ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር
Open in Telegram
ኦ አሐውየ እለ አፈቅረክሙ ጸልዩ ዲበ ድካምየ ከመ ይዕቀበኒ እግዚእ በዐቢይ ሣህሉ በሃይማኖት ርትዕት እስከ ፍጽሜ ደሓሪት እስትንፋስ። ወዝንቱ ውእቱ ባሕቲቱ ተስፋየ። ወስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ለዓለመ ዓለም አሜን። ሃይ. አበ. ዘቴዎዶስ. ፹፫፡፵፬ https://t.me/joinchat/SWWiqKcuci79Brh9
Show more2 126
Subscribers
No data24 hours
+187 days
+1130 days
Posts Archive
የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ዛሬ ሠኔ ፲፫/፳፻፲፰ ዓ/ም በሳባ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ ለጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች (መዘምራን) ሰፊ ሥልጠና ሰጠ።
"እዜምር በመንፈስየ ወእዜምር በልብየ ለርእስየኒ ወለቢጽየኒ = በነፍሴ እዘምራለሁ፥ በልቤም ለራሴና ለባልንጀራዬ እዘምራለሁ።" ፩ ቆሮ. ፲፬፡፲፭።
በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ ሐምሌ ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም የተዋቀረው የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ በድጓ፣ በአቋቋም በዝማሬ መዋሥእትና በቅዳሴ በመምህርነት እያገለገሉ ላሉ የጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች (መዘምራን) "ያሬዳዊ ዜማና መጽሐፍ ቅዱስ" በሚል ርእስ ሰፊ ሥልጠና አከናውኗል።
ጉባኤውም በጸሎት የተጀመረ ሲሆን የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራአስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል በጉባኤው ለተገኙ የጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክትን ከሰጡ በኋላ ሥልጠናውን በተመለከተ የብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፈዋል። ሥልጠናውንም በአጽንዖት እንዲከታተሉና የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶችን ለምእመናን በሚመጥን አቀራረብ ማድረስ ይቻል ዘንድ ዐደራ ብለዋል።
በመቀጠልም የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት መጋቤ ምስጢር #ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ "ያሬዳዊ ዜማና መጽሐፍ ቅዱስ" በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊ ሥልጠና ሰጥተዋል። በትምህርታቸውም ቅዱስ ያሬድ ከብሉይ፣ ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት፣ ከመነኰሳትና ከታሪክ መጻሕፍት ጠቅሶ ጸዋትወ ዜማን መድረስ መቻሉን በመግለጽ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶች ሁሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የተቀዱ መሆናቸውን በመግለጽ ለምእመናን ማድረስ የሚቻልበትን መንገድ በጥልቀት አብራርተዋል።
በጸዋትወ ዜማ በመምህርነት የተመረቁ በሥልጠናው የተገኙ መምህራንና መሪጌቶችም (መዘምራን) የተሰጣቸው ሥልጠና እጅግ አመርቂ መሆኑን ገልጸው ተገቢ የሆኑ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ለጥያቄዎቻቸውም ተገቢ የሆነ ምላሽ ሥልጠናውን በሰጡት መጋቤ ምስጢር #ያሬድ ዘርአ - ቡሩክ ተሰጥቷቸዋል። መምህራኑም ወንጌልን ይበልጥ ለማስፋፋትና ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን በደስታ ገልጸዋል።
