en
Feedback
Ethiopia Studio 🇪🇹

Ethiopia Studio 🇪🇹

Open in Telegram

አስመሳይ ሆኖ ስኬታማ ከመሆን ራሱን ሆኑ መወደቅ መልካም ነው ⁉️

Show more
902
Subscribers
-124 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
መንግስት ላለፉት 5 ወራት የኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ባደረገው አፈና በሀገሪቱ ላይ የደረሰው ኪሳራ የ5 ክልሎችን የቀጣይ አመት በጀት ይሸፍናል! የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ከሁለት አመት በፊት ባወጣው ዘገባ መሠረት ፣ ኢትዮጵያ በችግኝ አለመፅደቅ በየአመቱ - 65 ቢሊየን ብር ትከስራለች! ኢትዮጵያ ላለፉት 5 ወራት ኢንተርኔትን በማፈኗ - 27, 809, 526 ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ኪሳራ ደርሶባታል! በብላክ ማርኬት (መንግስትም የሚገዛው በብላክ በመሆኑ ነው) የ100 ብር ተመን ስንመታው 2,780,952,600 ማለት ነው። በዚሁ ምክንያት በጠቅላላ የምርት ኪሳራ ደግሞ 140,364,537 ዶላር ከስራለች! ወደኛ ሀገር ገለባ ስንመታውም 14,036,453,700 ብር ይሆናል። በኢንተርኔት አፈናው ብቻ በጥቅሉ 16,817,406,300 ሀገራዊ ኪሳራ ደርሷል። በዚህ አመት ከፕሮፓጋንዳ ችግኝ ተከላ የምትከስረውንም በ65 ቢሊየን ብር እንኳ ብናሰላው የሁለቱ ድምር 81,817,406,300 ብር ይሆናል። ይህ ደግሞ የደቡብ ፣ የሲዳማ ፣ የአፋር ፣ የሶማሌ ፣ የትግራይ ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ፣ የቤኒሻንጉል ፣ የጋምቤላ ክልሎችን የ2016 ዓ.ም አመታዊ በጀት ይሆናል። ከኦሮሚያ ክልል በጀት በ10 ቢሊየን ይበልጣል ፣ የአማራ ክልልን በጀት እጥፍ ሊሆን የሚጎድለው 9 ቢሊየን ብቻ ነው! የኢንተርኔቱ አፈና ያደረሰው የ5 ወር ኪሳራ ብቻውን ደግሞ የአዲስአበባ ፣ የሀረሪ ፣ የድሬደዋ ፣ የቤኒሻንጉል ፥ የጋምቤላ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አመታዊ በጀት ሸፍኖ ትርፍ አለው! ይቺ እንግዲህኮ ለእነሱ ከጆሮ የማትገባው ፣ ጥቃቅንና አነስተኛዋ ሀገራዊ ኪሳራ ነች!😜 የጧት ማታ መፈክሩ ግን '' ብልፅግናችንን እያረጋገጥን ነው!'' ይላል! እንደሀገር ብስቁልናችን ግን በታሪክ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ሁኔታ ላይ ደርሷል! ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/gimbamedianetwork

አባ ሳዊሮስ የእነ አባ አብርሃምንና አባ ጴጥሮስን መሰደብ በስልካቸው ሲቀርፁና ፎቶ ሲያነሱ ይታያሉ። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/gimbamedianetw
አባ ሳዊሮስ የእነ አባ አብርሃምንና አባ ጴጥሮስን መሰደብ በስልካቸው ሲቀርፁና ፎቶ ሲያነሱ ይታያሉ። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/gimbamedianetwork

የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የወሰዷቸውን ወረዳዎች በደቡብ ሱዳን ስር አዋቅረዋቸዋል ተባለ‼️ ታጣቂዎቹ ንጹሃን ዜጎች ላይ የሚያደርሱት ጥቃት እንደቀጠለ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ትኩረት እንዲሰጠው ተጠይቋል። ማንዱር እና ተማር የተባሉ ሁለት ወረዳዎችን ተቆጣጥረው ወደ ደቡብ ሱዳን አካለዋቸዋል ተብሏል። ለወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ👇👇👇👇 join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

