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች በተለይ ደግሞ አዋሳኝ አካባቢ ያሉ የሁለቱም ክልል ሕዝቦች አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። ☑️ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ‼️ 👇👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork 👉 ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ለመስጠት 👇 https://t.me/GMN_news

ልዩልዩ 503 ሺህ ኪሎ ግራም መሸከም የሚችለው የዓለማችን ግዙፍ ተሸከርካሪ በመጫን አቅሙ ከዓለም አንደኛ የሆነው ተሸከርካሪ በቡልጋሪያ ነው የተሰራው Š ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ  2023/6/11 9:38 GMT የዓለማችን ግዙፍ ተሸከርካሪ ተሽከርካሪው ያለጭነት ብቻ 360 ሺህ ኪሎ ግራም የሚመዝነው መኪናው በሰዓት እስከ 64 ኪሎ ሜትር ይጓዛል ቡልጋሪያ በመጫን አቅሙ ከዓለም አንደኛ የሆነ ተሸከርካሪ ሰራች፡፡ የቀድሞዋ የሶቪየት ህብረት አንድ አካል የሆነችው ቡልጋሪያ ተሸከርካሪዎችን በማምረት ጥሩ ልምድ ያላት ሀገር ነች፡፡ ለሩሲያ ባላት ቅርበት ከምዕራባዊያን ጋር የሻከረ ግንኙነት ያላት ቡልጋሪያ የዓለምን ክብረ ወሰን የሰበረ በግዝፈቱ የመጀመሪያ ነው የጠባለ ተሽከርካሪ ማምረቷን አስታውቃለች፡፡ ልዩ መለያው ቤልዜዜድ-75710 የተሰኘው ይህ የዓለማችን ግዙፍ ተሽከርካሪ 503 ሺህ ኪሎ ግራም ይመዝናል ተብሏል፡፡ የሩሲያው “ታይገር” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ከአሜሪካው “ሀምቪ” ብረት ለበስ ተሸከርካሪ ጋር ሲነጻፀሩ ተሽከርካሪው በተለይም በማዕድን ማውጣት ሾል ለተሰማሩ ኩባንያዎች ዋነኛ ተመራጭ ነው የተባለ ሲሆን በዚህ ዘርፍ በዓለም ተመራጭ ለሆኑት ካተርፒላር፣ ሌብሄር እና ቡሴረስ ኩባያዎች ጥሩ ዜና እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡ ተሽከርካሪው ማዕከሉን በቤላሩሷ ዞዲኖ ከተማ ባደረገው ቤልኤዜድ በተሰኘው ኩባንያ የተሰራ ሲሆን በመጫን አቅሙ እና በመጠኑ የዓለማችን ግዙፉ ተሽከርካሪ ተብሏል፡፡ ይህ ተሸከርካሪ ብቻውን እቃ ከመጫኑ በፊት 360 ሺህ ኪሎ ግራም የሚመዝን ሲሆን አንዱ ጎማ ብቻውን 5 ሺህ 500 ኪሎ ግራም ይመዝናል፡፡ 20 ሜትር ርዝመት ያለው ይህ ተሽከርካሪ እያንዳንዳቸው 2 ሺህ 300 የፈረስ ጉልበት ያላቸው ሀይል ሰጪ ሲሊንደሮች ሲኖሩት በሰዓት 60 ኪሎ ሜትር መጓዝ ይችላልም ተብሏል፡፡ ኩባንያው አሁን ላይ ሶስት ቤልኤዜድ-75710 ሞዴል ተሸከርካሪዎችን ያመረተ ሲሆን ሶስቱም ተሽከርካሪዎች በሩሲያ መገዛታቸው ተገልጿል፡፡ @gimbamedianetwork

የሚሸጥ የዩቱብ ቻናሎችን ከፈለጋችሁ በዚ ግቡና ቼክ አርጉ 👉 https://t.me/ethiotechnologyschool የሚሸጥ አካውንት ለጠየቃችሁኝ አሁን አለ ገብታችሁ ቼክ አርጉት መልካም ግዜ🙏🙏 🆕 የሚሸጥ ካላችሁ ደሞ በዉስጥ ያናግሩኝ 📩 •➤ 𝐈𝐧𝐛𝐨𝐱 𝐌𝐞 https://t.me/Ethiotechnology_school

+1
ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ exit exam lay ለምን ቅሬታን ገለፃችሁ በማለት መንግሰት የሚችለዉን አቅም በመጠቀም በዚህ መልኩ ሊያሻግራቸዉ ሲሞክር ዉሏል ። አሁን ላይ ልጅን ወደ ዩኒቨርስቲ ልኮ ማስተማር ማሰብ በህጋዊ መልኩ ይገረፍልኝ ይገደልልኝ ይታገትልኝ እንደማለት ነዉ። #stopethinccleansing #stopamharajenocide

