en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
በተፈጥሮ የታደልን ነን በአእምሮ ግን...❓❓ "ይህ ቦታ ጣራ ገዳም ደቡብ ጎንደር ይገኛል። እዚህ ተራራ አናት ላይ የአፄ ቴዎድሮስን ሀውልት ተክለን፣ ሙዚየም ገንብተን የቱሪስት መስህብ አድርገን የአ
በተፈጥሮ የታደልን ነን በአእምሮ ግን...❓❓ "ይህ ቦታ ጣራ ገዳም ደቡብ ጎንደር ይገኛል። እዚህ ተራራ አናት ላይ የአፄ ቴዎድሮስን ሀውልት ተክለን፣ ሙዚየም ገንብተን የቱሪስት መስህብ አድርገን የአለም ድንቅ የ adventure ቦታ መፍጠር እንችል ነበረ"(muktarovich osmanova)። በመንደር እና በጎጥ ታጥረን፣ ባልኖርንበት የኋላ ታሪክ ስንባለ፣አንዱ ብሄር ዱሮ ተበድያለሁ ሂሳቤን ማወራረድ አለብኝ፣እኔ የበላይ ነኝ ...ወዘተ በሚል ሰበብ የመሪዎቻችን ድክመት ተጨምሮ ከስልጣኔ ጀርባ ሆነን ቀርን፣ዳቦ ላይ ተቀምጠን ዳቦ ልመና ሄድን። ስንቱ ወጣት ስራአጥ ሆኖ ከምሞት በሚል የሜዲትራኒያን ባህር ሲሳይ ሆነው ቀሩ፣አሁንም አረፈደም ያለንን resource እንጠቀምበት። 👉በነገራችን ላይ ቻይና ዋነኛ የዕድገት መሰረቷ ውብ ተራራዎቿን እና መልከዓምድሯን ለ adventure እና ለመስህብ ምርጥ አድርጋ በመስራቷ ነው። ሀሳብ ስጡበት

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው አስታውቀዋል ! ሰብሳቢዋ ላለፉት ስድስት አመታት ተቋሙን የመሩ ሲሆን ፣
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው አስታውቀዋል ! ሰብሳቢዋ ላለፉት ስድስት አመታት ተቋሙን የመሩ ሲሆን ፣ ለመልቀቃቸው በምክንያትነት ያነሱት ከጤና ጋር በተያያዘ ረፍት እንደሚያስፈልጋቸው በመግለፅ ቢሆንም በገዢው መንግስት ፍፁም አንባገነናዊነት ተማረው እና ከሚቋቋሙት በላይ በመሆኑ መሆኑን ምንጮች እየገለፁ ይገኛሉ። ከሳምንት በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀውና ከሰላማዊ ፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓት ዳግም በዚሁ መጠሪያ በፓርቲነት ተመዝግቦ ለመንቀሳቀስ ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ የህግ መሠረት የሌለው መሆኑን ጠቅሶ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል። ይህን በማስመልከት ሪፖርተር ትናንት ሰኔ 18/2015 ዓ.ም ይዞት የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው ህወሓት ዳግም ወደምርጫ ፖለቲካው ለመግባትና በተፈረጀበት ስም ለመመዝገብ ከገዢው መንግስት (ቦርዱ?) ጋር ፖለቲካዊ ድርድር መጀመሩን አስታውቋል። ይህ ዜናና የሰብሳቢዋ በፈቃዳቸው ከሀላፊነት መነሳት በግልፅ የመንግስትን ጣልቃገብነትና ቦርዱ ገለልተኛ ሆኖ ተቋሙን መምራት አለመቻሉን አመላካች ነው። ሌሎች በቦርዱ ህግ እስካሁን መሰረዝ ያለባቸው የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰርተፍኬታቸውን ብቻ ይዘው በፖለቲካ ምህዳሩ ውስጥ መቆየታቸውም ሌላው የቦርዱን ነፃ ሆኖ የመወሰን ስልጣን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የከተተው መሆኑ አይዘነጋም። ገዢው ፓርቲም ለቦርዱ ህግ የማይተዳደርና ህግ የማይከተል መሆኑንም በተደጋጋሚ በአደባባይ ያሳየው እውነታ ሆኖ እናገኘዋለን ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ ወ/ሪት ብርቱካን “በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን ለተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ ወ/ሪት ብርቱካን “በገዛ ፍቃዴ  መልቀቄን  ለተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ” ብለዋል። ከኃላፈነታቸው የለቀቁበት ምክንያትም “ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ” ነው ብለዋል።