~ ~ *** የአምቡላንስ ግፍ *** _____________________________ • የእናቶችና የህጻናት እንባ ያጠፋችሗል። ለነብሰ ጡር እናቶችና ህጻናት እንዲሁም ድንገተኛ ታማሚዎች አገልግሎት እ
+1
~                                       ~ ***     የአምቡላንስ  ግፍ     *** _____________________________      • የእናቶችና የህጻናት እንባ ያጠፋችሗል። ለነብሰ ጡር እናቶችና ህጻናት እንዲሁም ድንገተኛ ታማሚዎች አገልግሎት እንዲውል መንግስት ከፍተኛ ወጪ አውጥቶ የሚገዛቸው አምቡላንሶች የግል ንግድ ቡናና ማር ማጓጓዣ፣ የሽያጭ በግና ፍየል ማመላለሻ፣ የሙሽራ  ማጀቢያ እና የሆቴሎች የንግድ ቢራና ለስላሳ ማመላለሻ ከሆነ ሰነባብቷል።     * እናቶች በወሊድ ምክንያት ሆስፒታል መድረስ አቅቷቸው እየሞቱ ህይወታችሁን ላይቀይር ለጥቂት ልቅምቃሚ ብር ብላችሁ ጸያፍ ሾል የምትሰሩ አመራሮችና የአምቡላንስ ሹፌሮች ፍርዱን ከፈጣሪ ትቀበላላችሁ ! join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork    ሸር በማድረግ መልእክቱን እናሰማ !!!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በተፈፀመ ጥቃት ቢያንስ 18 ሰዎች መገደላቸውን የዐይን እማኞች ተናገሩ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን፣ ግልገል በለስ ከተማ በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን እና የአካል ጉዳት መድረሱን የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ። የዐይን እማኞቹ እንዳሉት ባለፈው አርብ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም. ከቀኑ 11 ሰዓት ተኩል ገደማ በተፈፀመው ጥቃት ቢያንስ 18 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን በርካቶች ቆስለዋል። ጥቃቱን ያደረሱትም በቅርቡ ከትጥቅ ትግል በመውጣት በከተማው ቅርብ ርቀት ላይ የሰፈሩ ታጣቂዎች መሆናቸውን የዐይን መስክሮቹ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በክልሉ የሚንቀሳቀሰው ቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ) ባወጣው መግለጫ፣ እስካሁን ትጥቃቸውን ያልፈቱ የጉሙዝ ሕዝብ ዴሚክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) ታጣቂዎች በግልገል በለስ ከተማ ሰኔ 30 በፈፀሙት ጥቃት በርካታ ንፁሃን ዜጎች መገደላቸው እና በርካቶች መቁሰላቸውን አረጋግጧል። ፓርቲው ድርጊቱ በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው አስነዋሪ እና አሳፋሪ መሆኑን በመግለጽ አውግዟል። ግድያውን የፈጸሙ አካላት በአፋጣኝ ለሕግ እንዲቀርቡም ፓርቲው ጠይቋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የዐይን እማኞች፣ በጥቃቱ ቢያንስ የ18 ሰዎች ሕይወት ማለፉን እና 16 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መግባታቸውን ተናግረዋል። “በአካባቢው 'በመንግሥት የሚቀለቡ' ሽፍቶች አሉ” የሚሉት የዐይን እማኙ፣ ታጣቂዎቹ ከባድ መሣሪያ ታጥቀው ከተማ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱም ይናገራሉ። መንግሥት በክልሉ የሕዝቡን ደኅንነት እና ሰላም ለመጠበቅ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ሲገልጽ የቆየ ቢሆንም፣ የዐይን እማኙ ግን በሚኖሩበት አካባቢ “የሚደረገውን እናያለን። እየሆነ ያለው ነገር ያሳዝናል። መንግሥት የአካባቢውን ሕዝብ እያስተዳደረ አይደለም” ሲሉ ወቅሰዋል። አርብ ዕለት የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎም የአካባቢው ነዋሪዎች ከብቶቻቸውን እየነዱ ወደ ፓዌ መፈናቀላቸውን እና ከተማ ውስጥም የትራንስፖርትም ሆነ ሌላ እንቅስቃሴ መቆሙን እኚሁ የዐይን እማኝ ተናግረዋል። ሌላው ቢቢሲ ያነጋገራቸው የዐይን እማኝም ለጥቃቱ ተጠያቂ ያደረጉት “በሰላም ስምምነት ተመላሽ ተብለው ለመንግሥት እጅ ሰጥተዋል የተባሉት ታጣቂዎችን” ነው። ከቻግኒ ወደ ፓዌ መስመር የሚሄዱ ተሽከርካሪዎችን በማገድ ተሳፋሪ ላይ በመተኮስ እና ቦንብ በመወርወር ጥቃት መፈፀማቸውን የተናገሩት ግለሰቡ፣ በጥቃቱ ቢያንስ 18 ሰዎች መገደላቸውን እና ቢያንስ 12 ሰዎች መቁሰላቸውን ተናግረዋል። “አርብ አመሻሽ አካባቢ ላይ የተጀመረው ጥቃት ጋብ ያለው በጨለማ እና በዝናብ ምክንያት ነው” ሲሉም በአፋጣኝ የደረሰላቸው የፀጥታ አካል እንደሌለ ጨምረው ተናግረዋል። ጨምረውም እሁድ ሌሊት ለሰኞ አጥቢያ ተኩስ ነበር የሚሉት ነዋሪው፣ ተመሳሳይ ጥቃት ይደርስብናል በሚል ስጋት ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እየወጡ ነው ብለዋል። “ታጣቂዎቹ የሰላም ጥሪን ተቀብለው ከጫካ ወጡ ቢባልም፣ መሣሪያቸውን አላስረከቡም” ይላሉ የዐይን እማኙ። ጥቃቱን በተመለከተ ቢቢሲ ከአካባቢው አስተዳር እና የፖሊስ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት በተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም። ታጣቂ ቡድኑ የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ከዚህ ቀደም በመተከል አካባቢ የተለያዩ ጥቃቶች እና እገታዎች በመፈፀም ይከሰሳል። ቡድኑ “የጉሙዝ ሕዝብን ነጻ እናወጣለን” በሚል ታጥቆ በአካባቢው እንደሚንቀሳቀስም ይነገራል። ከዚህ ቀደም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በመተከል ዞን የታጣቂ ቡድን አባላት በሰላማዊ መንገድ ተስማምተው ትጥቃቸውን መፍታታቸውን በተደጋጋሚ መግለጹ አይዘነጋም። ቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤ የክልሉ መንግሥት በደረሰው ስምምነት መሠረት የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ ፈትተው የተሃድሶ ሥልጠና ከወሰዱ በኋላ ወደ ኅብረተሰቡ ይቀላቀላሉ ቢባልም የሚታየው ይህንን የሚያረጋግጥ እንዳልሆነ አመልክቷል። አክሎም ታጣቂዎቹ ትጥቅ ሳይፈቱ ማኅበረሰቡ ውስጥ የሚያደረጉት እንቅስቃሴ በተለይም የመንግሥት የፀጥታ አካላትን ሚና ተክተው የሚያደረጉት እንቅስቀሴ በአስቸኳይ እንዲቆም እና ትጥቅ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ከዚህ ቀደም ማሳሰቡን ፓርቲው አስታውሷል። በክልሉ በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሥልጣን በመጡ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት በተደጋጋሚ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋዎች ተፈጽመው በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም አካባቢያቸውን ለቀው ለመፈናቀል ተገደዋል። ጥቃቱን ለማስቆምም በተለያየ ጊዜ የክልሉ መንግሥት ከታጣቂዎች ጋር አደረኩት ያለውን ስምምነት ተከትሎ የተወሰኑ የታጣቂዎቹ አባላት የሰላም ትግል ለማድረግ መሣሪያ ማስረከባቸው መገለጹ ይታወሳል። በዚህም በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈፀመው ጥቃትም ጋብ ብሎ ቆይቶ ነበር። በክልሉ የትጥቅ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ ሕይወት ለመመለስ መስማማታቸው ከተገለጸ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ የተፈጸመው ጥቃት እና ግድያ ከፍተኛው ነው። መረጃው የቢቢሲ አማርኛ ነው!! join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

