en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
ሥልጣንዎን ይልቀቁ ጊዚያዊ የሲቪል አስተዳደር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፓርላማ ይበተን ሙሉ አገሪቷ የደም መሬት ሆኗል በአማራ ክልል የጦርነት አውድማ ተደርጓል እርስዎ የሚመሩት የብልፅግና መንግስት አስተዳ
ሥልጣንዎን ይልቀቁ ጊዚያዊ የሲቪል አስተዳደር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፓርላማ ይበተን ሙሉ አገሪቷ የደም መሬት ሆኗል በአማራ ክልል የጦርነት አውድማ ተደርጓል እርስዎ የሚመሩት የብልፅግና መንግስት አስተዳደር failed leadership የወደቀ አስተዳደር መንግስት መሆኑን አሳይቷል የመፍትሄዉ አካል እንዲሆኑ በጊዜያዊነት ሥልጣንዎን ለቀው ፓርላማዉን በትነው የሲቪል ጊዜያዊ አስተዳደር ቢያዉጁ የተሻለ ነው። ፓርላማ በዚህ ጥያቄ ማለገጡ እንዴት የወረዱ የግለሰቦች ስብስብ መሆኑን አሳይቷል።

➢ ምርት እና አገልግሎቶን በፈለጉት ከተማ እና ቦታ ያስተዋውቁ ➢ የቴሌግራም ፣የፌስቡክ ፣የቲክቶክ፣የኢንስቴግራም እና የዩትዩብ ቻናልዎን በማስተዋወቅ በአጭር ግዜ ብዙ ሺ ተከታዮች ባለቤት ይሁኑ 🔔• የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች ┣➤  Facebook Boost✈️ ┣➤  Instagram Boost✈️ ┣➤  Tiktok Boost✈️ ┣➤  YouTube Boost✈️ ➢ምርትና አገልግሎቶን በተመጣጣኝ ዋጋ ለብዙሀኑ ተደራሽ በማድረግ በእጥፍ ያትርፉ እነኚን ስልኮች ማስታወቂያ ለማሰራት ብቻ ይጠቀሙ •➤አሁኑኑ ያናግሩን 👇 📲 •➤ 0928929452 📲 •➤0904986739 📩 •➤ 𝐈𝐧𝐛𝐨𝐱 𝐌𝐞 ✍️ ለበቂ መረጃ በቴሌግራም 👉 https://t.me/GMN_news👈 ማናገር ይችላሉ❗

➨ እንኳን እኔ እሸቱም ተከራይ ነው 🙄 ➨ ሙሉውን ከታች ባላዉ ሊንክ ሰብስክራይብ በማድረግ ይጠብቁን 👇 https://youtube.com/@HD_Ethiopia ➨ እሽ የልጅ አባት ሁኗል እንኳን ደስ አለህ 🙏

ኢቢሲ በጉማ አዋርድ ላይ ግንባሯን በጥይት መመታቷንና አፏን በሽቦ መለጎሟን በሚያሳይ ሜካፕ የቀረበችውን ፍላጎት አብርሃምን ከስራ አገደ:: ሰኔ 2/2015 ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተካ
ኢቢሲ በጉማ አዋርድ ላይ ግንባሯን በጥይት መመታቷንና አፏን በሽቦ መለጎሟን በሚያሳይ ሜካፕ የቀረበችውን ፍላጎት አብርሃምን ከስራ አገደ:: ሰኔ 2/2015 ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው 9ኛው የጉማ ሽልማት ላይ የወገኗን መታፈን በሜካፕ ያሳየችው የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጇና ታዋቂ ቲክቶከሯ ፍላጎት አብርሃም/የልጅ ማኛ/ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢቢሲ/ ከነበራት የኢትዮጵያን አይዶል የዳኝነት ስራዋ ተሰናብታለች። ሮሃ ቲቪ ከታማኝ ምንጮቿ እንደደረሳት መረጃ ከሆነ ፍላጎት ከዚህ በፊት በአትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የተሰጥኦ ውድድር /ኢትዮጵያን አይዶል/ ላይ በዳኝነት ስራ  ቀረፃዎችን ከውና እንዲሁም ከሚዲያው ጋር ውል ተዋውላ ነበር። ይሁን እንጂ ተቋሙ አዲስ በገነባውና ነገ በሚያስመርቀው የሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንፃ ዛሬ ምሽት በጀመረው የኢትዮጵያን አይዶል ውድድር ላይ በፍላጎት ቦታ ከዚህ ቀደም በውድድሩ የዳኝነት ስራ ላይ ያልነበረው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ተተክቷል። ሚዲያው ፍላጎትን ከዚህ ስራዋ ያገደበትን ምክንያት በግልፅ ማወቅ ባይችሉም ፣ በጉማ አዋርድ ላይ በሜካፕ ባስተላለፈችው መልዕክት ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮቻችን ነግረውናል።