በቅርብ ቀን ጋሻ ሚድያ አድስ ነገር ይዘንላችሁ ልንመጣ ነዉ። ➨ጋሻ ሚድያን ጆይን በማለት ይቀላቀሉ https://t.me/Gashamedia

አድስ ነገር በቅርብ ቀን ጋሻ ሚድያ ➨ጋሻ ሚድያን ጆይን በማለት ይቀላቀሉ https://t.me/Gashamedia

የስራ ማቆም አድማዋን ገዥዎቹ ይፈልጓታል! ብዙ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ ወዘተ ጥሪ ወረቀት ፌስቡክ ላይ አያለሁ። ገዥዎቹ ለይምሰል ይቃወሙት ይሆናል እንጅ የሚፈልጉት ነው። በተለይ ያልተደራጀና ያልተጠና ከሆነ። 1) ገዥዎቹ ራሳቸው ህዝብ ስራ እያስፈቱ ነው። ጉዳያቸው አይደለም ባይሰራ። መንገድ ዘግተው ወደስራ እንዳይሄድ ሲከለክሉ ከርመዋል። ማዳበሪያ አያቀርቡ፣ ሲሚንቶ ከነጋዴ ጋር ተመሳጥረው በህገወጥ እየሸጡ ሌላውን ስራ አጥ አድርገውታል። በሶስት አመት ያልቃል የተባለ ግድብ 12 አመት የሞላው አለ። ፋብሪካዎቹ ስራ አቁመዋል። በሚቀጥለው አመት ደግሞ ተመራቂ አንቀጥርም ብለዋል። መስርያ ቤት ስራ የለም። ሄደህ ማየት ነው።ገዥዎቹ በኢትዮጵያ ላይ የስራ ማቆም አድማ ካወጁ ቆይተዋል። ብትሰራ ባትሰራ ጉዳያቸው አይደለም። 2) ወደ አገር ቤት የምትላከውን ትንሽ ዶላር ለራሳቸው አድርገዋል። ገንዘብ ጠፍቷል። አቅርቦት የለም። ነዳጅ በለው ስኳር ማቅረብ እየቻሉ አይደለም። ዘይት በለው ዱቄት ከቀን ቀን እየተወደደ ነው። ሱቅ ብትዘጋላቸው፣ ሳምንትና ወር ፀጥ ረጭ ብትል እረፍት የሰጠሃቸው ነው የሚመስላቸው። ችግሩ አንተ ባወጅከው የመጣ አድርገው፣ የአቅርቦት ጉዳይ ሳያስጨንቃቸው እረፍት ነው የሚወስዱበት። 3) የስራ ማቆም አድማ ስታደርግ ከአደባባይ ትጠፋለህ። ገዥዎቹ የሚፈሩት አደባባይ መውጣትን እንጅ ቤት ከተቀመጥክማ ደስታቸው ነው። ህዝብ የቤት ቁልፍ ቢሰጣቸው ዘግተውበት ቢጠፉ በወደዱ። 4) የስራ ማቆም አድማ የሚጎዳው ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮ ውስጥ ያለውን ነው። አብዛኛውን ህዝብ ማለት ነው። ይህ ማለት ደግሞ ህዝብ የስራ ማቆም አድማ የጠራውን ያማርራል ማለት ነው። አሊያም ገዥዎቹ አድማ የጠሩት እንዲጠሉ ያደርጋሉ። ለኢኮኖሚ ምስቅልቅል የዳረገው ገዥው ሆኖ ህዝብን ያስራበው የሶስት ቀን አድማ አድርገው ያቀርቡልሃል። በጅራፍህ ትገረፋለህ ማለት ነው። ነፃ አወጣዋለሁ ባልከው ህዝብ ዘንድ ፖለታካ ይሰሩብሃል። 5) በተለይ ባልተቀናጀ መልኩ ሲደረግ ሌላ ቀን አዋጭና አስፈላጊ ሲሆን ቢጠራ ህዝብ ከቁም ነገር እንዳያየው፣ ስልቱን እንዲሰለቸው፣ ትግሉን እንዲርቀው ያደርጋል። 6) ዋናዎቹ ገዥዎቹ አማራ ክልል በኢኮኖሚ ድቅቅ እንዲል ይፈልጋሉ። ስራ አቁሞ ቢከርም አድማ የጠራውን አካል ያመሰግኑታል። ህዝብ ትግሉን ሊያግዝ የሚችለው ደግሞ ገንዘብ ሲኖረው ነው። ሌላው በህገወጥ መንገድ ስራ እየሰጠ፤ አማራው ባለችውም ዘግቶ ከዋለ ለጠላቶቹ አዋጭ ነው። 7) ትግል ጊዜን ይጠይቃል። ተማሪዎች ለአመታት የደከሙበት ፈተና የሚፈተኑበት ወቅት ላይ "የትምህርት ማቆም" ተብሎ ስልት ከታጋይ ይሁን ከገዥዎች የመጣው ግራ የሚያጋባ ነው። ከዚህ ይልቅ የተቃውሞ ምንጩ ግራ እስኪገባቸው ድረስ ሊደረጉ የሚችሉ ስልቶች አሉ። በርካቶች ናቸው። ትግል የሚመራ አካል ስልቶቹን በደንብ አይቶ መርጦ፣ ጉዳትና ጥቅማቸውን አይቶ መሆን አለበት። ህዝብ በቀላሉ የሚቀባበለው፣ ለሚዲያ ግቡ የሆነ፣ ሰው አይቶት ምልክት የሚያደርገው፣ ፋሽን የሚያደርገው፣ የፀጥታ ኃይሉ ህገወጥ ነው አይደለም ብሎ የሚወዛገብበት፣ ቢከለክል ከህዝብ ጋር የሚጣላበት ስልት ሞልቷል። ከዚህ ላይ ልፃፈው? አልፅፈውም! እንደዛ አይደረግም! 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

