Ethiopia Studio 🇪🇹
Open in Telegram
902
Subscribers
-124 hours
-67 days
-630 days
Posts Archive
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇
https://t.me/gimbamedianetwork
እናንተ ህዝብ ላይ ችግር አትትከሉ እንጅ ችግኙንስ ህዝብ ይተክለዋል።
የስራ ክፍፍል ጠቃሚ ነው! ውጤትም ያመጣል።
ፖለቲከኞቹ ችግር አትትከሉ እንጅ ችግኙን አርሶ አደሩ በግብርና ባለሙያ ታግዞ ይተክለዋል።
እየውልህ፦
የደቡብ ሱዳን ታጣቂና ሌላው ንፁሃንን እያጠቃ መከላከያ ችግኝ ሲተክል ውጤታማ ስራ አይደለም!
የቀበሌ ሰራተኛ ቢሮ ዘግቶ ግብር ከፋይ እያጉላላ ጭቃ ያጨማለቀበት ችግኝ እርግጠኛ ሁን አይፀድቅም! ክስረት።
ሚኒስትሩ በአውሮፕላን፣ በመአት መኪና፣ ድግስ በርካታ ወጭ አውጥቶ፣ ሚዲያ አንጋግቶ የሚተክለው ችግኝ ኪሳራ ነው። አንድ ቀን ለፕሮፖጋንዳ በጭቃ ለውሰኸው የምትመጣውን ችግኝ ቀርቶ ግዙፍ ፕሮጀክት ትረሳዋለህ። እየተዋወቅን። ለሁለት ደቃቃ ፕሮፖጋንዳ ሚሊዮን ብር እየከሰረ አያዋጣም። ለሚሰራ ስጡት። ቀን ሙሉ የሚሰራ ይስራው።
የሚሻለው! ይህ ሁሉ ወጭ በአንድ ቋት ሆኖ፣ ችግኝ እተክላለሁ ብሎ ስራ የሚጎዳው ላይ አስርም አምስትም ብር አዋጥተህ ለአርሶ አደሩ አበል ክፈለው። ስራ አጥቶ የተቀመጠው ወጣትም ተወዳድሮ ጭምር መስራት ይችላል። ፕሮጀክት አድርገህ የስራ እድልም ይፈጥር ነበር። የግብርና ባለሙያዎችን በደንብ አሰልጥነህ አሰማራ። ለፕሮፖጋንዳ እንደምትለው ባይሆንም በርካታ ይተከላል። አንተ ድንጋይ ስር ሸጉጠኸው ከምትመጣው በተሻለ ይፀድቃል። ችግኝ በዘመቻ አይሆንም። ደግሞ አንድ ቀበሌ ሚሊዮን ሊተክል? ውሸት ነው።
ለኢትዮጵያ ህዝብ ችግር አትትከሉበት እንጅ ችግኙን በትንሽ ወጭ፣ በነፃም ጭምር ይተክለዋል። ሱፍ ለብሰህ ለሁለት ደቂቃ ለምትሰራው ፕሮፖጋንዳ የሚወጣን ወጭ የአንድ ቀበሌ ህዝብ መአት ችግኝ ይተክልበታል።
ችግር እየተከላችሁ ችግኞቹ ብቻ ሳይሆኑ የሰው ነፍስ በየቀኑ እየጠወለገ ነው። ጫካ ሄዶ ችግኝ ለመትከል አልተቻለም። ይህ ሁሉ የዘጭዘጭ ወጭ ለአርሶ አደሩ ማዳበሪያ ይሆን ነበር። ማዳበሪያ ብታደርሱት ችግኙን ደግሞ በትንሽ ውሎ አበል መስራት ይችል ነበር። የአካባቢው ህዝብ መካከል ተመርጦ የተከለውን እንዲንከባከብ ቢደረግ አዋጭ ነበር።
ይህንም ተውት ከፈለጋችሁ። ችግኝም አትትከሉ። ከፈለጋችሁ በብዙ ኪሳራም ፕሮፖጋንዳ ስሩበት። ግን ችግር በቃን። የተከላችሁት እሾሃማ ችግር መሄጃ መንቀሳቀሻ ነሳን። ተውን።
ችግር አትትከሉምን። አንደኛው ክልል ሌላኛውን ክልል ለመበጥበጥ ታጣቂ አያደራጅ፣ አንዱ የሌላውን ውስጣዊ አንድነት አይረብሽ። ንፁሃንን የሚያጠቃ የግልና የቡድን ታጣቂ አታደራጁ። ስንጠቃ የፀጥታ ኃይሉ አልታዘዝኩም አይበል። ችግኝ የሚተከለውን ተውትና ንፁሃን በአንድ ጉድጓድ የሚቀበሩበትን አሰቃቂ ችግር አስቁሙ። ህዝብ ላይ የጀመራችሁትኝ ዘመቻ አቁሙ። ተገንጣይ ኃይልን እየደገፋችሁ ህዝብን እረፍት አትንሱ። አንዱ በሌላኛው ህዝብ ላይ ልክ እንደ ጠላት ደባ ሲሰራ አይዋል።
በእናንተ ችግር ምክንያት የኢትዮጵያ ህዝብ እረፍት አጣ። የብሔር ጠብ፣ የኃይማኖት ጥቃት፣ የታጣቂ ጥቃት፣ በህዝብ ላይ ሰራዊት ማሰማራት፣ ደባ፣ ሴራ.... በቃ ችግር አትትከሉ! ችግር ባልተከላችሁ እንጅ ያለውም በበቃን። ገጀራና ክላሽ ቀርቶ የአየር ንብረት ለውጥ በገደለን እቴ። ንፋስ፣ ሙቀት ምናምን! ያንቃቃና! ከእናንተው ችግር አይበልጥ። ደግሞ ችግር መትከል ብታቆሙ ችግኙን ህዝብ "ሆ" ብሎ ይተክለው ነበር።
ተውን በቃ። ችግርን አመቱን ሙሉ እየተከላችሁ በሁለት ደቂቃ ለፕሮፖጋንዳ የምትተክሉት ችግኝ አያድነንም።