''ቋንቋ '' መግባቢያ እንጂ ፖለቲካ አይደለም! እንደአለመታደል ሆኖ ቋንቋ ፖለቲካ በሆነባትና ዜጎች በሚናገሩት ቋንቋ የሚገለሉባት ፣ የሚገደሉባት ፣ የሚበደሉባት ፣ የሚሸማቀቁባትና ትኩረት የሚያገኙባት ፤ በክ/ዘመኑ ይኖራል ተብሎ በማይታሰብ ፥ የትውልድ የአስተሳሰብ ኃላቀርነት ውስጥ በምትዳክር ሀገር ውስጥ እየኖርን ነው። ቋንቋ ተናጋሪነት የፌደራሊዝም ስርአቱ ቀዳሚ የማዋቀሪያ መስፈርት ተደርጎ ፣ ሌሎች በርካታ አንድ የሚያደርጉንና የሚያቆራኙን መስፈርቶች ተዘለው ፣ ከሰውነት ይልቅ የጎሳ መግባቢያ ቋንቋ ትኩረት ተሰጥቶት ፣ ‘’ቋንቋ’’ የሚለው ቃል ከአውዱ ውጪ እየተተረጎመ ፣ የፖለቲካ ማደራጃና፣ የጥላቻ መሳሪያ ሆኖ ፣ እጅግ ደካማና ኃላቀር በሆነ አስተሳሰባችን ደም ስንፋሰስና ስንራኮት በመኖር ላይ እንገኛለን። በነገራችን ላይ ‘’ማንነት/Identity ''  ለአንድ አካለ መጠን ለደረሰ ሰው ሊተው የሚገባው ግለሰባዊ ምርጫ መሆኑ ያልገባን ፣ ‘’ብሄርተኝነት/nationalism '' የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ እንኳ ፣ የሴራና የጥላቻ ፖለቲከኞቻችን እንደጥብቆ በፍላጎታቸውና ግባቸው ልክ ሰፍተው እንደሰጡን የተቀበልን  ህዝቦች ነን። ብቻ! ይህ ከአጀንዳዬ ውጪና በሌላ ጊዜ የምመለስበት ሰፊ ጉዳይ በመሆኑ ወደተነሳሁበት ነጥብ እገባለሁ። ቋንቋ መግባቢያ ነው። ተግባቦት ደግሞ አብሮ ለመኖር ወሳኙ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ሰዎች እስከተግባቡበት ድረስ የማንም ቋንቋ ከማንም አይበልጥም። የቋንቋ አገልግሎቱ መግባባት መሆኑ ካግባባን ሁሉም ቋንቋ እኩል መሆኑን መገንዘብም ቀላል ነው። ለመግባባትና አብሮ ለመኖር ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠርልንም ቋንቋዎችን መማርና ማወቅን አብዝተን እንድንፈልግ ያደርገናል። ሀገራችን ከ80 በላይ ብሔርና ብሔረሰቦች አሏት። እነዚህ ህዝቦች የተለያዩ የመግባቢያ ቋንቋዎችም አሏት። በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ የሺህ ዘመናት የራሷ ታሪክ ፣ ባህል ፣ ቋንቋዎችና ፊደላት ያላት ቀደምት ሀገርም ነች። በአለም ላይ አብዛኛዎቹ ሀገራት የራሳቸው የሆኑ ፊደላት የላቸውም። ይልቁንም የቅኝ ገዢዎቻቸውን ቋንቋና ፊደላት የሚጠቀሙት በቁጥር የትየለሌ ናቸው። ቋንቋን ከአውዱ ውጪ ለፖለቲካ ፍጆታነት የመጠቀማችን ድንቁርና ከምን ደረጃ እንደሚገኝ በቁንፅሉ ለማስረዳት ፣ በሀገራችን ብዙ ተናጋሪዎች ካሏቸው ቋንቋዎች መካከል አማርኛ እና ኦሮምኛን በምሳሌነት ላንሳ። አማርኛ የሀገሪቱ ብሄራዊ ቋንቋ ከመሆኑ ባሻገር በራሳችን ፊደላትና ቃላት የምንጠቀመው ፥ ከሌላው አለም የሚለየን የኩራት ምንጫችንም ነው። ኦሮምኛ ቋንቋም ከሀገራችን አልፎ በሌሎች ሀገራትም የሚነገር ፣ እምቅ የሆነ ተግባቦታዊ አቅም ያለው ነገርግን ከራሳችን ፊደል ይልቅ የላቲንን ፊደላት ተውሶ የሚጠቀም ትልቅ ቋንቋ ነው። እንደአለመታደል የኦሮሞ ብሄርተኞች ‘’አማርኛ የማይናገር ትውልድ ፈጥረናል!’’ ብለው በኩራት ሲናገሩ ሀፍረት የማይሰማቸውና ቋንቋው እንዳይነገርና እንዲዳከም ሁሉ በትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዳይሰጥ ከማድረግ ጀምሮ የቋንቋው ተናጋሪዎች ላይ ሁለንተናዊ መገለል እስከማድረግ የሚንቀሳቀሱት በአደባባይና በይፋ ነው። ጥቂት የማይባሉ የአማራ ብሔርተኞችም ኦሮምኛ ቋንቋ በተቋማት ሊሰጥ ነው ሲባል ሲጨነቁና ከፖለቲካ ይትባህሉ አኳያ እየበየኑ አሉታዊ ሂስ ሲሰነዝሩ ይስተዋላሉ። በዚህ መካከል ቋንቋ መግባቢያ ነው የሚለው ብያኔ ተረስቶ ፣ የመራኮቻ ፣ የመተራመሻ ፣ ጥላቻና አድሎ የማንፀባረቂያ አጀንዳ ሆኖ በኃላ ቀር አስተሳሰብና በቆሻሻው የፖለቲካ ይትባህላችን ተተብትበን ፤ የባእዳኑን ቋንቋ ለመማር ሀብትና ጊዜአችንን እያፈሰስን የራሳችንን ቋንቋዎች ግን ለማዳከም ሌት ከቀን የምንተጋ ከንቱና አሳፋሪ የአለም ህዝቦች ሆነን እንደምንገኝ በቅጡ መረዳት ያሻናል። ቋንቋ የሚጠቅመው ለራስ እስከሆነ ድረስ ፥ አንችልም እንጂ ቢቻል የሀገራችንን ቋንቋዎች ሁሉ ተምረን ፥ የሌሎች ሀገራትንም ብንጨምር የሚጠቅም ፣ የሚያኮራና አዋቂ የሚያስብል እንጂ የሚጎዳ ነውን ? እኔ በግሌ በሚገባ ከምቀኝበት አማርኛና ግዴታ ሆኖብኝ ተምሬ ከምሰባብረው እንግሊዝኛ ባሻገር ኦሮምኛና ሶማሊኛ ቋንቋዎችን በተወሰነ መልኩ እናገራለሁ። ይህን በማወቄም በተለያዩ አካባቢዎች ስንቀሳቀስ ተግባቦቶቼን አቅልለውልኛል ፣ አግባብተውኛል ፣ ዘመድ ጓደኛ አግኝቼባቸዋለሁ። እንደውም ኦሮምኛና ሶማሊኛ ቋንቋዎች ፣ የላቲንን ፊደል ከሚጠቀሙ የሀገራቸውን ፊደል ተጠቅመው ትውልዱን ቢያስተምሩ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቀላሉ ቋንቋዎቹን ሊለምድና የተግባቦት ደረጃውን ሊያሳድግ ይችላል። ‘’ የሚል የዘወትር ሀሳብና ምኞቴ ነው! ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል፦ በኦሮሞ ህዝብ የታላላቆችን ንግግርና ተረቶች እንደእውቀት ምንጭ ይቆጠራል። ምሳሌያዊ አባባሎች ፣ ተረቶች ፣ አፈ ታሪኮችና የመሳሰሉት የማህበረሰባዊና ፣  ባህላዊ ትውፊቶችን መግለጫና ለትውልዱም ማስተማሪያ ሆነው ያገለግላሉ። ‘’Mammaaksota Oromoo ‘’ በላቲን የተፃፈ ሲሆን ፣ << ማማቅሳ ኦሮሞ >> ብለን በአማርኛ ፊደል መፃፍ እንችላለን። ትርጉሙም << የኦሮሞ አባባሎች >> እንደማለት ነው። ‘’ የነብርን ጭራ አይዙም ፣ ከያዙ አይለቁም!’’ የሚለውን የኦሮሞ ህዝብም የሚጠቀምበት አባባል ፣ << Qeeransa eegee hin qaban qaban hin gadhiisiin. >> ብለን በትውስት የላቲን ፊደል ከምንፅፍ << ቄሬንሳ ኤጌ ሂን ቃበን ፣ ቃበን ሂን ጋዲሲን >> ብለን በራሳችን ፊደል ብንፅፈው ከብሄራዊ ኩራትነቱ ፣ በቀላሉ ሌሎች እንዲማሩት ከማድረጉ ባሻገር የእርስበርስ ትስስርና ተግባቦታችንን አሳድጎ ፣ ‘’  ቋንቋ መግባቢያ ነው!’’ የሚለውን ተሰክክለኛ መስመር እንድንይዝ የተዛባ አስተሳሰባችንም እንዲታረም የሚረዳን ይሆናል! ቋንቋ የሠው ልጆች መግባቢያ እንጂ የጥላቻ ፖለቲካ ማጠንጠኛ ማእከል አይደለም! የአስተሳሰብ ለውጥ እናምጣ! ራሳችንን እንገምግም! ያኔ የሴራ ፖለቲከኞች መጠጊያና መደበቂያ ያጣሉ! ይኸው ነው! ሠላም! #ዘሪሁን ገሰሰ