በማያያዝም የሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ክፍል ኀላፊ መልአከ ገነት ቀሲስ #ደሳለኝ ሀብቱና የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኀላፊና የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት መጋቤ ብሉይ #ሠምረ_አብ ገብሬ ልዩ ልዩ መልእክቶችን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራአስኪያጅና የሊቃውንት ጉባኤ ዋና ጸሓፊ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ #ዕንባቆም ገብረ ኪዳን ልዩ የሀገረ ስብከቱ መመሪያና ቃለ ምዕዳን ከሰጡ በኋላ ጉባኤውን በጸሎት አጠናቀዋል።
➖▪➖
የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ቀደም ሲል በ፳፻፱ ዓ/ም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራአስኪያጅ በሆኑት መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል አሳሳቢነት፥ በብፁዕ አቡነ #ዳንኤል መልካም ፈቃድና መመሪያ ሰጪነት የተዋቀረ ሲሆን እንደ ዐዲስ ሐምሌ ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ ልዩ መመሪያ ሰጪነት በሰፊው ተደራጅቶ አመርቂ መንፈሳውያን ተግባራትን በማከናወን ላይ ያለ መሆኑ የሚታወቅ ነው።
#የድሬዳዋ_ሀገረ_ስብከት_ጽሕፈት_ቤት
📢 ለፈጣንና ተአማኒ መረጃዎች
➩የፌስቡክ ገጻችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61563382452089
➩የቲክቶክ ገጻችን👇
https://www.tiktok.com/@ddhagersebektmedia
➩የቴሌግራም ገጻችን👇
https://t.me/ddhageresebket
#Follow #Share #Like #ያድርጉ_ቤተሰብ_ይሁኑ
• ቅኔ ዘሠኔ ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም
፩. ግእዝ ጉባኤ ቃና
• በሌሊት ብርሃነ እንዘ ያበርህ ጥዩቀ፥
• ብሩህ ኮከብ ሊቀ ብርሃናት ሠረቀ።
፪.፩. ዕዝል ጉባኤ ቃና
• ኵሉ ለያጽልል ተትሒቶ መትሕተ ሊቃውንት አእዋም፥
• እስመ ከመ ይዝንም ግብተ ሀለዎ ለቅኔ ያሬድ ዝናም።
፪.፪. ዕዝል ጉባኤ ቃና
• ሚካኤል ቀሲስ በጽንሓሕከ ለቤተ ክርስቲያን ምርጕዛ፥
• መዓዛ ዕጣንከ ፍቅረ ዐዋዴ ለኢትዮጵያ አምዕዛ።
፫. ዘአምላኪየ
• ለአርዌ ዐመፃ ወሞት ዘኢሐደገ እከዮ፥
• ሚካኤል እምኢትዮጵያ ፍጡነ ደርብዮ፥
• ወለዘበሕምዙ ደወየ ቀዲሙ በምሕረትከ አጥዕዮ።
፬. ሚ በዝሑ
• ነዳየ ሐጕለ ፀር ባሕራን በሠይጠ መጽሐፍ አእተተ ንዴተ ሐጕለ ፀር ወሱታፉ፥
• አምጣነ አኮ ነዳይ ዘይትረሳዕ ለዝሉፉ፥
• ወበሀብተ መጽሐፍ ከብረ በዐይነ ሚካኤል አንባቢ እስመ ይትነበብ መጽሐፉ።
፭.፩. ዋይዜማ
• ቤተ ክርስቲያን አፎምያ ዘባቲ ሐለፈ አስተራኒቆስ ሰላም፥
• አውሥአቶ ነገረ መስቀል ለመልአክ ሕሡም፥
• ወአይቴ ሀለወ ትእምርተ መስቀልከ ዮም፥
• ትቤሎ፦ ቅድመሰ ዘሖርከ ኀበ ማርያም፥
• ብሥራታዊ ብሥራተከ ሢም።
፭.፪. ዋይዜማ
• ሚካኤል ግብረ ዚኣከ ግብረ መደልው ውእቱ እስመ ከመ ታዘልፍ ዘልፈ፥
• ቀዊመከ ማእከለ ፍኖት ታነብብ መጽሐፈ፥
• ወታነውሕ ቃለ ኀበ ኀበ ትከሥት አፈ፥
• መሠረተከሂ አሐዘ ወአስተናደፈ፥
• ውስተ ባሕር ዘገደፈ እልፈ።
፮. መስኮት ዋይዜማ
• መልአከ ጽልመት ለአፎምያ ያመክራ ምዕረ እመ ውስተ ቤታ የአቱ፥
• ዘምስሌነሰ ይነብር በበ ዕለቱ፥
• እስመ ንሕነ ለሰይጣን አዕርክቱ።
፯. ሐፂር ዋይዜማ
• ምዝጋናየ እምይትባኅነኒ መዊተ እፈቱ፥
• አምጣነ ቅኔ ሀብትየ ወሕይወትየ ውእቱ።
• (ምዝጋናየ እምይትባኅነኒ መዊተ እፈቱ፥)
፰. ሥላሴ
• መላእክት እኩያን መላእክተ ብርሃን ተመሲሎሙ በኢትዮጵያ ተርእዩ አኮኑ እንዘ ይትመያየጡ ስብዐ፥
• ሚካኤል ሰይፈ መዓትከ ነሢአከ ነዐ፥
• ወበላዕሌሆሙ ኩን እንከሰ ዘእምልብከ ቍጡዐ፥
• ወኢትትመሰሎሙ መዘንግዐ፥
• ምሕረተከሂ ይነጽር ኵሉ ዘበፅዐ፥
• እምኀቤከ ለይትመጦ ጽንዐ።
፱.፩. ዘይእዜ
• ሚካኤል ለምንት አርምሞትከ እስመ ውስተ ቤትከ ጽድቅ እንበለ ይኩን ማእምረ፥
• መልአከ ብርሃን ተመሲሎ እኩይ መልአከ ጽልመት አሐዘ መንበረ፥
• ይትሐደግሰ ወንጌል መልክዐ መልክዕ ኢተምህረ፥
• ትምህርተ ጽድቅሂ ይትመሀር ለእመ ተነግረ፥
• ሐዲጎ ትምህርተ አፎምያሀ አፍቀረ።
• (ትምህርተ ጽድቅሂ ይትመሀር ለእመ ተነግረ፥)
፱.፪. ዘይእዜ
• ሶበ ኮነ ቀትር ጽልሑተ ጸር ለሐላፌ ፍኖት ባሕራን ኢረከባሁ ድካም፥
• ምጽላለ ሕይወት እስመ ኮኖ ዘበቈለ ማእከለ ፍኖት ሚካኤል ኦም፥
• ወውእቱ ኦም ሚካኤል ዘይጌርም፥
• መድሓኒት ውእቱ ለዘየሐምም፥
• ወእምአፎምያ ተግሕሠ ደዌ ምክረ ፀር ሕሡም።
(መድሓኒት ውእቱ ለዘየሐምም፥)
፲. ሣህልከ
• እመኒ በሐይል እምእለ ነግሡ፥
• በኢትዮጵያ ድንግል አድሕኖተነ ተኀሡ፥
• ሚካኤል አርምሞተከ ወተደሞተከ ገብርኤል አግሕሡ።
፲፩. ሐፂር ሣህልከ
• ሚ ትትሜዐዝ ደብረ ምሕረት፥
• እስመ በላዕሌሃ ይውሕዝ #በርቶሎሜዎስ ዕፍረት።
• (ሚ ትትሜዐዝ ደብረ ምሕረት)
፲፪. መወድስ
• መልእክተ ሕይወት ይኩን ከመ ተወለጠ ጦማረ ሞቱ ለባሕራን ዘይትአመን ረድኤተ፥
• ከመ ምስሌሁ ለባሕራን ለእመ ምስሌነ አንተ፥
• መልአከ ሕይወት ሚካኤል ወልጥ ጦማረ ሞትነ ወአሰስል ሞተ፥
• ወመልእክተ ሞትነ ደምሲሰከ በሰሌዳ ሰብእነ ጸሐፍ ፊደለ መጻሕፍት ሕይወተ፥
• እግዚእነሂ ኢይደሉ አርምሞትከ እስፍንተ፥
• ሰብእ ላዕለ ሰብእ እስመ ኮኑ አራዊተ፥
• ወበአፈ ዳዊት እብለከ ለእመ ሰማዕከኒ ሊተ፥
• ከዐው ላዕሌሆሙ መዓተ ወመቅሠፍተ።
፲፫. ኵልክሙ መወድስ
• ዕንጦንስ ብኪ በይነ ደቂቅከ እስመ ደቂቅከ ኀልቁ ውስተ ማዕበለ ግዮን ትዕይንት፥
• አመ ውስተ ገዳም ኮነ አፍቅሮ ንዋይ ክረምት፥
• ወመፍትው መቃርስ ከመ ትበል ትኩዝየ በመዋዕልየ አንሶሱ ለምንት፥
• ሚካኤል ዘወሀበከ አስኬማከ ለከ መዝገበ ንዋይ (ምክንያተ ሞት) እስመ ኮነት።
• አመሂ የሐልፉ ማእከለ አድባር ማያት፥
• ይትዌከፉ ለጽምኦሙ ሐለስዮታት መነ**ሳት፥ (መዝ. ፻፫፡፲፩)
• ወእምጋኔነ ቀትር ረቂቅ ወእሞተ ግብት፥
• መሐረነ አምላክነ አምላከ ጻድቃን ወሠማዕት።
• ወኢይኩን ብነ ዘቤተ ክርስቲያን ድቀት።
• መሐረነ አምላክነ አምላከ ጻድቃን ወሠማዕት።
፲፬. ሐፂር ኵልክሙ መወድስ
• ቅኔ መዓር ዘምስለ ማኅሌት ሐሊብ፥
• እስመ ቀርበ እንዘ ይጻውዑ ተጋብኡ ህዝብ።
፲፯. ዕዝል ክብር ይእቲ
• መኰንነ ጽድቅ ክርስቶስ እመ ፈቀድከ ከመ ንትጋዐዝከ ለከ፥
• አኮ ርቱዕ ዘዕለተ ዐርብ ፍትሕከ፥
• እስመ እንዘ ፍቅር አንተ ነፍስተ ይሁዳ ጸላእከ፥
• ወእምክልኤቱ ፈያት ለአሓዱ ግብረ አድልዎ ፈጸምከ።
፲፰. ዕዝል ዕጣነ ሞገር
• ምሕረተ ሚካኤል ፅንስት ዘበዘያንጸበርቅ ሥና፥
• ኵሉ ይትሜነይ ይጸወና፥
• ጊዜ ወሊዶታ ድሕረ አልጸቀ ለእመ ኢረከበት ዳሕና፥
• ወለእመ ኢቆመት በጥዒና፥
• ውስተ ቤተ ሐኪም ትሑር እንዘ ሀለወት በፍና፥
• ወለደቶ ማእከለ ፍኖት ለባሕራን ህፃና።
ዐሠረ ነጋሢ
• ኦ #መልአክ ዘልማድከ #ዘሐይለ_ማርያም ትሕትና፥
• አስምዐነ ለነ #ዘበርተሎሜዎስ ዜና፥
• በዘማርያም ቅድስና፥
• ወትንቢተ #ዕንባቆም ንስማዕ #እምገብረ_ሐና፥
• ጸግወነ ንጹሀ ልቡና።
➖▪➖
• ሠኔ ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም
• ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል
• ጊዜ ፮ ሰዓተ ሌሊት
• መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
በውጪ ሀገር ያሉ ቅኔ ለመማር፦
የሚከተለውን ሊንክ ጠቅ አድርገው በመግባት መመዝገብ ይችላሉ፦ https://t.me/kineyared
ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/yaredzer
በድሬዳዋ መንበረ ጵጵስና በርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በየዓመቱ ሠኔ ፲፪ የሚከበረው በኀይላት ላይ የተሾመው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ዛሬ ሠኔ ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም በታላቅ ድምቀት ተከብሮ በዋለው ዓመታዊ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስም ከሌሊት ጀምሮ መንፈሳዊውን አገልግሎት መርተዋል።
ጠዋት ላይ በተከናወነው የወንጌል መርሐ ግብርም በዐዲስ ዐበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔ ዓለም ካቴድራል የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የሆኑት መጋቤ ሐዲስ መልአክ አማረ "ለሰው በሚያደርገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ሚካኤል ነው።" (መጽሐፈ ሄኖክ. ፮፥፭) በሚል ርእስ ተነሥተው ስለ ቅዱስ ሚካኤል ምልጃና ጸሎት፣ አዳኝነትና ተራዳኢነት... ሰፊ ትምህርት አስተምረዋል።
በመቀጠልም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ምክትል ኀላፊ የሆኑት መምህር ዘማርያን ጌጡ "አንሣእኩ አዕይንትየ መንገለ አድባር = ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ" (መዝ. ፻፳፡፩) በሚል ርእስ ተነሥተው ስለ እግዚአብሔር ጌትነት፣ አምላክነት፣ ቸርነት፣ ምሕረትና ይቅርታ... ሰፊ ትምህርት አስተምረዋል።
በማያያዝም ብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ "እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?” (ዮና. ፫፡፱) በሚል ርእስ ተነሥተው ስለ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያና ስለ ሕዝቧ ደኅንነት ስለ መጸለይ፣ በያዝነው ጾመ ሐዋርያት ንስሓ ስለ መግባት፣ በፍቅር እግዚአብሔርን ስለ ማምለክ፣ ስለ ሀገራዊ አንድነትና ሕብረት... ሰፊ ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ ሰጥተዋል።
በዓሉም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል፣ የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራአስኪያጅ ቆሞስ አባ #ዕንባቆም ገብረ ኪዳን የሀገረ ስብከቱ የየክፍሉ ኀላፊዎች፣ የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሓፊያን፣ መምህራን፣ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ ዲያቆናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን/ትና መላው ማኅበረ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በመጨረሻም ከቀኑ ፱ ላይ ልዩ የአምልኮ ጊዜ የሆነው የቅዳሴ መንፈሳዊ አገልግሎት ከተጠናቀቀ በኋላ በዓሉ በብፁዕ አባታችን አቡነ #በርተሎሜዎስ በጸሎትና በቡራኬ ተጠናቋል።
#የድሬዳዋ_ሀገረ_ስብከት_ጽሕፈት_ቤት
📢 ለፈጣንና ተአማኒ መረጃዎች
➩የፌስ ቡክ ገጻችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=61563382452089
➩የቲክቶክ ገጻችን👇