ሚስጥሩ ይሄ ነው ወገን! ብዙ ጊዜ ይገርመኝ የነበረው "የበጋ ስንዴ" እያሉ የሚያሰሩት እጅግ የተጋነነ ዜና ነበር። 52 ሚሊዮን፣ 38 ሚሊዮን፣ 30 ሚሊዮን ወዘተ ኩንታል ሲሉ "እነዚህ ሰዎች አፈር
+3
ሚስጥሩ ይሄ ነው ወገን! ብዙ ጊዜ ይገርመኝ የነበረው "የበጋ ስንዴ" እያሉ የሚያሰሩት እጅግ የተጋነነ ዜና ነበር። 52 ሚሊዮን፣ 38 ሚሊዮን፣ 30 ሚሊዮን ወዘተ ኩንታል ሲሉ "እነዚህ ሰዎች አፈር ነው የሚያፍሱት? ወይስ ይሄ የምናውቀው ስንዴ?" እያልኩ ነበር። አንድ ዞን መአት ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ አመረተ ይባላል። እንደነሱ  ከሆነ  ክረምት በርካታ አይነት ሰብል አምርቶ የበጋው መስኖ ለሚገባባቸው አካባቢዎች ያውም ስንዴ ብቻ ተጨማሪ  በርካታ ሚሊዮን ይመረታል ማለት ነው። ኢትዮጵያውያን ምርት እስኪያስጠላቸው መሆኑ ነው። ሰሞኑን ለእርዳታ የሚመጣውን ስንዴ ዘርፈዋል ተባለ። በበጋ ይህን ያህል ስንዴ ምርት ተገኘ ሲሉ የነበሩ ሰዎች ዜናውን ሲያስጮሁት የኖሩት ለሚሰርቁት ነበር። ያ ሁሉ ዜና የሀሰት ብቻ አልነበረም። መዝረፊያም ጭምር ነው።via gatachew shiferaw 👉 ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ‼️ 👇👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork 👉 ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ለመስጠት 👇 https://t.me/GMN_news

ታሰረ #Ethiopia | የጉማ አዋርድ መሥራችና አዘጋጅ ፤ ዳይሬክተር ዮናስ ብርሃነ መዋ መርኃ ግብሩን ሳያጠናቅቅ ትናንት ምሽት መታሰሩን ባለቤቱ፤ ወ/ሮ ሳምራዊት ከሰተ (ሊሊ) ስልክ ደውላ ነግራኛ
+1
ታሰረ #Ethiopia | የጉማ አዋርድ መሥራችና አዘጋጅ ፤ ዳይሬክተር ዮናስ ብርሃነ መዋ መርኃ ግብሩን ሳያጠናቅቅ ትናንት ምሽት መታሰሩን ባለቤቱ፤ ወ/ሮ ሳምራዊት ከሰተ (ሊሊ) ስልክ ደውላ ነግራኛለች፡። 9ኛው የጉማ የሽልማት ዝግጅት በስካይላይት በደመቀ ሁኔታ ተከናውኖ ከምሽቱ 5:20 ሰዓት ላይ ተጠናቆ ነበር። ወ/ሮ ሳምራዊት ከሰተ (ሊሊ) እንደተናገራቸው "አንቺን አንፈልግሸም ! ... እርሱን ግን ለጥያቄ እፈልገዋለን " በማለት ቦሌ ትራፊክ መምሪያ በተለምዶ ስሙ አንበሳ ጋራዥ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩን ተናግራለች። *** [ ትውስታ : አምና፣ ካቻምና መድረክ ላይ ] [ ልጅ አባቱን በመድረክ፣ በሕዝብ ፊት የሰጠው ማስጠንቀቂያ ] እኔ አስራሃለሁ!" "ፖለቲካ ውስጥ ተመልሰህ ብትገባ መንግሥት ሳይሆን እኔ አስራሃለሁ!" "አንዳንድ ሰው እድለ ቢስ ሆኖ በልጅነቱ ሀገሩን እየጠላ አድጎ ሲያድግም ሀገሩን ለማፍረስ ይጥራል። አንዳንድ እድለኞች ደግሞ የሀገራቸውን ታላቅነት ተሰብከው አድገው ሀገራቸውን ለመገንባት ደፋ ቀና ሲሉ ህይወታቸውን ይጨርሳሉ። እንደዚህ ስለሀገር መልካምነት ተሰብከው ሀገር ለመገንባት ከባጁ እድለኞች መካከል አንዱ ወላጅ አባቴ ነው!" ዮናስ ብርሀነ መዋ፣ የጉማ አዋርድ መሥራች እና ሥራ አስኪያጅ በፕሮግራሙ ላይ የተናገረው "በሕይወት መቆየት እና በሕይወት መኖር ይለያያል። እኔ በሕይወት መኖር የጀመርኩት ዛሬ ነው። ይሁንና ልጄ፣ አባቱ የተነጠቀውን ሕይወት ለማኖር ዮናስ ብርሃነ መዋ ሲል አኑሮኛል። ልጄን በእናንተ ፊት በክብር እንዳመሰግነው ፍቀዱልኝ" ብርሃነ መዋ ( አንጋፋ ነጋዴና ፖለቲከኛ) Join👉@gimbamedianetwork