በፌስቡክ ፣በቴሌግራም ማስታወቂያዎችን እና ቻናላዎን ወይም ምርትና አገሌግሎትዎን ለማስተዋወቅ ያናግሩን👇👇 https://t.me/GimbaChat

ይህ ሰው ሚስተር ሳይ ይባላል ። የሆነ ጊዜ ወደአውሮፓ መሄድ ፈልጎ በ500 ሺ ዶላር የገዛትን ሮል ሮይስ መኪናውን አስይዞ 500 ዶላር ብድር እንዲሰጠው ጠየቀ ። ተፈቀድለትና ዶላሩ ተሰጠው ። እሱም
ይህ ሰው ሚስተር ሳይ ይባላል ። የሆነ ጊዜ ወደአውሮፓ መሄድ ፈልጎ በ500 ሺ ዶላር የገዛትን ሮል ሮይስ መኪናውን አስይዞ 500 ዶላር ብድር እንዲሰጠው ጠየቀ ። ተፈቀድለትና ዶላሩ ተሰጠው ። እሱም የመኪናዋን ቁልፍ ሰጥቶ ሄደ ። የባንኩ ሰራተኛም መኪናዋን እየነዳ ወደባንኩ የመኪና ማቆሚያ አስገብቶ አቆማት ። ከሳምንት በኃላ የባንኩ ማናጀርና የብድር መኮነኑ የሚስተር ሳይን አካውንት ሲያዩት ብዙ ሚሊዮን ዶላር አለው ። ይሄ ሁሉ ገንዘብ እያለው 500 ዶላር ብቻ ለምን ተበደረ የሚለው ግራ ገባቸው ። ከ2 ሳምንት በኃላ ከነወለዱ 506.50 ዶላር ከፍሎ መኪናውን ይዞ ሲወጣ ማናጀሩና ሌሎች የባንኩ ሰራተኞች "ሚስተር ሳይ! ያ ሁሉ ሚሊዮን ዶላር እያለህ ይችን ዶላር ብቻ የተበደርከው ለምንድን ነው?" አሉት ። ሚስተር ሳይ ፈገግ ብሎ፡- "በዚህ ወቅት በ6.50 ዶላር መኪናየን ለ2 ሳምንት የሚጠብቅልኝ ከዚህ የተሻለ ታማኝ ቦታ የት አገኛለሁ?" አላቸውና ወደቤቱ ቆሰቆሰው.... ወዳጀ! ማንንም ሳትጎዳ ጭንቅላትክን ተጠቀምበት!!!