ትንተና፡ የመገበያያ ገንዘብ ችግር እየተባባሰ በሄደ ቁጥር የኢትዮጵያ ብር እየቀነሰ ለኢኮኖሚው ከባድ ፈተናዎች እየፈጠረ ነው። ይፋዊው ተመን አሁን በዶላር 55 ብር አካባቢ በማንዣበብ፣ የሃርድ ምንዛሪ እጥረት አሁን የአንድ ዶላር የጥቁር ገበያ ዋጋ ከ110 ብር በላይ እንዲሆን አድርጎታል። ከ100% በላይ የሆነው ይህ የተጋነነ ፕሪሚየም በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ ጉልህ የሆነ ክስተት ነው። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመገበያያ ገንዘብ ዋጋ እያሽቆለቆለ ከሚገኙ ሀገራት ተርታ ትሰለፋለች። በጥቁር እና በስፖት ገበያ ላይ ያለውን የምንዛሪ ዋጋ የሚከታተለው የችግር ገንዘቦች ፕሮጀክት በቅርቡ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከጥር 2022 ጀምሮ የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር በ40 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል። *** ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት በተለያዩ ዘርፎች አስመጪዎች አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። በተለይ እንደ ማኑፋክቸሪንግ፣ግብርና እና ኮንስትራክሽን ያሉ ኢንዱስትሪዎች በዚህ ቀውስ ክፉኛ ተጎድተዋል። እንደ አለመታደል ሆኖ፣ እንደ መድኃኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች ያሉ አስፈላጊ ዕቃዎችን በማስመጣት ላይ የተሳተፉት እንኳን ከጉዳቱ አላዳኑም። ብሩህ ተስፋ ፋርማሱቲካልስ አስመጪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ላለፉት አምስት አመታት መድሀኒቶችን እና የህክምና ቁሳቁሶችን ከውጭ አስመጥቶ ለጅምላ አከፋፋይ ሲያከፋፍል ቆይቷል። ይሁን እንጂ ኩባንያው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሥራውን ለማስቀጠል በቂ የሆነ የሃርድ ምንዛሪ ለማግኘት ተግዳሮቶች አጋጥመውታል። *** በብሩህ ተስፋ ፋርማሲዩቲካል የፋርማሲዩቲካል ቁጥጥር ጉዳዮች አማካሪ አቶ አበባው ገሠሠ “በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ደብዳቤ ለመክፈት ሒደቱን ከጀመርን ሁለት ዓመታት ተቆጥረዋል” ብለዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኩባንያው 50,000 ዶላር የሚያወጣ የብድር ደብዳቤ ማግኘት አልቻለም። #አድስ ስታዳርድ Telegram ጆይን 👉  https://t.me/Gimbamedianetwork

በሐዋሳ ከተማ ግብረሰዶማዊነትን የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ:: በትናንትናው እለት በሲዳማና በደቡብ ክልሎች መቀመጫ በሐዋሳ ከተማ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ/ግብረሰዶማዊነትን/ እና ጽንስ ማቋረጥን የሚያወግዝ
በሐዋሳ ከተማ ግብረሰዶማዊነትን የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ:: በትናንትናው እለት በሲዳማና በደቡብ ክልሎች መቀመጫ በሐዋሳ ከተማ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ/ግብረሰዶማዊነትን/ እና ጽንስ ማቋረጥን የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሒዷል። ሰልፉን ያዘጋጁት በከተማዋ ከሚገኙ 22 የቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ-ክርስቲያናት