https://www.tiktok.com/@ddhagersebektmedia
➩የቴሌግራም ገጻችን👇
https://t.me/ddhageresebket
#Follow #Share #Like #ያድርጉ_ቤተሰብ_ይሁኑ
ቅዱስ ጳውሎስም “አገልግሎታችን እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም” ሲል ምክንያት እየፈጠርን ከመንፈሳዊ ሕይወትና ከአገልግሎት ወደ ኋላ ማለት እንደሌለብን አስተምሮናል። ፪ ቆሮ. ፮፥፫። በጾም ወቅት መጸለይ፣ መመጽወትና መስገድ በጾም የምናገኘውን ዋጋ ከፍ ያደርገዋል።
ሁላችንም ጾሙን በደስታና በፍቅር ጾመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እናገኝ ዘንድ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ምልጃና ጸሎት አይለየን! አሜን!
“ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ - ጾምን እንጹም! ፤ እርስ በርሳችንም እንዋደድ!” ቅዱስ ያሬድ
“ወአንትሙኒ ጹሙ ወሰአሉ ኀቤሁ ሥርየተ ኃጢአት = እናንተም ጹሙ፤ የኃጢአትንም ሥርየት ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) ዘንድ ለምኑ።” ዲድ. ፴፡፷፮።
ጾም ማለት “መተው፣ መጠበቅ፣ መከልከል” ማለት ነው። ጾም ከምግብ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ተግባር ሁሉ መቈጠብ ጭምር ነው። ሠለስቱ ምእትም “ጾምሰ ተከልኦተ ብእሲ እመብልዕ በጊዜ ዕውቅ በውስተ ሕግ - ጾምስ በታወቀው ሰዓት፣ በታወቀው ዕለት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው” በማለት የጾምን ትርጕም አስረድተዋል። ፍት. መን. ፲፭፡፭፻፷፬።
ጾም በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን የታወቀ፣ በነቢያት የነበረ፣ በክርስቶስ የጸና፣ በሐዋርያት የተሰበከ እና የተረጋገጠ መንፈሳዊ ሕግ፤ ፈጣሪን መለመኛ መንፈሳዊ መሣሪያ ነው። ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን ልዑል እግዚአብሔር የመሠረተው፣ ከእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የተሰጠ የመጀመሪያው ትእዛዝ ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰብዓቱ አጽዋም የምንላቸው፡- ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)፣ ጾመ፣ ነነዌ፣ ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ሐዋርያት ቀዳማይ (የሠኔ ጾም)፣ ጾመ ሐዋርያት ካልኣይ (የፍልሰታ ጾም)፣ ጾመ ድኅነት እና ጾመ ገሃድ ናቸው።
ዛሬ ግንቦት ፳፬/፳፻፲፰ ዓ/ም የጀመርነው ጾምም ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የአገልግሎታቸው መጀመሪያቸው ያደረጉት ጾም ነው። ይህንም ጾም ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት ስለ ሁለት ዓላማ ነው። አንደኛው ስለ ተሰጣቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ አምላካቸውን ለማመስገን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በዓለሙ ሁሉ ዞረው ለሚሰብኩት ወንጌል ራሳቸውን ለማዘጋጀት ነው። ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ መጾማቸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አብነት አድርገው ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማየ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ሲጠመቅ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ጌትነቱን ለመመስከር ከወረደ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ በዚያ ፵ መዓልትና ፵ ሌሊት ጾሟልና እነርሱ ደግሞ ኀይል ይሆናቸው ዘንድ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ከተቀበሉ በኋላ ጾምን የሥራቸው ሁሉ መጀመሪያ አድርገዋል።