ከእርቀት ስልክ ለመጥለፍ

በትግራይ "አባቶች" ሁኔታ ግራ የተጋባችሁ ካላችሁ! የሆነው እንዲህ ነው፦ ትህነግ "ኮሚኒስት ነኝ" ብሎ ነው ጫካ የገባው። ኮሚኒስቶች ደግሞ ኃይማኖትን "የድሆች ማደንዘዣ" ነው የሚሉት። ፀረ እምነት ናቸው። ትህነግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስን በጠላትነት ፈርጆ ነው ጫካ የገባው። ይሁንና የራሱን ቤተ ክርስትያን ግን  የፈጠረው ትግል በገባ በጥቂት አመታት ውስጥ ነው።  ይህ መረጃ የመጀመርያው የትህነግ ሊቀመንበር አረጋዊ በርሄ በመፅሐፉ ያጋለጠው ነው። 1) በ1971 ትህነግ በየወረዳው የትግራይ ቄሶችን መለመለ። መልማዩ የጥላቻ አባት የሚባለውና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስነመለኮት የተማረው የትህነግ ታጋይ ገብረኪዳን ደስታ ነው።  ሰውየው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትናን የአማራ ነው ብሎ ፈርጆ፣ አማርኛ የጠላት ቋንቋ ስለሆነ በትግርኛ መስበክ አለብን ብሎ ንቅናቄ ጀመረ። የራሳችን ቤተ ክርስቲያን እንመሰርታለን ብሎ ሰራ። በየወረዳው ኮንፈረንስ አደረገ። የትህነግ አስተሳረብ ያጠመቋቸውን ቄሶች አደራጀ። 2) ስብሃት ነጋ የትህነግ ታጋዮችን መልምሎ ደብረዳሞና ሌሎች ገዳሞች መነኩሴ አስመስሎ አስገባ። እነዛ የትህነግ ታጋይ ሆነው መነኩሴ መስለው ገዳም የገቡት ለአሁኑ የኃይማኖት ካባ ለተከጀቦነ ንቅናቄ መሰረት ናቸው። 3) በ1978/9 ዓ/ም አካባቢ ትህነግ የገብረኪዳን ደስታን ምልምሎች አደራጅቶ "ብሔራዊ የትግራይ ቄሶች ኮንፈረንስ" አደረገ። ትግራይ እንደ አገር የራሷን ሲኖዶስ ማወጅ አለባት አሉ። አወጁ። 4) ትህነግ ይዟቸው በነበሩት የትግራይ አካባቢ ልክ በቅርቡ ኦሮሚያ እየተደረገ እንዳለው የትህነግ "ቄሶች" ቤተ ክርስቲያንን ሲኖዶስ ከመደባቸው አባቶች ቀሙ። ትግራይ ውስጥ ቤተ ክርስቲያንን ለሁለት ከፈሏት። ደርግ በያዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ ትህነግ በያዛቸው የትግራይ አካባቢዎች የትግራይ ቤተ ክርስቲያን ተባለ። የትህነግ/ህወሓት ቤተ ክርስቲያን  ማለት ነው። ደርግ መቀሌን ሲለቅ መቀሌ የነበሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶች ወደ ደሴ እንዲሸሹ ተደገደዱ። የትህነግ ቄሶች ሙሉ በሙሉ የትግራይ ቤተ ክህነትን መመስራቸውን ይፋ አደረገ። ይህ ጉዳይ ትህነግ አዲስ አበባ እስኪገባ ቆየ። 5) ትህነግ ስልጣን ሲይዝ የትግራይ አገርነትን እንደተወው፣ የትህነግ ቄሶችም የተገንጣይ አላማቸውን ተውት። 