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇
https://t.me/gimbamedianetwork
የምድራችን ትልቁ ጦር ስሜት ነው። የምድራችን ትልቁ ጀብድ ይቅርታ ማድረግ ነው። የምድራችን ትልቁ በሽታ ቅናትና ምቀኝነት ነው።ነገሩ እንዲህ ነው።
ይህ ኢትዮዽያዊ የመን ውስጥ የጥይት ተኩስ እየተለማመደ በስህተት አንድ የመናዊ ይገድላል። ያው የመን በአለማችን በማንኛውም ሱቅ ያለምንም ፓስፖርት ጠያቂ መሳሪያ የሚሸጥበት አገር ናት። ዱላ ከረሚላ ማለት መሳሪያ ነው የመን ውስጥ፣ የሆነው ሆኖ ልጅ ልክ እንደገደለው በአካባቢው ሰዎች ቁጥጥር ስር ይውላል። ሟች ተቀብሮ እስከሚያበቃ ልጅን ደበቀው ለሸህ አስቀመጡት። የልጅ ወላጆች ተጠርተው ልጅን ምን እናድረገው ተባሉ። በሸሪአ ህግ መሰረት የገደለ ይግደል ነውና ይገደል ተባለ። የማች አባት ገዳዮን ላግኘው አሉ። ተገናኙ። አባት ለምን ልጀን ገደልከው .? አሉት። ገዳይ መተኮስ እያስለመደኝ ነበር ጥይቱ አልቋል ብየ ስስብ ደገልኩት አውቄ አደለም አለው። አንተ ምንድነህ ዜግነትህ ምንድነው ሲባል ሀበሻ ( ኢትዮዽያዊ) ነኝ አላቸው። ለምን የመን መጣህ አሉት ወደ ሳኡዲ እየሄድኩ ነው አላቸው።
የሟች አባት ይሄንን ካወቁ ቡኋላ ምንም ሳይሉ ወደቤታቸው ተመለሱ።ዘመድና ቤተሰብ ሰብስበው፣ ገዳይ ስደተኛ ነው። እጅ ላይ ምንም የለውም። ቢደገልም ቤተሰቡን መጉዳት ነው። እናት ልጀ ይመጣል ስትል እሰው አገር ተቀብሯል ትባላለች እንጅ ትርፍ የለውም። ስለዚህ የሞተውን አላህ ይዘንለት ያለውን ይቅር ብለነው ወደ ቤተሰቡ ይሂድ አሉ። የሟች ወንድሞችና ዘመዶች ሁሉ ተስማሙ ይህ ልጅ ከሞት ተርፎ
ዛሬ የመኖች ተገርመው ዜና እየሰሩበት ነው። ይቅርታ ብሄር ጎሳ ድንበር ዜግነት የለውም። የገዛ ወንድሙን በብሄር እየለየ ለሚገለውና ለሚዘርፈው የአገሬ ነውረኛ ፖለቲካ የየመናዊያን ከተራራ የገዘፈ ይቅር ባይነት ትልቅ መልዕክት አለው።
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇
https://t.me/gimbamedianetwork
በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ዛሬ በከባድ መሳሪያ የታገዘ የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ ውሏል። በተኩሱ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን እና በወግዲ ሆስፒታል በርካታ ቁስለኞች ማየታቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ሁኔታው ግራ አጋቢ ነው ይላሉ አስተያየት ሰጪዎች።
==[=====================
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ይህን ቻናል join በማድረግ ተከታተሉ ቻናል ሊንክ👇👇👇👇
https://t.me/gimbamedianetwork
#ሰበር ዜና/ሼር ይደረግ
ለነገው የሚሊሻ ስልጠና መካነ ሰላም ሊገቡ የነበሩ ከ60 በላይ ፖሊሶች ትናንት ምሽት በጉዞ ላይ እያሉ መጥፋታቸው ታዎቀ
በዚህ ምክንያት ነገ ሊጀምር የነበረው የሚሊሻ እና የከተማ ፖሊሶች ስልጠና ወደ ሚቀጥለው ሳምንት መዛውሩን የውስጥ ምንጮቼ ገልፀውልኛል።
ከተለያዩ የጎጃም አካባቢዎች፣በተለይም ከመርጦ ለማሪያም፤ከቢቸና፣ከሞጣ፣ከግንደዎይን እና አካባቢዋ ትናት ተመርጠው ወደ መካነ ሰላም ለስልጠና ሊገቡ የነበሩ ከ60 በላይ የ32ኛ ዙር የፖሊስ አባላት ናቸው ይጓዙበት የነበረውን አውቶብስ በማስቆም በሙሉ ስርዓቱን ከድተው ትናንት አመሻሹን የጠፉት።
