en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
እገታ የሚባል ነገር ታይቶና ተሰምቶ የማያውቅበት ሀገር ያለን ይመስል ይህን "መናኛ" ዜና እንዲህ ሲቀባበሉት ስናይ ይገርመናል። ከሰሞኑ እንኳን 50 ሹፌሮች እና መንገደኞች ታግተው ከ50 ሚልዮን ብር
እገታ የሚባል ነገር ታይቶና ተሰምቶ የማያውቅበት ሀገር ያለን ይመስል ይህን "መናኛ" ዜና እንዲህ ሲቀባበሉት ስናይ ይገርመናል። ከሰሞኑ እንኳን 50 ሹፌሮች እና መንገደኞች ታግተው ከ50 ሚልዮን ብር በላይ ሲጠየቅባቸው እነዚህ ሚድያዎች አንድ ነገር እንኳን ትንፍሽ አላሉም ነበር፣ አሁን ግን... ⬆️ ሳትታገት ታገትኩ ብላ ብር ጠየቀች፣ ይገርማል፣ ክፉ ድርጊት ነው። ግን ገንዘብ ካልተከፈለባቸው ህይወታቸውን እያጡ ስላሉት ዜጎቻችንስ ማን ይናገርላቸው? ዋናውን ድርጊት ለማስካድ #ማደንዘዣ መሆኑ ነው። #EliasMeseret

ሽመልስ አብዲሳ << ሞቼ ነው ቆሜ የሚፈታው? አይደለም መፈታት ዋስትናም አያገኝም! >> ብሎ የፎከረባቸው አዛውንቱ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ ፥ ዛሬም ለ3ተኛ ቀን ረዥም ሰአት የፈጀውን
ሽመልስ አብዲሳ << ሞቼ ነው ቆሜ የሚፈታው? አይደለም መፈታት ዋስትናም አያገኝም! >> ብሎ የፎከረባቸው አዛውንቱ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ ፥ ዛሬም ለ3ተኛ ቀን ረዥም ሰአት የፈጀውን የመከላከያ ምስክር ሲያሰሙ ውለዋል! በዛሬው ችሎት ፦👇 የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ም/ዳይሬክተር - ረ/ፕ/ር አበባው አያሌው የትምህርት ሚኒስትር - ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ የታሪክ ምሁሩ - ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማሪያም በችሎት ቀርበው የምስክርነት ቃል የሰጡ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም በነበሩት ሁለት ችሎቶች የቀድሞ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ፣ ጋዜጠኛ መስከረም አበራ ፥ ከሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ጨምሮ ሌሎች በርካቶች ቀርበው የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል! ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ በአገዛዙ ጥርስ የተነከሰባቸውና የሀሳብ ነፃነት መብታቸውን ተጠቅመው በእውቀትና በሙያ ያገኙትን እውነታ በሚዲያ በማጋራታቸው ብሎም የስርአቱን አስከፊነትና ህገወጥ ተግባራት በይፋ በሀሳብ በመሞገታቸው ፣ በአንባገነኖቹ ይህ እንደወንጀልና አሸባሪነት ተቆጥሮ ፣ በርካታ የክስ ዶሴ ተከፍቶባቸው በወህኒ ቤት እየተሰቃዩ እንደሚገኙ የሚታወስ ነው! ፍትህ ለጋዜጠኛ ታዲዎስ ታንቱና በአንባገነኖች ወህኒ እየማቀቁ ለሚገኙ በቁጥር እጅግ በርካታ ለሆኑት የህሊና እስረኞች!

"ፖለቲካ በጣም ነው የሚያስጠላኝ።" ይለኛል። "አስጠላህ አላስጠላህ አይለቅህ።" እመልሳለሁ እኔ የዋህ። ትንሽ ቆይቸ ዞር ስል ፖለቲካውን በአስር ጣቱ እያቦካው😂 ኧረ በእግሩም ገባበት😂 አንተ እንደሱ አይደለም ቆይ ቆይ🏃 የገጠመን ችግር!