2010 በኋላ ትህነግ ወደ መቀሌ ሲመለሾ የኃይማኖት ፕሮጀክቱን እንደገና ጀመረው። በጦርነቱ ወቅት ሲያደርጉ የነበረው የሚታወቅ ነው። "አገረ ትግራይ" እያሉ ቀድሰዋል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ትህነግ ብሶት ማሰሚያ፣ የመገንጠል ጥያቄውን እንዳልተውት ማስታወሻ አድርጓቸዋል። ባለፈው የኢትዮጵያ መከላከያ ትግራይን ጥሎ ሲወጣ ፀጋዬ በርሄ "የትህነግን ቄሶች" እንዲመራ ተደርጎ በየአካባቢው ተዘዋውሮ "አገረ ትግራይ እያላችሁ ቀድሱ" ብሎ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የአክሱም አባቶች ብቻ "እናንተ አገረ ትግራይ ብላችሁ ካወጃችሁ እኛም እንላለን። እናንተ ሳታውጁ እኛ አገረ ትግራይ አንልም።" ብለው ተቃውመዋል። በበርካታ ቦታዎች አሁን ትግራይ አገር ተደርጋ "አገረ ትግራይ" እየተባለ ይቀደሳል። ጠርናፊው "አለቃ" ፀጋዬ በርሄ ነው። 6) የትግራይ ጳጳሳት  በጦርነቱ ወቅት እንኳን ደሞዝ አልተቋረጠባቸውም። የባንክ አገልግሎት ስላልነበር ማውጣት ባይችሉም ቤተ ክርስቲያን  ግን ከፍላቸዋለች። አሁንም ደሞዝ ይላክላቸዋል። ደሞዛቸውን እየወሰዱ ነው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  ጋር አንቀጥልም የሚሉት። ትህነግ በጦርነቱ ወቅት "ጦርነቱን እቀጥላለሁ። በጀት ግን ላኩ።" እንዳለው መሆኑ ነው። ከስር መሰረቱ ካየነው የትግራይ አባቶች ኩርፊያ ኃይማኖታዊ አይደለም። ባለፈው አመት ጀምረው በጠላት ቋንቋ አማርኛ አንሰብክም ብለዋል። ይህ ተጀምሮ የነበረው በ1971 ነው። አላማው ፖለቲካዊ ነው። የኮሚኒስት "ቄሶች" ፕሮጀክት ነው የቀጠለው። የጥላቻ አባቱ ገብረኪዳንና ስብሃት ነጋን ፕሮጀክት ነው አፈሩን አራግፈው ያመጡት። አሁን ፀጋዬ በርሄ ነው የሚመራው። ገብረኪዳን ደስታን "መምህር" ይሉት የነበረው ኃይማኖት ማዕረግ ሰጥተውት ነው። ፀጋዬን ደግሞ አለቃ ፀጋዬ" ይሉታል። ሁለቱም የኃይማኖት ትምህርት አላቸው። ርዕዮት አለማቸውን ቢጠየቁ  ግን  ድሮ ኮሚኒስም፤ በቅርብ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ነው የሚሉት።  ዞሮ ዞሮ ፀረ እምነት ናቸው። ገብረኪዳንም ሆነ ፀጋዬ ኃይማኖተኞች አይደሉም። አላማቸው የትህነግ አላማ ነው። ፀረ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ነው። በኃይማኖት ስም ከወደ ትግራይ የሚጎሰመው ልዩነት መነሻው ተገንጣይ ብሔርተኝነት እንጅ ኃይማኖት አይደለም። ለበለጠ የአረጋዊ በርሄን መፅሐፍ ማንበብ ይቻላል። መንበረ ከሳቴ ወዘተ የሚሉት የትህነግን ማንፌስቶ አላማቸው አድርገው ጫካ የገቡ፣ ጫካ የገቡት በፀረ ኦርቶዶክስነት ያደራጇቸው፣ እንጅ ኃይማኖተኞች አይደሉም። መነሻውም ትህነግ ከተመሰረተ ሶስትና አራት አመት ውስጥ እንጅ ባለፈው ሁለት አመት ጦርነት ምክንያት የተጀመረ አይደለም። ጦርነቱ ሰበብ ነው። ትህነግ ስልጣን ሳይዝ ጫካ ሆነው የራሳችን ሲኖዶስ አዋቅረናል ብለው አውጀው ነበር። አሁን የኦሮሚያው እንደማያደርገው የትህነግ ታጣቂን አስከትለው ቤተ ክርስቲያን  ነጥቀው ገብተው ነበር። የኦሮሚያው "መልካም ተሞክሮ" ብሎ የወሰደው ከአርባ አመት በፊት ከነበረው ነው። ትህነግም ድሮ መታገያ ያደረገውን ነው አሁን እንደ አዲስ የጀመረው። (ከወር በፊት ከፃፍኩት የተወሰደ ነው) join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