የተውጣጡ ምዕምናን ናቸው። ሠልፈኞቹ ከትላንት በስቲያ እሁድ በከተማዋ ዋና ዋና ጎዳናዎች እየተዘዋወሩ ባሰሙት መፈክር የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ እና ጽንስ ማቋረጥን አውግዘዋል። ሠልፈኞቹ በተመሳሳይ ፆታዊ ግንኙነት እና በውርጃ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ያሰሙት የጹሁፍ መልዕክቶችን በማንገብና መፈክሮችን በማሰማት ነው ፡፡ ሠልፈኞቹ ካሰሟቸው መፈክሮች መካከል “ ግብረ ሶዶማዊነትን እንቃወማለን “ ፣ “ ጽንስ ሕይወት አለው “ ፤ “ ህይወትን መግደል ሀጢያት ነው “ የሚሉ ይገኙባቸዋል ፡፡ የተቃውሞ ሠልፉን ያካሄዱት በሀዋሳ ከተማ ከ22 የቃለ ህይወት አጥቢያ ቤተክርስቲያናት የተሰባሰቡ ምዕመናን መሆናቸውን ከሠልፉ አስተባባሪዎች አንዱ መጋቢ ፍፁምዘለቀ ይናገራሉ ፡፡ ሠልፉ ያስፈለገበት ምክንያትም አገር ፣ ከተማ ፣ ህዝብ እንዲነቃ ለማድረግ መሆኑን የገለጹት መጋቢ ፍፁም “ ህዝቡ ጉዳዩን እንደተራ ነገር ሊያየው አይገባም ፡፡ አስከፊነቱን ሊረዳ ይገባል ፡፡ አዲስ ነገር አይደለም እየተባለ በማህበረሰቡ ውስጥ ሥፍራ እያገኘ ወጣቶችንም ከመንገድ እያስቀረ ይገኛል ፡፡ ሠልፉ ህብረተሰቡ ይህን እንዲውያቅ ለማድረግ የታሰበ ነው “ ብለዋል፡፡ Telegram 👉 https://t.me/Gimbamedianetwork

'' እስከ 40 ሺህ የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች ተገድለዋል'' ተባለ ! በኢትዮጵያ የመንግሥት ለውጥ ከተደረገበት 2010 ወዲህ ባሉት ዓመታት ከ25 ሺሕ እስከ 40 ሺሕ የሚገመቱ የአማራ ተወላጆች በአክራሪ ብሔርተኞች መገደላቸውን ካውንተር ፓንች በድህረ ገጹ አስነብቧል። ዘገባው አብዛኞቹ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በሚል በሚጠራው እና በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በተፈረጀው ኃይል የተገደሉ መሆናቸውን መገለጹን አዲስ ማለዳ ከድህረ ገጹ ዘገባ ተመልክታለች፡፡ ከዚህ ባለፈም ፤ ከአምስት እስከ ሰባት ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸው ነው የተገለጸው። እንዲሁም በአገሪቱ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ከጊዜ ወደ ጊዜ አደጋ ውስጥ እየገባ ነው የተባለ ሲሆን ፤ የመሰበሰብ ፣ የሚዲያ ነጻነት እና ሌሎች ተያያዥ ዴሞክራሲያዊ መብቶች አደጋ ውስጥ መግባታቸው ተጠቅሷል። በዚህም ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ በግልጽ የሚናገሩ ጋዜጠኞች እና የግል የሚዲያ ተቋማት በነጻነት የመናገርና የመስራት መብታቸውን አጥተዋል ሲል የካውንተር ፓንች ዘገባ አመላክቷል። ዘገባው መሰረቱን በአሜሪካ ያደረገ “ፍሪደም ሃውስ” የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትን መረጃ ጠቅሶ፤ በኢትዮጵያ በስፋት መንግሥትን የሚተቹ አካላት ከእውቅናቸው ውጭ በሆነ መንገድ በመንግሥት የደህንነት አካላት በእጅ ስልካቸው ላይ ሳይቀር ሚስጥራዊ ክትትል እንደሚደረግባቸው ጠቁሟል። በአገሪቱ የዘፈቀደ እስራት በተደጋጋሚ እንደሚፈጸም በመጥቀስም፤ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ አክቲቪስቶች እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞች ከመኖሪያ ቤታቸው፣ ከሥራ ቦታቸው ወይም ከመንገድ ላይ  ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በደህንነቶች ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ እንደሚወሰዱመወ ተገልጿል። በአገሪቱ ሥር የሰደደ ሙስና መኖሩን የጠቀሰው ዘገባው፤ ገንዝብ ተቀብለው ፍርድ የሚያጣምሙ ዳኞች ላይ ሳይቀር ያለው ተጠያቂነትም እምብዛም ነው ብሏል። የጋዜጠኞች መብት ተማጋች ሲፒጄ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች ነጻነት አሳፋሪ ገጽታ እንዳለው በመጠቆም፤ ባለስልጣናት የታሰሩትን ጋዜጠኞች በሙሉ ሊለቁ እንደሚገባና እስር ቤት ውስጥ በነበሩበት ወቅት በደል ወይም ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል የሚለውን መመርመር ብሎም ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባቸው ማሳሰቡ ይታወሳል። አብዛኛው የአገሪቱ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ ጥሎበት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር፣ ቀስ በቀስ ራሱን ወደ አምባገነናዊ ስርዓት እየለወጠ ነው ሲልም ካውንተር ፓንች በዘገባው አመላክቷል። //ዘገባው - የአዲስ ማለዳ- ማክሰኞ ሰኔ 27 ቀን 2015 ነው//

ውብ አገር ውብ መሬት ለም አፈር ልዮ ተፈጥሮ ያላት አገር ይዘን፣ ዘመኑን በማይመጥን ሀሳብ እራሳችንን እያጠፋን በተስፋ ነገን ሞልተን የምንራመድ ህዝቦች ነን። አለምን ከመለን ይልቅ መለመንን ከመልመ
+3
ውብ አገር ውብ መሬት ለም አፈር ልዮ ተፈጥሮ ያላት አገር ይዘን፣ ዘመኑን በማይመጥን ሀሳብ እራሳችንን እያጠፋን በተስፋ ነገን ሞልተን የምንራመድ ህዝቦች ነን። አለምን ከመለን ይልቅ መለመንን ከመልመድ ይልቅ አለምን የምንመግብ ሰዎች ነን፣ ዛሬ የአሜሪካ እርዳታ ቀረ ብለን በድንጋጤ የተዋጥነው። ለምኖ የተቀየረ የለም ሰርቶ ታሪክ የቀየረ እንጅ። አገርን በዘር ገመድ በጣጥሰን የሰውን ልጅ በልዮነት ቆፈን ቀፍድደን አስረን ሰለ ባህር በር መጨነቅ አያስፈልገንም። አንድ ፓስፖርት ይዘን በአገር ውስጥ መታወቂያ የምንገዳደል ሰዎች ስለ ቀይ ባህር መጨነቅ የለብንም። መጀመሪያ እስቲ በአገር ውስጥ የመኖር የመስራት ሀብት የማፍራት መብታችንና እንቅልፍ በነፃነት የምንተኛበት መጠለያ ቤታችን ዋስት ይረጋገጥልን። ምስል ሙሉ ነህ ዮዎናስ ሱሌማን አብደላ

በጭራሽ አልፀፀትም! ከአማራ ህዝብ ጎን በመቆሜ በጭራሽ ፀፀት አይሰማኝም፣ ከአማራ ህዝብ ጎን መቆም አድርባይነት አይደለም ለእውነት መቆም እንጂ! ልጆቼ ከዚህ በላይ መከራ ቢደርስብኝ ስለ እውነት እን
በጭራሽ አልፀፀትም! ከአማራ ህዝብ ጎን በመቆሜ በጭራሽ ፀፀት አይሰማኝም፣ ከአማራ ህዝብ ጎን መቆም አድርባይነት አይደለም ለእውነት መቆም እንጂ! ልጆቼ ከዚህ በላይ መከራ ቢደርስብኝ ስለ እውነት እንጂ ስለ አማራ አይደለም። ይልቅስ እውነትን ችላ ብዬ ለሆዴ ብሰለፍ ያኔ ይፀፅተኝ ነበር። ስጋዬ ነፃ ቢሆንም መንፈሴ እስረኛ ነበር። አሁን በሚገርም ሁኔታ ውስጤ ሰላም ነው። የታሪክ ፀሀፊ እና ጋዜጠኛ ታዲዎስ ታንቱ

ሁሌም አነቃቂ መልእክቶችን ከፈለጋችሁ Join➨ https://t.me/HD_Ethiopia