መንገድ ዳር ወድቆ የነበረው የዚህ ቤተሰብ ህይወት በእናንተ ደጋጎች ርብርብ ተቀይሯል። የተደረገላቸውን ድጋፍ ተጠቅመው አቶ ባሚሌ አበበ እና ባለቤታቸው ወደ ልብስ ስፌት ሙያቸው ሊመለሱ እያሰቡ ነው፣
መንገድ ዳር ወድቆ የነበረው የዚህ ቤተሰብ ህይወት በእናንተ ደጋጎች ርብርብ ተቀይሯል። የተደረገላቸውን ድጋፍ ተጠቅመው አቶ ባሚሌ አበበ እና ባለቤታቸው ወደ ልብስ ስፌት ሙያቸው ሊመለሱ እያሰቡ ነው፣ አሁን ቤት ተከራይተው መኖር ጀምረዋል፣ ልጆቻቸውንም እያስተማሩ ይገኛሉ። ለትብብራችሁ ሁሉ ምስጋና ይድረሳችሁ፣ በተለይ አክሊሉ ተስፋዬ ትልቁን ድርሻ ተወጥቷል፣ እግዚአብሔር ይስጣችሁ። #EliasMeseret

አዲስ አበባ የኔ ብቻ ናት ብሎ ትናንት ለህክምና አንኳ እንዳትገባ የከለከለህ አካል፣አዲስ አበባ የኔ ብቻ ናት ብሎ እየገደለና እያፈናቀለህ ያለ አካል ዛሬ ለቀይ ባህር እንዋጋ ሲልህ ልብህ ሸፍት፣ሸፍት ካለው? Ironically, you need to have a medical check-up to make sure you are not being mocked or mon^keyed!

↖️💦ለመዝናኛ🐇 አንዷ የቦሌ ልጅ መንገድ እየሄደች ውሻ ሲጮህባት... 🐕 ቆይ ይሄ ውሻ Wow! Wow! የሚለው እያደነቀኝ ነው እንዴ አላለችኝም😂😂 #My_sister ለምን ሄደሽ አትፈርሚለትም ያኔ እርግጠኛ ትሆኛለሽ 😄😄 መልካም ቀን🙏 የእናንተዉ ምርጥ ጓደኛ @Gimbamedianwtwork

ለሚረዳው ይህ መረጃ ብቻውን ብዙ ይናገራል! &lt;&lt; የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ከሚጥሱ አገራት ዝርዝር ውስጥ ሊያወጣ መሆኑን ፎርይን ፖሊሲ ዘግቧል፡፡ በአሜሪ
ለሚረዳው ይህ መረጃ ብቻውን ብዙ ይናገራል! << የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ከሚጥሱ አገራት ዝርዝር ውስጥ ሊያወጣ መሆኑን ፎርይን ፖሊሲ ዘግቧል፡፡ በአሜሪካ ግምጃ ቤት ውስጥ ያሉ ምንጮቹንና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን የጠቀሰው ዘገባው ይህ በቅርቡ ሊሆን እንደሚችልና ለኮንግረስ አባላትም እንዲያውቁት መደረጉን አስረድቷል፡፡ ኢትዮጵያ ከዚህ ዝርዝር ውስጥ ከወጣች ከአሜሪካ የምታገኘውና የተቋረጠው የኢኮኖሚ እርዳታ እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡ ይህ የአሜሪካ መንግስት ውሳኔ ሂውማን ራይትስ ዎችና ሌሎችም የመብት ተሟጋቾች ከሚያወጡት ሪፖርትና መግለጫ ተቃራኒ እንደሆነም ጨምሮ ዘግቧል፡፡ >> ዘ-ሀበሻ አሜሪካ የምትፈልገው ''ቅጥረኛ ተዋጊና ጉዳይ አስፈፃሚ '' እንድትሆናት ብቻ ነው!' የአንተ መጨፍጨፍና የሚደርስብህን ገደብ የለሽ ሰቆቃ የምታስተጋባው እጅ ለመጠምዘዝ ያህልና ለፍጆታ እስከዋለ ድረስ ነው!