➨በቅንነት ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን👇 https://youtu.be/95E_lF3jzyg

Watch "መሪዎች ስለ ኢትዮጵያ ምን አሉ|ከመንግስቱ ሀይለማርያም እስከ አብይ አህመድ ለኢትዮጵያ ህዝብ ታማኝነታቸዉን ምን አሉ?" on YouTube https://youtu.be/95E_lF3jzyg

➨በቅንነት ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን👇 https://youtube.com/@Ze_dagumedia

የሳምንቱ አንኳር ዜናዎች እሁድ ሰኔ 18፣ 2015 1) ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል በሚወስደው መንገድ ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ ወረዳ ገርበ ጉራቻ ላይ፤ በ“ኦነግ-ሸኔ” ታጣቂዎች የታገቱ አሽከርካሪዎችን ለማስለቀቅ 50 ሚሊዮን ብር  ተጠይቋል፡፡ የታጋች ቤተሰቦች የተጠየቁትን ገንዘብ የመፈክፈል አቅም በማጣታቸው፤ ከሕዝብ ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ በዚሁ ሳምንት ዘግባለች፡፡ ከታጋቾቹ መካከል የተጠየቁትን በአንድ ሰው አንድ ሚሊዮን ብር ከፍለው የተለቀቁ አስከርካሪዎች መኖራቸው ታውቋል፡፡ 2) 200 የሚጠጉ ወጣቶች “ኤክስክሉሲቭ ትራቭል” በተባለ ኤጀንሲ በኩል ወደ ተለያዩ የአውሮፓ አገራት ትሄዳለችሁ ተብለው 20 ሚሊዮን ብር መጭበርበራቸውን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡ ተጭበርብረናል ያሉ ወጣቶች ለአዲስ ማለዳ እንደገለጹት፤ መቀመጫውን አዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ደንበል ህንፃ ላይ ያደረገው “ኤክስሉሲቭ ትራቭል” ወደ አውሮፓ እና ወደ ተለያዩ አገራት እልካችኋለሁ በማለት ገንዘብ ከሰበሰበ በኋላ አድራሻውን አጥፍቶ እንደተሰወረ ጠቁመዋል፡፡ 3) የራያ አላማጣ ማኅበረሰብ የማንነት ጥያቄ ሰነድ በቀድሞ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም አማካኝነት እንዲጠፋ መደረጉ የአካባቢው አስመላሽ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡ ለምክር ቤቱ የገባው መረጃ እንዲጠፋ መደረጉ፤ የራያ አላማጣ ማኅበረሰብ የማንነት ጥያቄ መፍትሄ ሳያገኝ ለአራት ዓመታት እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል ተብሏል፡፡ 4) በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሼር ባሉ አራት ገዳማት ላይ መንግሥት በወሰደው እርጃ፣ አንድ መነኩሴ ብቻ መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስታውቃለች፡፡ በገዳማቱ ከግንቦት 18 እስከ 23/2015 ለተከታታይ አምስት ቀናት “የታጠቁ ኃይሎች በገዳሙ ውስጥ ይገኛሉ” በሚል በተደረገ ኦፕሬሽን እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ መነኮሳት መሞታቸውን፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት አሥተዳደር መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዎርጊስ አሥራት ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡ 5) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ጉጂ ዞን ከማዕድን ማውጣት ጋር በተያያዘ ጥቅም ላይ የዋሉ መርዛማ ኬሚካሎች ምክንያት በአካባቢው ማኅበረሰብ ላይ የሚደርሰው ጉዳት ተባብሶ መቀጠሉ ተስምቷል፡፡ በዞኑ በተፈጥሮ የማዕድን ሀብት የበለጸጉ እንደ ኦዶላ፣ ሻኪሶ፣ አዶላ ዋዩ፣ ሰበቦሩ፣ አዶላ ሬዴ እና አጋ ዋዩ በመሳሰሉ ወረዳዎች ጉዳቱ እንደቀጠለ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። 6) ባለፈው ሳምንት ከሰኔ 3-9/2015 በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተፈጠሩ የፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት 100 ሰዎች መገደላቸውን፣ የግጭት ሁኔታ “ኢትዮጵያ ፒስ ኦብዘርቫቶሪ” በሳምንታዊ ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል፡፡ ዓለም አቀፍ የግጭት ሁኔታ እና የክስተት መረጃ በመሰብሰብና በመተንተን የሚታወቀው “The Armed Conflict Location & Event Data Project” የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ይህንኑ ሼል በኢትዮጵያ እንዲሠራ በፕሮጀክት ደረጃ ያቋቋመው፤ “Ethiopia Peace Observatory” የተባለው ተቋም ባወጣው ሳምታዊ ሪፖርት፤ በሳምንቱ ከተገደሉት 100 ሰዎች መካከል 35ቱ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸውን አስታውቋል። 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

ሰላም ወዳዱ ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ የኔን አካውንት ሀክ በማድረግ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል እንዳልደርስ ብዙ እየጣሩ ነው ሆኖም ግን አዲስ አካውንት ለመክፈት ተገድጃለው ስለዚህ ከታች ያለውን የዩትዩብ ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን

ስንቱ እንደወጣ በዛው ቀረ.? ስንቱ ግን ያለጥፋቱ ተበልቶ የበላው ጅብ ሳይጮህ ቀረ። የስንቱ ቤት በጥቁር ሀዘን ጎርፍ ታረዘ፣ የስንቱ ህፃን ልብ በቂምና በዕልህ ውስጥ ተስለቅልቆ ኖረ.? 800 የሚሆ
ስንቱ እንደወጣ በዛው ቀረ.? ስንቱ ግን ያለጥፋቱ ተበልቶ የበላው ጅብ ሳይጮህ ቀረ። የስንቱ ቤት በጥቁር ሀዘን ጎርፍ ታረዘ፣ የስንቱ ህፃን ልብ በቂምና በዕልህ ውስጥ ተስለቅልቆ ኖረ.? 800 የሚሆኑ ህፃናት እናትና አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በጥይት አልቀው ደብረብረሀን ወስጥ አሉ። የዚህም ወንድማችን ልጆችና ቤተሰቦችም እንደዚሁ ናቸው። ጥበብ የሰጠውን ኑሮ እየኖረ በግፍ ታግቶ እንደወጣ ቀረ። መልካም እረፍት። እንደ አገር ግን የሊቢያ ሰሜናዊ ክፍል ውስጥ እንዳለን ነው መቁጠር ያለብን። ሱሌማን አብደላ