በ2023 በአለም ላይ ለጎብኝዎች በፍጹም ከማይመከሩና እጅግ አደገኛ ከተባሉ 10 ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንደኛዋ መሆኗን ያውቃሉን ? በየአመቱ የሀገራትን የሰላምና ደህንነት ሁኔታ ተገምግሞ ደረጃ በሚሰጥበት The Global Peace Index እ.ኤ.አ በ2023 በተቀመጡ መመዘኛ መስፈርቶች መሠረት የ163 ሀገራትን ደረጃ ተለይቶ  ይፋ ተደርጓል። በዚህ የደረጃ ሠንጠረዥ መሠረት ከግርጌ ያሉት አስር  ሀገራት << በአለም ላይ ለጉዞና ለጎብኚዎች ፍፁም የማይመከሩ አደገኛ ሀገራት >> ተብለው ተቀምጠዋል። በዚህ መሠረት ሀገራችን ኢትዮጵያ ከ163 ሀገራት በ2.80 የGPI ነጥብ 151ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥና ከአፍሪካ 8ተኛ ተራ ቁጥር ላይ ሰፍራ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተተች ሀገር ሆናለች። ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት በበኩሉ ፤ << ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ደረጃ-3/level 3  የጉዞ አማራጭ ሀገር ነች>>  ሲል መመደቡ የሚታወስ ነው። ይህ ማለት << የሀገሪቱ ሁኔታ እስከሚስተካከል ድረስ ፍፁም ለጉዞና ለጉብኝት አትመከርም! >> እንደማለት ነው። በGPI የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ ፣  በሀገሪቱ ያሉ የሽብርና የእገታ ወንጀሎች መስፋፋት ፣ የእርስበርስ ግጭቶች  ፣ ያልተረጋጋና ረፍት አልባ ህዝብ መኖሩ ፣ የወንጀል ድርጊቶች እየተበራከተ መምጣት ፣ በጎረቤት ሀገራት ድንበሮች አካባቢ ያሉ የደህንነት ስጋቶችና በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ችግሮች በቀጠና ተለይተው በዝርዝር ተቀምጠዋል። በአለም ላይ ለጎብኚዎች መረጃ የሚሰጡ ድህረ-ገፆችና ሌሎች ሚዲያዎች ፣ አስጎብኚ ድርጅቶች ፣ የሀገራት ኤምባሲዎች ወዘተረፈ  <<...According to GPI ranking, Ethiopia is considered one of the most dangerous countries in Africa. >> እያሉ ሲያስተጋቡ መመልከት ልብን ቢያሳምምም ፣ እውነታው ግን ይኸው ነው! በሁለንተናዊ መልኩ ፣ ሁለንተናዊ በጎ ገፅታዋንና ክብሯን እያጣች ያለች ሀገር-ኢትዮጵያ! Fact check links 👇 https://travellersworldwide.com/most-dangerous-countries-in-africa/ https://reliefweb.int/report/world/global-peace-index-2023 https://www.gfmag.com/global-data/non-economic-data/most-peaceful-countries

ኢትዮጵያ በ2023 በከፍተኛ ሁኔታ እየፈራረሱ ካሉ 12 የአለም ደካማ ሀገራት (fragile States) ተርታ ተመድባለች! በየአመቱ ደካማ/የወደቀ (failed/fragile) መንግስት ያላቸውን ሀገራት መዝኖ በደረጃ የሚያስቀምጠው Fund for peace /FFP/ የተሰኘው አለምአቀፍ ተቋም እኤአ በ2023 አጠቃላይ የአለም ሀገራትን በተለያዩ መመዘኛዎች መዝኖ ደረጃቸውን አስቀምጧል ። በዚህም መሠረት እጅግ በጣም ከፍተኛ እና በጣም ከፍተኛ የወደቀና ደካማ መንግስት ካላቸው ሀገራት ተርታ ኢትዮጵያ ተካታለች። እጅግ በጣም አስከፊ የመፍረስ አደጋ ውስጥ ከተካተቱት 12ቱ ሀገራት መካከል ወደ7 የሚሆኑት የአፍሪካ ሀገራት ሲሆኑ ከዚህም ውስጥ ኢትዮጵያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሱዳንና ሶማሊያ የምስራቅ ሀፍሪካ ሀገራቶች