Update ኢትዮ ቴሌኮም ችግሩን ቀርፏል።አዲስ አበባን ጨምሮ የድምፅ ጥሪ ኔትወርክ ተቋርጦ ነበር፣አሁን ተስተካክሏል። 🙏🙏

ደሴ እና ኮምቦልቻ ዛሬ ቅዳሜ ከማዳው 1:00 ጀምሮ ስልክ ተቋርጧል።የተቋረጠው የድምፅ አገልግሎት ሲሆን የፅሁፍ መልዕክትና ኢንተርኔት አልተቋረጠም።ዛሬ ደሴ ከተማ ሠልፍ  ይካሄዳል።ከስልኩ ጋር ምን እንዳገናኘው አይታወቅም።የሚገርመው ሳፋሪኮም ይሰራል።ኢትዮ ቴሌኮም ምን ነካው? ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ለመስጠት 👇 https://t.me/GMN_news

ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ለመስጠት 👇 https://t.me/GMN_news

ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ለመስጠት 👇 https://t.me/GMN_news

9ኛው የጉማ ሽልማት ስነስርዓት ትናንት ሰኔ 2 2015 ዓ.ም ምሽቱን በ ስካይላይት ሆቴል ተካሄዷል ። በዘጠነኛው የጉማ አሸናፊዎች ታዉቀዋል 1.ምርጥ አጭር ፊልም፡   የጉድ ሀገር መንገድ /ብስራት ተስፋ 2.ምርጥ የተማሪ አጭር ፊልም ፡ መሐይማን / አማኑኤል ተሾመ 3. ምርጥ ተከታታይ ኮሜዲ ድራማ : አሰኳላ 4.ምርጥ ዉርስ ትርጉም ድራማ : አደይ 5.ምርጥ ዶክመንተሪ ፡ ባሌ ብሄራዊ ፓርክ /አዚዝ አህመድ 6.ምርጥ ዉርስ  ድራማ ተዋናይት ፡ በእምነት ሙሉጌታ / አደይ 7. ምርጥ ዉርስ  ድራማ ተዋናይ : አለማየሁ ታደሰ / አጋፋሪ 8.ምርጥ የፊልም ሙዚቃ :  የሱፍ አበባ  9.ምርጥ ስኮር : ረመጥ / ብሩክ አሰፍ 10.ምርጥ ሜካፕ : ተሚማ ሁላላ / ረመጥ 11.ምርጥ ፊልም ፅሁፍ : ረመጥ / ዳንኤል በየነ 12. ምርጥ ቅንብር : የሱፍ አበባ /እስክንድር ተፈራ 13.ምርጥ ሲኒሚአቶግራፊ : የሱፍ አበባ / ዋለልኝ አደገ 14.ምርጥ ተስፍ የተጣለበት ተዋናይነት : ክሱት / እየሩሳሌም አሰፍ 15.ምርጥ ተስፍ የተጣለበት ተዋናይ : ፊናፍ / ብሩክ ግርማ 16.ምርጥ ረዳት ሴት ተዋናይት : የማር ዉሃ / መስከረም አበራ 17.ምርጥ ረዳት ተዋናይ : ጥላዬ / እንግዳሰዉ ሀብቴ 18. ምርጥሴት ተዋናይት : ክሱት / ጠረፍ ካሳሁን 19.ምርጥ ወንድ  ተዋናይ : ሄኖክ በሪሁን  /ረመጥ 20.ምርጥ ዳይሬክተር : ረመጥ/ ዳንኤል በየነ 21.ምርጥ ፊልም : የሱፍ አበባ /ለገሰ ገነቱ 22.የህይወት ዘመን ተሸላሚ : አርቲስት ኪሮስ  አለማየሁ 23.የሔርሜላ አሸናፊ : ገነት ከበደ 24. አርአያ ሰብ ከያኒ : አርቲስት  መሰረት መብራቴ አሸናፊዎች ናቸዉ።