አስቀድመው "ወያኔ ስለወረረን ነው ስልጠና የምትገቡት" የሚል የሃሰት ማስረጃ ነግረዋቸው ነበር።ይሁን እንጅ ሰከስልጠናው በኋላ ከምስራቅ አማራ ፋኖ እና ከሸዋ ፋኖ ጋር ሊያዋጓቸው መሆኑን ሲያዉቁ"ከወንድሞቻችን ጋር እንዋጋም" በሚል በኋላ ነው ጥለው የጠፉት።
"ስልጠና ካልገባችሁ መሳሪያችሁን እንዎስድባችኋለን"ተብለው ለነገ ስልጠና እንዲዘጋጁ ተነግሯቸው የነበሩ ከ400 በላይ የሚሊሻ አባላት ገሚሱ "መሳሪያችንን ውሰዱ እንጂ፣ከፋኖ ጋር ልንዋጋ አንሰለጠንም"የሚል አቋም ይዘዋል።ገሚሱ ደግሞ ለነገ ስልጠና ዛሬ ምሽት ወደ እየተመደቡበት እንዲገቡ ቢነገራቸውም የት እንደገቡ አልታዎቀም ተብሏል።
👉 ተጨማሪ መረጃ ጆይን➨ https://t.me/gimbamedianetwork
♨ ያለጥፋቱ ህይወቱ የተበላሸው ሜንዲ
- ፈረንሳዊው ኮኮብ በሀሰተኛ ክስ ላለፉት ሁለት አመታት ከእግር ኳስ ውጪ እንዲሆን በማድረግ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደረገ።
- አሰሪዎቹ በሀሰተኛ ክሱ ምክንያት ከሱ ጋር ያላቸውን ውሎች በሙሉ አቋረጡ።
- ፍርድ ቤት እሱ ላይ የቀረቡት 10 የአስገድዶ መድፈር ክሶች በሙሉ አንድ በአንድ አጣርቶ እሱ ከወንጀል ነፃ መሆኑን በማረጋገጥ ይፋ አድርጓል።
- ዝናው እና ህይወቱ በሀሰተኛ ክሶች ምክንያት ሙሉለሙሉ ተበላሽቶበታል፤ በሀሰት ስሙ ጠፍቷል።
- ይህን ያህል ጊዜ ያለጥፋቱ አንገላተውታል።
ቤንጃሚን ሜንዲ ንፁህነቱን ካረጋገጠጠለት ከትላንትናው የመጨረሻ የፍርድ ቤት ቆይታው በኋላ ጋዜጠኞች ስለ ንፁህነቱ እና ስለወደፊት የእግር ኳስ ህይወቱ በርካታ ጥያቄ ቢያቀርቡለትም ግን በስሜት እያነባ 'አልሀምዱሊላህ' በማለት ለፈጣሪው ምስጋናውን በማቅረብ ብቻ ጥያቄዎቹን በዝምታ መልስ ሰጥቶባቸው አልፏል። ❤😢
ጆይን➨ https://t.me/gimbamedianetwork
የዕለቱ አጫጭር መረጃዎች፤ ©ጊምባ ሚድያ ኒትወርክ ቅዳሜ ሐምሌ 8/ 2015
1) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ከወሰዱ 150 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ነጥብ ያስመዘገቡት 40.65 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ከነዚህም ውስጥ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 17.2 በመቶው ብቻ የማለፊያውን 50 በመቶና ከዚያ በላይ የሆነውን ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል። ከሰኔ 30 ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና መጠናቀቁን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ሳሙኤል ክፍሌ ዛሬ ሐምሌ 8/ 2015 ዓ.ም መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው ይህ የተገለጸው።
2) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደብረ ብርሃን ከተማ ፖሊስ አዛዥ ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸውን የከተማዋ አስተዳደር ገልጸዋል። ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 130 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የደብረ ብርሃን ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ምንውየለት ጭንቅሎ የተገደሉት አርብ ሐምሌ 07/2015 ዓ.