👇ከታች ካለዉ ጋር ይያያዛል 👇
+5
👇ከታች ካለዉ ጋር ይያያዛል 👇

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማራ ክልል ከወልቃይትና ራያ እንዲወጣ ካስተላለፉ በኋላ አማራ ክልል በጉዳዩ ላይ አቋሙን ማሳወቁ ተሰምቷል። አማራ ክልል ምላሹን በፅሁፍ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ  አቅርቧል። ህወሓት ደግሞ ጦርነት እጀምራለሁ ብሏል። በመረጃ እና በማስረጃ በዝርዝር እንመለሳለን ። join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

በአፋር ቡሬ ማንዳ ወታደራዊ ካምፕ ፣ በቀን እስከ 10 የሚደርሱ የግፍ እስረኞች ፣ በረሀብና በህክምና እጦት እየሞቱ እንደሚገኙ ተገለፀ! በአፋር ክልል ቡሬ ማንዳ በሚባል ስፍራ ከሚገኝ የመከላከያ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ፣ በተለይም ከመከላከያና ከፌደራል ፖሊስ አማራ በመሆናቸው ብቻ ''ፋኖ ናችሁ! ፋኖን ትደግፋላችሁ!'' እየተባሉ  ከየአካባቢው ተለቅመው እጅግ በርካቶች ለወራት ታስረው ይገኛሉ። ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገና ከስፍራው ያለ የመረጃ ምንጬ  << ታሳሪዎቹ እንደእሳት በሚፋጀው በረሀ ላይ እጅግ አሰቃቂ በሚባል ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ እየተሰቃዩ ታስረው የሚገኙ ሲሆን ፣ ምግብና ውሃ እንዲሁም ህክምና ባለማግኘታቸው ምክንያት ብቻ በየቀኑ እየረገፉ ሲሆን በቀን በአማካኝ እስከ 10 የሚደርሱ የግፍ ታሳሪዎች  በረሀብና በህክምና እጦት እየሞቱ ይገኛሉ! >> ሲል ተናግሯል ። << ለእናንተ ጥይት አናባክንም ፣ ተሰቃይታችሁ ትሞቷታላችሁ ! >> እንደሚባሉ የገለፀው የመረጃ ምንጬ ፣  በረሀብ ከመሞት በማለት ለማምለጥ ሙከራ ያደረጉም በየእለቱ እንደሚረሸኑ አስታውቋል።  በተመሳሳይ መልኩ ከቀናት በፊት ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ታፍነው ተወስደው ፣ በአፋር ክልል - ከኤርትራ 42 ኪ/ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው '' በሱላ ወታደራዊ ካምፕ '' በእስር ላይ የሚገኙት በርካታ አማራዎች በረሀብ እና በህክምና እጦት ህይወታቸውን እያጡ እንደሚገኙ መዘገቡ የሚታወስ ነው። ድምፅ እንሁናቸው ቢያንስ የተረፉትን ሰሚ ካገኘን! #ሟር_ይደረግ! join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

➨ጭረት አማረኛ ፊልም ከተዛሬዎቹ ለየት ባለ መልኩ የተሰራ እና ፊልሙን ለመስራት ብቻ ሁለት አመትን ፈጅቷል። ➨ፊልሙ በእዉነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ሲሆን ለየት የሚያደርገዉ ከሀገር ዉስጥ እስከ የዉጭ ሀገር የፊልም ባለሙያዋች ተሳትፈዉበታል። ➨ጭረት አዲስ የአማርኛ ፊልም  የሚመረቀው ሃምሌ 14 ,15 ,16  እና ሃምሌ 21, 22 ,23 በሁሉም የግል እና የመንግስት ሲኒማ ቤቶች ይመረቃል። https://youtu.be/vQ25q5hPt5g

አላማጣ! በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች "ለማንነቴ እሮጣለሁ፤ ማንነቴም አማራ ነው" በሚል መሪ መልእክት የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል። በሩጫውም ላይ የተሳተፉት ነዋሪዎቹ ላለፍት 30 ዓመታ
አላማጣ! በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች "ለማንነቴ እሮጣለሁ፤ ማንነቴም አማራ ነው" በሚል መሪ መልእክት የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል። በሩጫውም ላይ የተሳተፉት ነዋሪዎቹ ላለፍት 30 ዓመታት በማንነታቸው ምክንያት ሲደርሳባቸው ከነበረው በደል፣ ግፍና ጭቆና በመላቀቃቸው እንዲሁም ተፈጥሮዓዊ ማንነታችን አማራ ነው፣ የነፃነት ማንነታችን ይከበር በማለት ደማቅ የጎዳና ላይ ሩጫ አካሂደዋል። አሚኮ