ለማመን የሚከብድ የአንድ ሰው ህይወት | ፊልም አይደለም እዉነተኛ ታሪክ እንጂ https://youtube.com/watch?v=ulBioJIMZAU&feature=share

ቀይ ባህርም፣ አሰብም አሁን የግጭት ምንጭ ሊሆን አይችልም!  "አዲስ አበባ የእኛ ብቻ ነው" ብለው ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ፣ ከአፍሪካ መዲና ንፃሃንን እያፈናቀሉ ያሉት ገዥዎች "አሰብን በጦርነት እናስመልስ" እያሉ እየቀለዱ ነው! ከሰላም ስምምነቱ በኋላም ትህነግ/ ህወሓት ሲፈነጭ ለአገር አደጋ ነውና አስቁሙት ሲባሉ "ጦርነት ናፋቂዎች፤ ሰላም የማይወዱ" ብለው የዘመቱት ኃይሎች ከጎረቤት አገር ጋር ጦርነት ካልገጠምን እያሉ ነው። "ሸገር"  ብለው ከሰየሙት ከተማ በራሱ አገር በመቶ ሺህ ህዝብ ያፈናቀሉ ነውረኞች፣ ወለጋ አገርህ አይደለም እንዳላሉን ሾለ አሰብ የኢትዮጵያነት ሊቀሰቅሱ መጥተዋል። ኧረ የፈጣሪ ያለህ! ኤርትራና ኢትዮጵያ ሰላም ከፈጠሩ በኋላ የኤርትራን ወደቦች ለመጠቀም ንግግር ተደርጓል። ኤርትራ መንገድ ሰርታ ጨርሳ፣  የእናንተውን ክፈቱ ሲባል አይሆንም ያሉት የአራት ኪሎዎቹ ገዥዎቹ ናቸው። ምክንያቱ ደግሞ ለወደቦቹ በቅርብ ርቀት ያለው አፋርና አማራ ይጠቀማል በሚል ነው። በዚህ ጉዳይ ስብሰባ ተደርጎ "ይቅርብን" ያሉት ራሳቸው በቀጥታ ደንበር ስለሌላቸው ነው። አሁን አሰብ ወዘተ የሚሉት ለአገር አስበው እንዳልሆነ ማንም ያውቃል። የኢትዮጵያ ህዝብ አሁን ወደብ ነው ችግሩ? በአገሩ እንዳይኖር አድርጋችሁ፣ ወደ አዲስ አበባ እንዳያልፍ መንገድ እየዘጋችሁ፣ ከቀየው እያፈናቀላችሁ፣ የእምነት ተቋሙን እያፈረሳችሁ.... ወደብ እናስመልስ ልትሉት? ካለፈው ጦርነት ሳያገግም በየቀየው ዘምታችሁበት፣ አስራችሁት፣ ማዳበሪያ እንኳን ማቅረብ ተሶኗችሁ፣ ባንኩን ባዶ አድርጋችሁ በሌላ አገር ሾር ያለን ወደብ እናስመልስ ብትሉት ሊያምናችሁ? ቀይ ባህርም አሰብም ወቅታዊ የህዝብ ጥያቄ አይደለም። ጥያቄው ቢነሳ እንኳን በሰላማዊ መንገድ ይነሳል እንጅ ህዝብ ጦርነት አይፈልግም። የጦርነት ፍላጎት የውጭ ኃይል ተላላኪነት ነው። ኢትዮጵያ ጦርነት በቃት አላላችሁም? አዎ! ኢትዮጵያ ጦርነት በቃት! #ጌታቸዉሽፈራዉ 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

በመላው ዓለም ላይ የምትገኙ ሙስሊም እህት ወንድሞቸ እንኳን አደረሳች አደረሰን። ኢድ ሙባረክ
በመላው ዓለም ላይ የምትገኙ ሙስሊም እህት ወንድሞቸ እንኳን አደረሳች አደረሰን። ኢድ ሙባረክ