ም. እንደሆነ ተገልጿል። የአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው የደብረ ብርሃን ከተማ ኮምዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው የሐዘን መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የፖሊስ አዛዡ በሥራ ላይ ሳሉ ነው ባልታወቁ ሰዎች በጥይት የተመቱት፤ ኮማንደር ምንውየለት ጭንቅሎ በታጣቂዎቹ ጥቃት ከተፈጸመባቸው ከቆሰሉ በኋላ ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ቢሆንም ሕይወታቸው ማለፉ ተገልጿል። የከተማው ኮሚዩኒኬሽን “ጠንካራ መሪዎችን መርጦ በመግደል፣ የሚመጣ ለውጥ፣ የሚረጋገጥ ፍትህም የለም” በማለት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታዋቂ እና ጠንካራ የፖለቲካም እና የፀጥታ ዘርፍ አመራሮች ላይ ግድያ እንደሚፈጸም አመልክቷል።
3) በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ እና ያያ ጉለሌ ወረዳዎች ያለው የጸጥታ ችግር ከሌሎች ወረዳዎች የተለየ እና የከፋ በመሆኑ፤ የግብርና ሥራችንን መከወን አልቻልንም ያሉ አርሶ አደሮች ለከፋ ድህነት ተጋልጠናል ሲሉ ገልጸዋል። በአካባቢው ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በማለት የሚጠራው እና በመንግሥት ኦነግ ሸኔ በመባል በአሸባሪነት የተፈረጀው ታጣቂ ቡድን በሚያደርገው ዝርፊያ እና አፈና እንደልብ ተንቀሳቅሶ መስራት አለመቻሉን ነው አርሶ አደሮቹ የጠቆሙት፤ አብዛኛው የእርሻ መሬታቸው ሳይታረስ የዘር ወቅት ማለፉንም ገልጸዋል።
4) የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኒዩ በአገሪቱ እየተከሰተ ያለውን የምግብ ዋጋ መናርን ለማረጋጋትና እጥረትን ለመቅረፍ የአስቸኳይ ጊዜ ማወጃቸው ተገልጿል። በቅርቡ ከተነሳው የነዳጅ ድጎማ የተቆጠበውን ገንዘብ ለአርሶ አደሮች ማዳበሪያና ዘር ማቅረብም መንግሥት የምግብ ዋጋ ገበያውን ለማረጋጋት ከወጠናቸው አንዱ መሆኑም ተጠቅሷል። በርካታ አርሶ አደሮች በወሮበሎች እየታገቱ ካሳ እየተጠየቀባቸው በመሆኑም መሬታቸውን ጥለው ለመሄድ ተገደዋል። ይህንንም ለማስቀረት መንግሥት ለአርሶ አደሮች ጥበቃ እንደሚያደርግ አስታውቋል። በተጨማሪም በከፍተኛ ድህነት ውስጥ ያሉ ሰዎችም በየወሩ 10 ዶላር ለስድስት ወራት ያህል እንዲረዱ ይደረጋል ተብሏል።
5) ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዋግነር ከሩሲያ ጦር ጋር እንዲቀላቀል የቀረበለትን ሃሳብ ውድቅ ማድረጉን አስታውቀዋል። ከሳምንታት በፊት በሞስኮ በተደረጉ ውይይቶች በርካታ የዋግነር ከፍተኛ የጦር አዛዦች ተዋጊዎቹ ከጦሩ ጋር የመቀላቀላቸውን ሃሳብ እንደደገፉ ኮመርሳንት ከተሰኘው ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል። ተዋጊዎቹን የሚመራው ከፍተኛ የዋግነር አመራር ሊሆን እንደሚችልም ሃሳብ የቀረበለት ፕሪጎዚን “ተዋጊዎቼ በዚህ አይስማሙም” የሚል ምላሽ እንደሰጠም ፑቲን ለጋዜጣው ተናግረዋል። ከሳምንታት በፊት የዋግነር ኃላፊ ፕሪጎዚን የሩሲያን መከላከያ ከፍተኛ አመራሮችን ልክ እንደሚያስገባና የትኛውንም ርቀት እንደሚሄድ መናገሩ ይታወሳል።
#ስለአማራ ሚሊሻ አስቸኳይ መረጃ‼️
ሰኞ የሚጀመር ስልጠና ነው የማይሳተፍ ሚሊሻ መሳሪያውን ይቀማል የሚል አዋጅ አውጥተዋል።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ
ስልጠናውም 3 ቀን የብልጽግና ማኒፌስቶ ይማራሉ 4 ቀን ደግሞ ፋኖን እና የተበተነውን ልዩ ሃይል እንዴት መውጋት እንደሚቻል የሚሰጥ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ስልጠና ነው። ይሄን ኦፕሬሽን ከሰሩ ቦሀላ ሚሊሺያው እዲበተኑ እና መከላከያ ውስጥ እዲገቡ ተወስኗል ሲሉ የመረጃ ምንጮች ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ለጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ አረጋግጠዋል።
"ውድ የጊምባ ሚዲያ ኒትወርክ ቤተሰቦች ጊምባ ሚዲያ ኒትወርክ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"
ጆይን➨ https://t.me/gimbamedianetwork
#ስለአማራ ሚሊሻ አስቸኳይ መረጃ‼️
ሰኞ የሚጀመር ስልጠና ነው የማይሳተፍ ሚሊሻ መሳሪያውን ይቀማል የሚል አዋጅ አውጥተዋል።
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
ጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ
ስልጠናውም 3 ቀን የብልጽግና ማኒፌስቶ ይማራሉ 4 ቀን ደግሞ ፋኖን እና የተበተነውን ልዩ ሃይል እንዴት መውጋት እንደሚቻል የሚሰጥ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ስልጠና ነው። ይሄን ኦፕሬሽን ከሰሩ ቦሀላ ሚሊሺያው እዲበተኑ እና መከላከያ ውስጥ እዲገቡ ተወስኗል ሲሉ የመረጃ ምንጮች ከላይ በተያያዘው ደብዳቤ ለጊምባ ሚድያ ኒትዎርክ አረጋግጠዋል።
"ውድ የጊምባ ሚዲያ ኒትወርክ ቤተሰቦች ጊምባ ሚዲያ ኒትወርክ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"
ጆይን➨ https://t.me/gimbamedianetwork
አንዳንድ ነገሮች....!
በማንኛውም ኃይማኖት ዙሪያ ሀሳብ ከመሰንዘር የታቀብኩት በዘመነ-ብልፅግና ''ሀይማኖት'' ራሱ ግልፅ የፖለቲካ-ኢኮኖሚ መድረክና የመደብ ትግል ሆኖ በመገኘቱ ነው!
ስለዚህ ምዕመኑ ይሄ ገብቶት ሀይማኖቶቹን ከሴራና ከጥላቻ ፖለቲከኞች መዳፍ ነፃ እስከሚያወጣ ፣ ቀድሞ ገብቶህ በምትሰነዝረው አስተያየት ፥ ካልገባው ምዕመን ጋር በመላተም ነገሩን ከማባባስ 'በደንብ እስኪገባለት እኛ ዝም እንበልለት' ብዬ የግል ውሳኔ አሳልፌአለሁ!
ሀይማኖትን በሀይማኖታዊ (በምዕመኑ) ትግል እንጂ በፖለቲከኛ ትግል ከፖለቲከኞች መጠቀሚያነት ነፃ ማውጣት አይቻልም!
እምነትህን ከወደድክና እንዲከበር ከፈለክ ከፖለቲካዊ ይልቅ መንፈሳዊውን መስመርና ቀኖና ይዘህ በፅናት ታገል!
ከአምልኮ ስፍራ ሂደህ ''ይቅርታ'' እየጠየከው በሩን ከረሰችሞ የሚዘጋብህ ግለሰብ ፣ ፖለቲከኛ እንጂ ሀይማኖተኛ አለያም ''የበደሏችሁንም ይቅር በሉ!'' እያለ የመስበክ ሞራላዊ ልእልና ያለው የሀይማኖት መሪ ፣ ሊሆን ፈፆሞ አይችልም!
ይህን የጥላቻ ፖለቲካ መንፈስ የሰፈረበት ፣ 'የሀይማኖት መሪ ነኝ' የሚልን ኃይል ሀይማኖታዊ ቀኖናውንና ህግጋቶቹን ይዘህ በፅናት በመታገል እንጂ በፖለቲካዊ ተግባቦት አለያም ትግል ልትግባባውም ሆነ ልታሸንፈው አትችልም። ብታሸንፈው እንኳ የሚኖርህ የፖለቲካ ድርጅት እንጂ የሀይማኖት ተቋም አይሆንምና!
ሌላው ፦ ለፖለቲካ የተሰጠ ነፍስ ይዘህ ሀይማኖታዊነትንና የሀይማኖታዊ ነፃነት ትግልን መምራት እጅግ ይከብዳል! አብሮም አይሄድም! ስለዚህ ግለሰባዊ ሀሳብ ከማዋጣትና ከመሰንዘር ባሻገር የፖለቲካ ነፍሶች ሀይማኖት ውስጥ መግባታቸው ትርፉ የሀይማኖትን ትርጉም ማሳጣት ነው!
በተለይ እንደኛ ብዘሀ ሀይማኖትና ባህል ባለበት ሀገር ፣ አንድ በህዝብ ስሌጣን ላይ የተቀመጠ መሪ ወይም የፖለቲካ ተሿሚ ''ሀይማኖት የሚኖረውና ሀይማኖታዊ አስተምህሮውን የሚጨርሰው ከቤቱ ሆኖ ነው። ወደህዝብ ሲወጣ ሀይማኖት የለውም!