Watch "የኮሜዲያን_እሸቱ_መለሰ_ኑሮ፣_ባለቤት_እና_መኖርያ_ቤትበማራኪ_ወግ_Ethio_Multimedia_ለልጃቸው_ስም_አወጡ" on YouTube https://youtu.be/05PUFhBGvoY

ናዝሬት ላይ በብሔርና በኃይማኖት የሚደረገው ቆጠራ አማራና ሌሎች ብሔሮችን አሳቅቀው ካፈናቀሉ በኋላ ኦሮሞ በቁጥር የበላይ መሆኑን ለማረጋገጥ እንደሆነ ታውቋል። የኦሮሚያ ክልል "አማራን ከአዳማ አፅድተነዋል" የሚል ሪፖርት ማቅረቡ ታውቋል። Join➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

"አንዳንዶች"... ተብሎ ይህ accusatory መረጃ ዛሬ ተፅፏል፣ እረፍት ብዬ ነበር ግን ስለሚመለከተኝ ይህን ልበል። ራሳቸው ክቡር ዶ/ር ለገሰ ያረጋገጡት እኔ ትናንት የፃፍኩትን ነው፣ ከፓርላማ
"አንዳንዶች"... ተብሎ ይህ accusatory መረጃ ዛሬ ተፅፏል፣ እረፍት ብዬ ነበር ግን ስለሚመለከተኝ ይህን ልበል። ራሳቸው ክቡር ዶ/ር ለገሰ ያረጋገጡት እኔ ትናንት የፃፍኩትን ነው፣ ከፓርላማ ተነግሮን የነበረው "ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢትዮጵያ ልክ እድገት ያረጋግጣል ተብሎ የተተነበየ ሀገር የለም" ነበር። ታድያ እዚህ የእርሳቸው ዳታ ላይ ቢያንስ ከሰሀራ በታች ያሉት ሴኔጋል እና ርዋንዳ አሉ፣ ወይ ሀገራቱ ከእስያ ናቸው ካልተባለ። Peace, I'm ou #elias mesret

#ሌሎች እንደዜጋ ብዙዎቻችን ጋር ጥያቄ የሚያጭሩ የፓርላማ መረጃዎች : 1. ግንባታ ላይ ስላሉ እና ቀድመው ስለተገነቡ የፓርክ፣ የሪዞርቶች እና የቤተ-መንግስት ስራዎች ዛሬ በፓርላማ በአንፃራዊነት ትንሽ ሰፋ ያለ መረጃ መቅረቡ በመልካም ጎኑ ይታያል። የተለያዩ ሀገራት የራሳቸውን የግንባታ ድርጅቶች እያመጡ ስራውን እያሰሩ እንደሆነ ተገልጿል፣ ይህም እየሆነ ያለው ጠ/ሚሩ ለተለያዩ ሀገራት መሪዎች ባቀረቧቸው ጥያቄዎች መሆኑ ተመላክቷል። ጥያቄው ግን፣ በመሪ ደረጃ ለውጭ ሀገራት መሪዎች ሊቀርብ የሚገባው ጥያቄ ይህ የፓርክ፣ የሪዞርቶች እና የቤተ-መንግስት ግንባታ ወይስ በጦርነት የወደሙ መሰረተ-ልማቶችን መገንባት፣ የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት የውጭ ድጋፍ ማፈላለግ እና በጦርነቱ ወቅት ሀገሪቱን ጥለው የወጡ የውጭ ድርጅቶች እንዲመለሱ መስራት? 2. "... ተጎጂነትን ማጉላት እየተለመደ መጥቷል" ተብሎ ከፓርላማ የተሰማው ንግግር ለብዙዎች የሚያም ሆኖ እንደሚቀር ተሰምቶኛል። እስከ 800,000 ሺህ ህዝብ በሁለት አመት ጦርነት ህይወቱን ባጣበት፣ ሚሊዮኖች ከቀዬአቸው በተፈናቀሉበት፣ በአንዳንድ ስፍራዎች ወጥቶ መግባት ብርቅ በሆነበት እንዲሁም የኑሮ ውድነቱ ብዙዎችን እያሰቃየ ባለበት ወቅት ማማረር እና ተጎጂነትን ማጉላት ምንም ማለት እንዳልሆነ ለሁላችንም ግልፅ ነው።  3. የ "መደመር" ቁጥር ሁለት መፅሀፍ ያስገኘው ገቢ 3 ቢልዮን ብር እንደሆነ ዛሬ በፓርላማ ተገልፁዋል። ይህ ማለት አንድ መፅሀፍ እንኳን 300 ብር ተሸጠ ብንል 10 ሚልዮን ኮፒ ተሽጧል ማለት ነው። አንዳንድ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ጭምር በኮታ መፅሀፉን እንዲገዙ መደረጉ ቢታወቅም፣ 10 ሚልዮን የሀገራችን አንባቢ ተገኝቶ መፅሀፉን በፈቃደኝነት መግዛቱ ጥርጣሬን ያጭራል። ጆይን➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