መረጃዎችን በድምፅ እና በምስል የማቀርብበት የዩትዩብ ቻናሌ ለሁለተኛ ግዜ ተዘግቷል ዉድ የቻናሌ ቤተሰቦች 😭

ኮምቦልቻ ከተማ ቀበሌ 03 ኳስ ሜዳ ሰኔ 13/2015 ምሽት 2:00 ከፍቅረኛዋ ጋር የነበረች ወጣትን አስገድደው የደፈሩት የፀጥታ ሀይል አባላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋ
+2
ኮምቦልቻ ከተማ ቀበሌ 03 ኳስ ሜዳ ሰኔ 13/2015 ምሽት 2:00 ከፍቅረኛዋ ጋር የነበረች ወጣትን አስገድደው የደፈሩት የፀጥታ ሀይል አባላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋል።

የስምንት ዓመት ሕጻን መደፈሯን ተከትሎ በደላንታ ወረዳ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ! በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ በአንዲት የስምንት ዓመት ሕጻን ልጅ መደፈሯን ተከትሎ በትናንትናው ዕለት ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉ ተሰምቷል።ሕጿኗ የተደፈረችው ረቡዕ ሰኔ 14/ 2015 ማታ 11 ሰዓት አካባቢ ሲሆን፤ የሰልፉ መነሻ ሕጻኗን “የመከላከያ ሰራዊት አባል ነው የደፈራት” በሚል ምክንያት መሆኑን አዲስ ማለዳ ከአካባቢው ነዋሪዎችና ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ያገኘችው መረጃ ያመለክታል፡፡ ማኅበረሰቡ ሰልፍ ወጣው የሕጻኗን መደፈር ምክንያት አደርጎ ቢሆንም፤ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ረቡዕ ዕለት ከ11 ሰዓት ጀምሮ ራሱን “ፋኖ” ብሎ በሚጠራው ተጣቂ ኃይል እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። መከላከያ በደላንታ ወረዳ ዙሪያ ጊዜያዊ ካምፕ እንዳለው የጠቆሙት ነዋሪዎቹ፤ ከታጣቂ ኃይሉ ጋር የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ተከትሎ በአካባቢው የተሰማራው የመከላከያ ሰራዊት አካባቢውን ለቆ መውጣቱን ጠቁመዋል፡፡በጉዳዩ ላይ አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው የደላንታ ወረዳ የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያ መዝገበ ፈንታው፤ የመከላከያ አባካቱ ረቡዕ ሰኔ 14/2015 አካባቢውን ለቀው መውጣታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ ዋና አላማ “በመከላከያ ሰራዊት አባል ተደፍራለች የተባለችውን ሕጻን ፍትህ እንዲሰጣትና የመከላከያ ሰራዊት ከከተማዋ ይውጣ የሙል አቋም የተንጸባረቀበት እንደሆነ መዝገበ አብራርተዋል፡፡ተድፍራለች የተባለችው የስምንት ዓመት ሕጻን በከተማው ጤና ጣቢያ በሕክምና ላይ መሆኗን የጠቆሙት መዝገበ፤ "በተኩስ ልውውጡ እና በሰላማዊ ሰልፉ የተጎዳ አካል መኖሩን ማረጋጋጥ አልቻልንም" ብለዋል። 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

መነጋገሪያ ሆኖ የዋለ ዜና‼️ የቲዊተር ባለቤት ኤለን መስክና የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የቡጢ ግጥሚያ ሊያደርጉ ነው‼️ የዓለማችን ቁጥር አንድ ቱጃር ኤለን መስክ በትዊተር እንደቀልድ የሰነዘረው “
መነጋገሪያ ሆኖ የዋለ ዜና‼️ የቲዊተር ባለቤት ኤለን መስክና የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የቡጢ ግጥሚያ ሊያደርጉ ነው‼️ የዓለማችን ቁጥር አንድ ቱጃር ኤለን መስክ በትዊተር እንደቀልድ የሰነዘረው “የእንጋጠም” ጥያቄን የፌስቡክ ባለቤቱ ዙከርበርግ ተቀብሎታል። ቢሊየነሮቹ የቦክስ ፍልሚያቸውን በሎስ አንጀለስ ለማድረግ አስበዋል። ኤለን መስክ እንደ ዱቄት እበትነዋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል😂(BBC)። 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