ለምሳሌ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ቀድሞ የምናውቀው በሀይማኖት አስተማሪነቱና ለሀይማኖት ነፃነት በሚያደርገው ትግል ነበር። አሁን ግን የፖለቲካ ተሿሚና መንግስታዊ የፖለቲካ ስልጣኑ ውስጥ ድርሻ ያለው ግለሰብ ነው። ስለዚህ ''ኡስታዝ'' የሚለው ስሙ ፖለቲከኛ ከሆነ በኃላ ማእረግና ክብሩን ያጣል። ማጣትም አለበት። ያ ካልሆነ ግን አንድም የሀይማኖቱን ክብር ማሳጣት ነው ፤ ሁለትም ፖለቲከኞች በኃይማኖት ውስጥ ለሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት እንደመራመጃ እግር ሆኖ ማገለረገል ነው። አብይ በሆነው ነገር ሁሉ አቡበከርን አንጠልጥሎ የሚሄደው ስለምን መሠላችሁ ? ፖለቲካ ውስጥ ገብቶም ያልተገፈፈውን ሀይማኖታዊ ማእረግና ድጋፉን ተጠቅሞ ፖለቲካ ለመስራት ነው።
ፖለቲካና ፖለቲከኝነት ዋሽተህም ቀጥፈህም በማሳመን ተከታይና ተመሪን ማብዛት ነው። ሀይማኖት ደግሞ በባህሪው ቀጥ ያለ መስመርን የሚከተል ፣ የማይቀያየር (rigid )የሆነ ቀኖናን የሚከተል ነው። ስለዚህ ፖለቲከኛም ሀይማኖተኛም መሆን ፖለቲካው በሀይማኖት ውስጥ ቀጥተኛ ጣልቃገብነት እንዲኖረው መፍቀድ ነው። ሲቀጥል አብረውም አይሄዱም።
ከኡስታዝ አበቡከር በተጨማሪ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ፣ መምህር ዘመድኩን በቀለን እናንሳ። ሁለቱም ፖለቲካ ውስጥ ያሉ ሰዎች ናቸው። ፖለቲካ ደግሞ ''ግራህን ሲመታህ ቀኝህን ድገመው'' ከሚለው ሀይማኖታዊ ቀኖናና አስተምህሮ በተቃራኒው የሚያሠራህ አለማዊ ህግጋቶችን የሚከተል ሳይንስ ነው። ስለዚህ በተለይ አንድ ሰው በመሪና በከፍተኛ ደረጃ ፖለቲካ ውስጥ ሲገባ አምልኮዎች ግለሰቡ ሀይማኖቱን እንዲየሠገለግል የሰጡትን ማእረግና ስልጣን የሚቀሙበት አሰራር መኖር አለበት ብዬ አምናለሁ። ይህ እንደኛ ላለው የተደበላለቀና የተጨመላለቀ ትርምስ ውስጥ ለገባ ሀገር ፣ እያንዳንዱን ሀይማኖት ከፖለቲካ ጣልቃገብነትና ተፅዕኖ ለማራቅ ብሎም ለማስከበር እንደአንድ ስልት ሊረዳ ይችላል። ፖለቲከኛው ተስፋ ሲያስቆርጠን የምንጣጋውና መሸሻችን ሀይማኖቶቻችን ስለሆኑ ሳይቀረዙና በፖለቲከኛ ሳይታመሱ ማስቀጠል የትውልዱ ሀላፊነት ነው።
ይህን ስል ''ፖለቲከኛ ሀይማኖት አይኑረው!'' እያልኩ አለመሆኑን ልብ ይሏል!
ከተነሳሁበት ግላዊ የሀሳብ መስመር ብወጣም በጥቅሉ ግን የግሌ እይታ ይኸው ነው!
ሠላም!
መረጃ‼️
በሰሜን ወሎ ቆቦና አካባቢው በዛሬው እለት ለግማሽ ቀን ያህል ቆም ብሎ የነበረው ተኩስ ከ9:00 ጀምሮ በተኩለሽና በግዳን በኩል መጀመሩን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል!
ትናንት ምሽት ከቆቦና አካባቢው እየፈረሰ የመጣው የአብይ ሰራዊት ወልዲያ ከተማ በመግባት ለሊቱን ለሰአታት የዘለቀ ተኩስ ከፍቶ እንደነበርም በስፍራው ያሉ የመረጃ ምንጮቻችን ገልፀዋል ! ተኩሱ ከማን ጋርና ለምን የሚለውን ማረጋገጥ አልተቻለም!