#FactCheck ትናንት ስለተመረቀው የኢቢሲ አዲሱ ህንፃ "በአፍሪካ በዚህ ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ አንድም የሚድያ ተቋም አይገኝም" ተብሏል በዛሬው ፓርላማ። ነገር ግን እኔ በአንድ ወቅት ዞሬ እንዳየ
#FactCheck ትናንት ስለተመረቀው የኢቢሲ አዲሱ ህንፃ "በአፍሪካ በዚህ ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ አንድም የሚድያ ተቋም አይገኝም" ተብሏል በዛሬው ፓርላማ። ነገር ግን እኔ በአንድ ወቅት ዞሬ እንዳየሁት፣ ማንኛውም ሰው ኦንላይን ላይ ቢፈልግም የሚያገኘው መልስ በምንም መስፈርት ቢሆን በአፍሪካ ትልቁ የሚድያ ተቋም የደቡብ አፍሪካው Media 24 ነው። ይህ ተቋም ከ2,400 በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን አመታዊ ትርፉ እስከ 326 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ ይገመታል። በስሩ እጅግ በርካታ ቴሌቭዥን ጣቢያዎች፣ ዲጂታል ሚድያዎች፣ ጋዜጦች እና የሬድዮ ቻናሎች አሉት። በሁለተኛነት ስሙ የሚጠቀሰው የኬንያው ዴይሊ ኔሽን ግሩፕ ነው። ይህ ተቋም 350 ሚልዮን ዶላር የሚገመት ሲሆን በውስጡ 7 የተለያዩ የጋዜጣ እትሞች፣ ሶስት የቴሌቭዥን ጣብያዎች፣ ሶስት የሬድዮ ጣብያዎች አሉት፣ 1,578 ሰራተኞችም በስሩ አሉት። ድርጅቱ ከኬንያ በተጨማሪ በታንዛንያ፣ ርዋንዳ እና ዩጋንዳ በሚድያ ስራ ተሰማርቶ ይገኛል። እንደሌላው ሀገር የኢቢሲ ቁጥሮችን ማግኘት ቀላል ባይሆንም ይህ ከላይ የቀረበው መረጃ በጣም አጠራጣሪ መሆኑን ማየት ይቻላል። Image: Media 24 HQ #EliasMeseret ጆይን➨ https://t.me/GimbaMediaNetwork

#ፓርላማ #FactCheck ዛሬ በፓርላማ የ IMF ዳታን መሰረት በማድረግ "ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢትዮጵያ ልክ እድገት ያረጋግጣል ተብሎ የተተነበየ ሀገር የለም" ተብሏል። እውነታውስ? የ IM
#ፓርላማ #FactCheck ዛሬ በፓርላማ የ IMF ዳታን መሰረት በማድረግ "ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢትዮጵያ ልክ እድገት ያረጋግጣል ተብሎ የተተነበየ ሀገር የለም" ተብሏል። እውነታውስ? የ IMF ዳታ እንደሚያመለክተው ዘንድሮ (እ.አ.አ በ2023) ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ያሉት ከሰሀራ በታች ያሉት የአፍሪካ ሀገራት በቅደም ተከተል እነዚህ ናቸው: 1. ሴኔጋል- 8.3% 2. ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ- 6.3% 3. ርዋንዳ እና አይቬሪ ኮስት- 6.2% 4. ኢትዮጵያ እና ኒጀር- 6.1% ናቸው። በቀጣዩ አመት (2024) ከፍ ያለ እድገት ያስመዘግባሉ የተባሉት ሀገራት ደግሞ: 1. ኒጀር- 13% 2. ሴኔጋል- 10.6% 3. ርዋንዳ- 7.5% 4. ሞዛምቢክ- 8.2% 5. አይቬሪ ኮስት- 6.6% 6. ኢትዮጵያ- 6.4% ናቸው። ሪፖርቱን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይቻላል: https://www.imf.org/en/Publications/REO/SSA/Issues/2023/04/14/regional-economic-outlook-for-sub-saharan-africa-april-2023 ስለዚህ መረጃው የተሳሳተ ነው። Via Ethiopia Check @Gimbamedianetwork