ናቸው። ለግዛት መፈራረስ/ State Fragility ዋና ዋና ምክንያቶች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል፦  የአስተዳደር ድክመት/Weak governance ፤ የአስተዳደር አቅም ውስንነት (limited administrative capacity) ፤ ስር የሰደዱ ሰብአዊ ቀውሶች (chronic humanitarian crises) የማያቋርጡ ማኅበራዊ ውጥረቶች ( persistent social tensions) እና ብዙ ጊዜ ሁከት ወይም የትጥቅ ግጭት እና የእርስ በርስ ጦርነት (violence or the legacy of armed conflict and civil war) ከብዙ በጥቂቱ የሚገለፁ ናቸው። የግዛት መፈራረስ/ State Fragility  ምን  ማለት ነው? እንደ Fund for peace /FFP/ አገላለጽ ደካማ የሆኑና በመፈራረስ ላይ ያሉ ሀገራት በርካታ መገለጫ ባህሪያት ያሏቸውና በተለያዩ መንገዶች ሊገለፁ የሚችሉ ቢሆንም በጣም ከተለመዱት እየፈራረሱ ያሉ ሀገራት መገለጫ ባህሪያት መካከል አንዳንዶቹ የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ። -የግዛቱን አካላዊ ቁጥጥር ማጣት ወይም በሕጋዊው የኃይል አጠቃቀም ላይ ያለው ጠቅላይነት / The loss of physical control of its territory or a monopoly on the legitimate use of force -የጋራ ውሳኔዎችን ለመወሰን የህጋዊ ስልጣን መሸርሸር/ The erosion of legitimate authority to make collective decisions -መሠረታዊ የህዝብ አገልግሎቶችን ለማቅረብ አለመቻል/ An inability to provide reasonable public services -እንደ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሙሉ አባል ከሌሎች ሀገራት ጋር ጤናማና የተሳካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማድረግ አለመቻል/ The inability to interact with other states as a full member of the international community. ከብዙ በጥቂቱ የቀረቡ ማሳያዎች መሆናቸውን ይገልፃል። Fund for peace /FFP/ የሀገራቱን ደረጃ ለመለየት በመመዘኛነት ከተጠቀማቸው 12 መለኪያ መስፈርቶች መካከል ፦  መጠነ ሰፊ የሙስና ወንጀልና የወንጀል ባህሪ ፤ የዜጎችን ሁለንተናዊ ድጋፍ ማጣትና ግብር መሰብሰብ አለመቻል ፣ የዜጎች ያለፍላጎትና በአስገዳጅ የጥቃት ሁኔታ መፈናቀል ፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ውድቀት፣ በቡድን ላይ የተመሰረተ ኢ-ፍትሀዊነት ፣ ተቋማዊ ስደት/መፈናቀል ወይም መድልዎ ፣ ከባድ የስነ-ሕዝብ ጫናዎች ፣ አእምሯዊ ፍልሰት (brain drain)  እና በተለያዩ ግዛቶች በተለያዩ ጊዜያት የሚፈፀሙ አሰቃቂና በጭካኔ የተሞሉ ወንጀሎችና ግጭቶች መበራከት የመሳሰሉት ይገኙበታል። Fund for peace /FFP/ የልየታ ነጥብ መሠረት ከ100 ነጥብ በላይ ያገኙና እጅግ በጣም ከፍተኛና በጣም ከፍተኛ በሚል ደረጃ የተቀመጡት 12ቱ ሀገራት ፦ ሶማሊያ ፣ የመን ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፣ ሶሪያ ፣ አፍጋኒስታን ፣ ሱዳን ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ፣ ቻድ ፣ ሀይቲ ፣ ኢትዮጵያ እና ማይናማር ናቸው።