‹‹በመሀል›› ተከታታይ ድራማ ከነገ ሰኔ 19 ጀምሮ ዘወትር ሰኞ ምሽት በ2፡20 በኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ይቀርባል፡፡ ‹‹በመሀል›› እውነተኛ ገፀባህርያትን መሰረት አድርጎ በፈጠራና በህይወት፣ በድርሰትና በእውነት መሀል ላይ የሚያጠነጥን፣ በሲትኮምና በድራማ መካከል የሚመደብ ተከታታይ ድራማ ነው፡፡ 👉subscribe በማድረግ ይከታተሉ👇👇 https://youtu.be/Pm68Ea4nM00?sub_confirmation=1

አሁንም " ሳይቃጠል በቅጠል!" እላለሁ! ተከታዩ ፅሁፍ ከአመት በፊት በዚሁ መንደር ያጋራሁት ቢሆንም ፣ ከሰሞኑ የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ የአማርኛና የታሪክ ትምህርት ክፍሎችን መዝጋቱን ተከትሎ ለማስታወስ ያህል በድጋሜ ልለጥፈው ወደድኩ! 👇👇👇 አሁንም " ሳይቃጠል በቅጠል!" እላለሁ! " ..የታሪክ ሽሚያ - የራሱን ታሪክ መፃፍ የማይችል የመከነ ትውልድ መገለጫ ነው!" ታሪክ ጥሩም ሆነ መጥፎ በታሪክነቱ ተከትቦ ትውልድ ከመልካሙ ታሪክ እንዲማርበትና እንዲያስቀጥለው ፥ እኩይ የሆነውን ታሪክ ደግሞ ዳግም እንዳይከሰት ተግቶ የሚሰራበት ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፍ ቀዲም አሻራ  ነው፡፡ የአሁኑ ትውልድ የሚጠበቅበት ከትናንት ተምሮ ፥ በጎ ታሪኮችን አስቀጥሎ ነገን የመስራትና የራሱን ታሪክ ፅፎ  ፥ ለተተኪው ትውልድ አውርሶ ማለፍ ነው፡፡ ያለፈ ታሪክ ዛሬውንም ሆነ ነገውን እንዲያበላሽ የሚፈቅድና  የትናንቱን የቀድምት አባቶቹን አኩሪ ታሪክ ከመድገም ይልቅ ወደሽሚያ ውስጥ የሚገባ እርሱ ታሪክ መስራት የማይችል የመከነ ትውልድ ነው፡፡ አብይ አህመድ ጠቅላይ ሚንስትር ሆኖ ከመጣ ጀምሮ የታሪክ ትምህርት በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከሀምሳ በላይ  ዩኒቨርስቲዎች መሠጠት አቁሟል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ከዚህ " ቀደምት የነበረው የኢትዮጵያ ታሪክ የእኛ ታሪክ አይደለም!" ብለው የሚያምኑና ለታሪክ ሽሚያ ያሰፈሰፉ ነውረኛ የፖለቲካ ሀይሎች ፥ የሀገረ መንግስቱን ስልጣን በመያዛቸው ነው፡፡ እነዚህ ሀይሎች የቀደምት አባቶቻችንን አኩሪ ታሪክ በብሄር ሚዛን ላይ አስቀምጠው ለቅርጫ የተቀመጡ ብሎም የተፈፀመውንም ሆነ በትርክት የወለዱትን በጎ ያልሆነ ታሪክ ፥ ህዝብን እርስበርሱ በማባላት በደም የጨቀየ አሁናዊው የፖለቲካ ስልጣን ረሀባቸውን ለማስታገስ የሚጠቀሙ ከንቱዎች መሆናቸው የሚታመን ነው፡፡ የዛሬ ሁለት አመት ገደማ የኦሮሞ የፖለቲካ ኤሊት ከሚባሉት አብዛኛዎቹ በተገኙበት መድረክ ላይ የመታደም እድሉን አግኝቼ በውይይታችን ካነሳሁት ጭብጥ መካከል  ፦ << ..