በተመሳሳይ ቀጠናውን ረፍት አልባና የጦርነት ምድር ያደረጉት ያሉት እኚህ የስርአቱ ወታደሮች ፣ በቆቦና አካባቢው ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙና ከመኖሪያ ቤታቸው እየታደኑ ጭምር በርካታ ያልታጠቁ ሰላማዊ ነዋሪ ወጣቶችን አፍነው መውሰዳቸውም ተገልጿል!
ትናንት የአየር ጥቃት ለመፈፀም በሚመስል መልኩ የጦር ጀቶች በአካባቢው ሲያንጃብቡ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን ድብደባ መፈፀምና አለመፈፀማቸውን ግን እስከአሁን በመረጃ ማረጋገጥ አልተቻለም!
የወጣቶች አፈሳው በዚህ ሰአትም አድማሱን በማስፋት ቀጥሏል!
join➨ @gimbamedianetwork
የቻይና ህዝብ 1.4 ቢሊዮን ሆኖ ቤት የሌላቸው ግን 2.5 ሚሊዮን ብቻ ናቸው። እነሱም ቤት አጥተው ሳይሆን በተለያየ የተፈጥሮ አደጋ የተፈናቀሉ ናቸው።
ኢትዮጵያ ደግሞ 110 ሚሊዮን ሆነን ከቻይና እኩል 2.6 ሚሊዮን ቤት አልባዎች አሉን። ግብፅ ደግሞ ይባስ 100 ሚሊዮን ሆና 12 ሚሊዮን ቤት አልባዎች አሏት።
ቻይና ከመላው አፍሪካ የሚበልጥ ህዝብ ቢኖራትም በዓለማችን ከአሜሪካ በላይ የቤት ፍላጎትን ከቀረፉት ትመደባለች።
ምክንያቱ ደግሞ መንግስታቸው የቤትን ጉዳይ በመሰረታዊ ጉዳይነት ስለሚሰራበት ነው።
እኛ አገር ቤት የተወደደው መንግስት ስላልሰራበት እንጅ ህዝብ ስለበዛ አይደለም። በዚህም የተነሳ ሰው እየለፋ ገቢውን ለቤት ኪራይ እየከፈለ ባዶውን መቅረት ይዟል። ሰው የሚያገኘውን ገቢ ለመኖሪያ ብቻ ከከፈለው ምኑን ኖረው ይባላል? የኢትዮጵያ መንግስት የኢኮኖሚ ለውጥ ከፈለገ ከመሰረታዊው የመኖሪያ ቤት አቅርቦት መጀመር አለበት። ካልሆነ ለጥቂት የቤት ባላባቶች ጭሰኛ ሆነን መቅረታችን ነው።
join➨ @gimbamedianetwork
መንግስት ላለፉት 5 ወራት የኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ባደረገው አፈና በሀገሪቱ ላይ የደረሰው ኪሳራ የ5 ክልሎችን የቀጣይ አመት በጀት ይሸፍናል!
የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ከሁለት አመት በፊት ባወጣው ዘገባ መሠረት ፣ ኢትዮጵያ በችግኝ አለመፅደቅ በየአመቱ - 65 ቢሊየን ብር ትከስራለች!
ኢትዮጵያ ላለፉት 5 ወራት ኢንተርኔትን በማፈኗ - 27, 809, 526 ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ኪሳራ ደርሶባታል! በብላክ ማርኬት (መንግስትም የሚገዛው በብላክ በመሆኑ ነው) የ100 ብር ተመን ስንመታው 2,780,952,600 ማለት ነው።
በዚሁ ምክንያት በጠቅላላ የምርት ኪሳራ ደግሞ 140,364,537 ዶላር ከስራለች! ወደኛ ሀገር ገለባ ስንመታውም 14,036,453,700 ብር ይሆናል።
በኢንተርኔት አፈናው ብቻ በጥቅሉ 16,817,406,300 ሀገራዊ ኪሳራ ደርሷል። በዚህ አመት ከፕሮፓጋንዳ ችግኝ ተከላ የምትከስረውንም በ65 ቢሊየን ብር እንኳ ብናሰላው የሁለቱ ድምር 81,817,406,300 ብር ይሆናል።
ይህ ደግሞ የደቡብ ፣ የሲዳማ ፣ የአፋር ፣ የሶማሌ ፣ የትግራይ ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ፣ የቤኒሻንጉል ፣ የጋምቤላ ክልሎችን የ2016 ዓ.ም አመታዊ በጀት ይሆናል። ከኦሮሚያ ክልል በጀት በ10 ቢሊየን ይበልጣል ፣ የአማራ ክልልን በጀት እጥፍ ሊሆን የሚጎድለው 9 ቢሊየን ብቻ ነው!
የኢንተርኔቱ አፈና ያደረሰው የ5 ወር ኪሳራ ብቻውን ደግሞ የአዲስአበባ ፣ የሀረሪ ፣ የድሬደዋ ፣ የቤኒሻንጉል ፥ የጋምቤላ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች አመታዊ በጀት ሸፍኖ ትርፍ አለው!
ይቺ እንግዲህኮ ለእነሱ ከጆሮ የማትገባው ፣ ጥቃቅንና አነስተኛዋ ሀገራዊ ኪሳራ ነች!😜
የጧት ማታ መፈክሩ ግን '' ብልፅግናችንን እያረጋገጥን ነው!'' ይላል! እንደሀገር ብስቁልናችን ግን በታሪክ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ሁኔታ ላይ ደርሷል!
ህንዳዊ ነው ሲያሻው መኪናን በሰማይ የሚያሽከረክር ሲለውም በአውራ ጣቱ አፈናጥሮ ከገደል የሚጨምር። ከአንበሳ ጋር ተናንቆ የሚረታ በሰማይ የሚምዘገዘግን ጥይት ሽል ማለት የሚችል ተዋናይ አሚር ኻን ይሰኛል።
Mahi Mahisho
አንድ አንድ ኪሎ ፍርኖ ዱቄት ለችግረኞች መስጠት ፈለገና በይፋ አሳወቀ። ከሚሊየነሮች ተርታ የሚመደብ፣ ቢዘገን የማያልቅ ኃብት ሸክፎ አንድ አንድ ኪሎ ዱቄት ሊሰጥ መሆኑ ሀገሬውን አስገረመ። ስስታም ቆንቋና እያሉ ሰደቡት። ና ከእኛ ውሰድ እያሉ ፎቶውን በዱቄት አቀናብረው ተሳለቁበት። ድንቄም አንድ ኪሎ ዱቄት ቱ እያሉ ረገሙት። መኪና በጣቱ እየጎተተ አሽቀንጥሮ ከገደል ሲወረውር ነበርና የሚታወቀው እየተወነ ይሆን በማለት ሰዎችን አጀብ አሰኘ።
ቀኑ ደረሰና እርዳታውን ለመቀበል ሚስኪኖች ከደጃፉ ላይ ተኮለኮሉ። በገዛ እጁ የቋጠረውን አንድ አንድ ኪሎ ዱቄት ከትልቅ ትህትና ጋር የተቸገሩትን እያቀፈና እየሳመ መስጠቱን ተያያዘው። አጀብ የዚህ ሰው ነገር አሰኘ። ሙሉ ቤተሰብን ቁርስና ምሳ አጥግቦ የማያበላ፣ በመጠኑም በይዘቱም ትንሽ የሆነ፣ ታይቶ የማይታወቅ ሰደቃ እየሰጠ ጭራሽ አቅፎ ይስማቸዋል?! የቀየው ሰው ተዓጀበ።
እርሱ ዘንድ ተሰብስበው የመጡት ግን ይህ በመጠኑ ትንሹሽ የሆነው ዱቄት የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ብቻ ነበሩ። በረሐብ ጠኔ የተገረፉ መሳኪኖች። የዕለት ጉርስ የቸገራቸው ከፊታቸው ገፅ ላይ ርሀብ የሚነበብባቸው ቅልስልስ ኩምሽሽ ያሉ ድሆች።
ዱቄቱን ተቀብለው ወደ ቤታቸው አቀኑ። እሳት አያይዘው ቂጣ ጋግረው ሊበሉ አቡክተው ከምጣዱ ሊጋግሩ ፌስታሉን ሲከፍቱ 15 ሺህ ብር ተጠቅልሎ ከዱቄቱ ላይ አገኙ። የእውነት ለተቸገሩት ሰዎች እርዳታው ደረሰ።
ሰደቃቸው ለትክክለኛ ሰዎች እንዲደርስላቸው የሚመኙና የሚተጉ ሙተሰዲቆች አጀብ ተሰኙበት።
"....በምልክታቸው ታውቃቸዋለህ፡፡ ሰዎችን በችክታ አይለምኑም" ለተባለላቸው ሚስኪኖች ሰደቃን በትክክል ማድረስ ይሉሀል ይህ ነው።
ተጨማሪ ዝርዝር በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://t.me/gimbamedianetwork
በቲክቶክ ፉክክር ህይወቱን ያጣው አሜሪካዊ፤ ሚስቱ ህልፈቱን ቀርጻለች
በአሜሪካ አላባማ ሚስት የባሏን ህልፈት በቪዲዮ ቀርጻ ማስቀረቷ ተነግሯል።
ስሙ ያልተጠቀሰው ግለሰብ በቲክቶክ ተከታዮቹን ለማስደመም ከሚበር ጀልባ ላይ በመዝለል ወደ ባህር ተወርውሮ ነው ውዱን ህይወቱን ያጣው።
በቲክቶክ የተለየ ነገር በማድረግ ተከታዮችን ለማብዛት የሚደረግ ፉክክር የበርካቶችን ህይወት መቀማቱ ይነገራል።
ተጨማሪ ዝርዝር በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://t.me/gimbamedianetwork