ኢትዮጵያ ውስጥ ታሪክን አንሻፎ የሚተረጉም ፥ በክፉም ሆነ በበጎ የነበረውን ታሪክ ያለፈ የኢትዮጵያ ታሪክ ነው ብሎ የማያምን ፥ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አባቶቻችን ስለሀገር ብለው ሰርተው ያለፉትን ታሪክ በብሔር ቅርጫ ላይ አስቀምጦ ለመከፋፈልና ለመነጣጠቅ የሚተጋ ብሎም "ኢትዮጵያ" በምትባለው ሀገር ላይ በጋራ የሚያግባባ ተመሳሳይ ሀገራዊ ብያኔ የሌለው እንዲሁም ስያሜዋን ሁሉ የማይቀበል በፅንፈኝነትና በጥላቻ የሠከረ የፖለቲካ ኤሊት ባለበት ሀገር ፥ ማንኛውን ዘላቂ ሰላምና አብሮት ለማምጣት ነው ለውይይት የተቀመጥነው? ስለየቱ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ነው የምናወራው? ግጭትና እልቂትን እየደገሰ ያሐ የፖለቲካ ኢሊት ስለሰላምና ህዝባዊ አንድነት ለመስበክ መነሳቱ አሽሙር አይሆንምን ? ….. >> የሚል ሀሳብ አንስቼ ተከራክረን ሳንግባባ መለያየታችንን አስታውሳለሁ፡፡ በነገራችን ላይ ከኢህአዴግ/ህወሓት በፊት  በነገስታቶችና በህዝቦች  መካከል  የነበረው ጥሩም ሆነ መጥፎ ታሪክ የተሰራው በሀገራዊ (ኢትዮጵያዊነት) ስሜት እንጂ በብሔር አጥር ሾር አልነበረም፡፡ የሀገርን ሉአላዊነት ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው ከውጭ ወራሪዎች ጋር ካደረጓቸው ጦርነቶችና ካስመዘገቧቸው አኩሪ ድሎች ባሻገር ፥ እርስበርስ ተደረጉ የሚባሉት ግጭቶች  ለስልጣን ሽኩቻ (ንግስና) ካልሆነ በስተቀርም ለብሔር የበላይነት የተደረጉ አለመሆናቸውን በቀና ልቦና የኢትዮጵያን ታሪክ ለሚገነዘብ ሁሉ ግልፅ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ እናም " ለምን?" ብሎ የማይጠይቅ አድርባይና አጎብዳጁ የፖለቲካ ሀይል ፥ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ከመጡ በኃላ በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ እየተሰራ ያለውን ሀገር አፍራሽና ለማንም የማይጠቅም የታሪክ ሽሚያ ማስቆምና መታገል አለመቻሉ ፥ በጥላቻ የሠከረው ፣ ፅንፈኛውና ታሪክ ለመስራት ያልተፈጠረው ይህ የፖለቲካ ቡድን ፥ ከዩኒቨርስቲ የታሪክ ዲፓርትመንት መዝጋት አልፎ ፥ መጪው ትውልድ የሚታነፅበትን ከአንደኛ ደረጃ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተዘረጋ የትምህርት ስርአት ውስጥ የተንሻፈፈ ፣ የተፋለሰ ብሎም ለልሾ ፖለቲካዊ ፍጆታ ማሳኪያነት ብቻ የሚውል ትርክት ተቀርፆ በማስተማሪያነት ሊመጣ ችሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት ነገ ሀገሪቱ አሁን ካለችበት ማጥ መውጣት ቀርቶ ወደከፋ የእልቂት ጎዳና እየተንደረደረች እንደምትገኝ ፥ የተሟላ ጤንነት ያለው ሙሉ ሠው ሁሉ ፣ በቀላሉ የሚረዳው ሀቅ ነው! ሠላም! #ዘሪሁን ገሰሰ 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

#እውነትእውነቷን ድርጊቱ የተከሰተው ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ቀን በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ ነው። አንድ የአካባቢው ሚሊሺያ ራሳቸውን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግስት ደግሞ ሸኔ ብሎ በሚጠራቸው) ታጣቂዎች ይታገታል። ይህንን ምስኪን ሚሊሺያ መሳርያህን እና 100 ሺህ ብር አምጣ እና ትለቀቃለህ ይሉታል። እሱ ደግሞ መሳርያውን ደብቆ ቀብሮ ነበርና "ለመንግስት መልሻለሁ" ብሎ ይነግራቸዋል። ከዛ ግን የሆነው ይገርማል... ታጣቂዎቹ ሚሊሺያው ፊት ሆነው በቀጥታ የደወሉት ለወረዳ አመራሮች ነበር (to be exact ለወረዳው ደህንነት አዛዥ)። ታጣቂዎቹ ሚሊሺያው መሳርያውን ለመንግስት መልሷል ወይስ አልመለሰም ብለው ሲጠይቁ የወረዳው አመራሮች "አልመለሰም" ብለው ይናገራሉ።  ከዛማ ሰውየውን አንጠልጥለው እቤቱ አምጥተው ቆፍሮ ከደበቀበት አስወጡት፣ ስለዋሻቸው ገንዘቡን እጥፍ አርገው 200,000 ብር ወሰዱ፣ ከዛም ለቀቁት። ጊንጪ ከተማ የሆነ ሌላ ታሪክ ልጨምር። ብዙዎችን የሚረዳ አንድ የካቶሊክ ትምህርት ቤት ነበር። ከሶስት ወር በፊት የካቶሊክ ቄሶችን እና ሲስተሮችን ታጣቂዎች አፍነው ወሰዱ፣ ከታገቱት መሀል ህንዳዊ ሲስተር ይገኙበታል። 300 ሺህ ብር በነፍስ ወከፍ ከፍለው አስለቅቀው ከዛ ግን ትምህርት ቤቱን ዘግተው ወጡ። ተጨማሪ ታሪክ፣ የዛሬ 2 ሳምንት በፈረስ ለሸኔ መሳርያ ሊያቀብሉ ነበር የተባሉ ወጣት ተማሪዎች እዛው ምዕራብ ሸዋ ተያዙ። ልጆቹ በትናንትናው እለት እንዲያመልጡ ተደርጓል፣ ጥይት እንደያዙ የጠቆመው ግለሰብ ግን ለእስር ተዳርጎ ይገኛል። በአንድ በኩል መከላከያ እና ፖሊስ የህይወት መስዋዕትነት እየከፈሉ ውጊያ ቢያካሂዱም ጥይት እና የወታደር ኮሾሮ ጭምር ለታጣቂዎቹ እንዲደርሳቸው እያረጉ ያሉት የአካባቢው አመራሮች እንደሆኑ የሚደርሱኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ሌላኛው የሰማሁት ደግሞ ወደ ያቤሎ አቅራቢያ አንድ ግለሰብ ታግቶ ነበር፣ ገንዘብ አምጡ ተብሎ ብር ሲሰበሰብ ትንሽ ቀናት ፈጀ። በመጨረሻም ብሩ ሞልቶ ተላከ፣ ታጣቂዎቹ ግን ገንዘቡን ተቀብለው ታጋቹን ገደሉ። ምነው ብሎ ቤተሰብ እያለቀሰ ሲጠይቅ "በተባላችሁበት ቀን ገንዘቡን አላመጣችሁም" ተባሉ። *በነገራችን ላይ፣ ብዙም የማይወራለት ግን በየቤቱ እየተሄደ እየታገተ እና ስቃዩን እያየ ያለው የኦሮሚያ ህዝብ ጭምር ነው። አንዳንዶች ድርጊቱ ሌሎች ላይ ብቻ ያተኮረ እንደሆነ የሚፅፉት እና የሚናገሩት ትክክል እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል፣ ሁሉም ፍዳውን እያየ ይገኛል። መልካሙን ቀን ያምጣልን። #ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት

50 እና 100 ሰው በታጣቂዎች በገፍ ሲታገት ተከታትሎ የሚያስለቅቅ ኮማንዶ፣ ልዩ ሀይል ወይም የደህንነት አካል የለም? በማታ ጭምር የመብረር አቅም አላቸው የተባሉት ሂሊኮፕተሮችስ ቅኝት እንኳን ለማረግ ሞክረው ይሆን? ሁለት እና ሶስት ሰው ቢሆን ትንሽ ሊያስቸግር ይችላል እንበል፣ ይህ ሁሉ ሰው ታፍኖ ያለበትን ለማወቅ አልተቻለም ሲባል ለማመን ይከብዳል፣ እኔ ከብዶኛል። #EliasMeseret 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork

#ወላሂ_አልቻልኩም😥 ቦርቀው ያልጠገቡ ጨቅላ ህፃናት እየተራቡ አንጀታቸው እህል እየፈለገ የሚበሉት አጥተው  እያነቡ! ትምርት መማር እየፈለጉ ግን በኛ በታላላቆቹ በቆሸሸና በተጨማለቀ ፖለቲካ ምክንያት በዘርና በሀይማኖት እየተከፋፈልን እየተባላን! እነኝህ ምንም የማያውቁ ጨቅላ ህፃናቶች ባልሰሩት ወንጀልና በማያውቁት ሁኔታ ሜዳ ላይ ወድቀው መማር እየፈለጉ ሁኔታዎች ሳይመቻችላቸው ቀርቶ እያዘኑ ፣ እያለቀሱና  እየተከዙ ከማየት ሌላ ምን የሚያም ነገር አለ😥 👉ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇 https://t.me/GimbaMediaNetwork ዜጎችህን በዚህ ሁኔታ እያየህ ስለምን እድገት ነው የምታወራው ስለምን ፍትህ ስለየትኛውስ ህብረትና መቻቻል ነው የሚደሰኮረው😥

ቀጣይ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ? "ለውጥ" አደረግን ተብሎ ምዕራባውያንን ጭምር የወተወቱባቸው ሶስት ተሿሚዎች ናቸው። መአዛ ለቅቃለች። ብርቱካን ቀጥላለች። የቀረው ዶክተር ዳንኤል ነው። እሱንም ቢሆን ትህ
ቀጣይ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ? "ለውጥ" አደረግን ተብሎ ምዕራባውያንን ጭምር የወተወቱባቸው ሶስት ተሿሚዎች ናቸው። መአዛ ለቅቃለች። ብርቱካን ቀጥላለች። የቀረው ዶክተር ዳንኤል ነው። እሱንም ቢሆን ትህነግ እያማረረበት ነው። ደህና ሰሩም አልሰሩም፣ ምዕራባውያን "እነዚህን ከሾሙ አበረታች ነው" ይላሉ ተብሎ የመጡት ሰዎች እየተማረሩ እየለቀቁ ነው። ዶክተር ዳንኤል ላይ ያለው ጫና የሚታወቅ ነው። በጦርነቱ ትህነግ ለምዕራባውያን ያሳየውን ወዳጅነትና የተደረገለትን አይተው ደግሞ እነ ክንድያን አምጥተው ይሾሙ ይሆናል። "ለውጥ" ምናምን ያሉት አፈር ከበላ ቆይቷል። አሁን ምንም አይነት ማስመሰያ እንዳይኖራቸው የቀረው ዳንኤል ነው። ሶስቱን ሰዎች ሾምን ብለው የውጮቹንም አደንቁረው ነበር። የኢትዮጵያን ህዝብም "ከብልፅግና ውጭ ሾምን" ብለው ደጋግመውለታል። አሁን አንድ ብቻ ቀርቷል። በቦታቸው ከትህነግም ወይንም ከቲክቶክ ያመጡ ይሆናል።