ከሐዋርያት በመቀጠል የተነሡ ክርስቲያኖችም ይህን የሐዋርያትን ጾም በየዓመቱ ይጾሙ ነበር። እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስም የሐዋርያት ጾም የሚጀምረው ከጰራቅሊጦስ አንድ ሳምንት በኋላ ነበር። “ወእምድኅረ በዓለ ኀምሳ ግበሩ በዓለ ሰቡዐ ዕለተ ወእምዝ ጹሙ እስመ መፍትው እንከ ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ እስመ ከፈለነ ንንሣእ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ።” (ዲድ. ፴፥፷) እንዲልም እስከ ድሜጥሮስ ዘመን ድረስ በዓለ ጰራቅሊጦስ በዋለ በሳምንቱ ጾመ ሐዋርያት ይጾም ነበር። በኋላ ግን ድሜጥሮስ የአጽዋማትን ቀመር ሲቀምር በዓለ ጰራቅሊጦስ በተከበረ በማግስቱ ጾመ ሐዋርያት እንዲጾም አድርጓል።
እንደ ቅዱስ ድሜጥሮስ ቀመርም በ258 ዓ/ም ከበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግሥት አንሥቶ የሐዋርያት በዓለ ዕረፍት እስከሚውልበት እስከ ሐምሌ ፭ ድረስ (The Feast of the Holy Apostles) እንዳጾም አባቶች ወስነዋል። ሐምሌ ፭ የጾሙ ማጠናቀቂያ እንዲሆን የተወሰነበት ምክንያትም ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ በኔሮን ቄሳር በሮም ዐደባባይ ሰማዕትነት የተቀበሉበትን ዕለት ዐብሮ ለማሰብ ነው።
በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተገለጸው ጾም የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፦
• ሰማያዊ ክብርንና ጸጋን ያስገኛል። (፩ ነገ. ፲፱፥፰)
• አጋንንትን ያስወጣል። (ማር. ፱፡፳፱፤ ኢያ. ፯፡፮-፱)
• በመንግሥተ ሰማያት ለመኖር የሚያስችል ምግባርን ያሠራል። (ሉቃ. ፮፥፳፩)
• ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቅርታንና ምሕረትን ለማግኘት ይረዳል።
• አጋንንትና ጠላትን ድል ለማድረግ ያግዛል። (ማቴ. ፬፥፲፩)፤
• ፈቃደ እግዚአብሔርን ለመፈጸም ይረዳል። (፩ ነገ. ፲፱፥፩)
• ከእግዚአብሔር ቍጣ ለመዳን ያስችላል። (ዮና. ፫፥፩)
• የተደበቀ ምስጢርን ይገልጣል። (ዳን. ፲፥፲፬)
• መንፈሳዊ ኀይልን ያሰጣል። (፩ኛ ሳሙ. ፯፥፭)
• ጥበብን ይገልጣል። (ዕዝ. ፯፥፮፤ ዳን. ፱፥፪)
• በመላእክት ጠባቂነት ለመኖር ያስችላል። (ዘፀ. ፲፬፥፲፱. ሐዋ. ፲፥፫)
• ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ያስገዛል። (ፍት. ነገ. ፲፭፥፭፻፷፬)
• የሥጋን ምኞት ያጠፋል።
• የነፍስ ቊስልን ያደርቃል።
• መላእክትን መስሎ ለመኖር ያስችላል።
• ልዩ ልዩ መከራን ያቃልላል።
• ጸጥታን እና ርጋታን ያስተምራል።
• ከቅዱሳን በረከት ያሳትፋል።
• ሕይወትን ያድሳል።
• ክሕደትንና ጥርጥርን በማጥፋት እምነትን ለማጠንከር ይረዳል።
• ዕድሜን ያረዝማል።
• ትዕግሥትን ያስተምራል።
ጾም ከሚያስገኘው መንሳዊ ጸጋና በረከት ባሻገር በርካታ ሥጋውያን ጥቅሞችም እንዳሉት በጾም ዙሪያ የተደረጉ ልዩ ልዩ ሳይንሳዊ ጥናቶች ያሳያሉ። በጥናቶቹ መሠረትም ጾም፡- የደምና የስኳር መጠንን ይቈጣጠራል፤ የአንጎል እንቅስቃሴ የተቀላጠፈ እንዲሆን ያደርጋል፤ የስብ ክምችትን ይቀንሳል፤ የምግብ መፍጨት ሥርዐታችንን ያስተካክላል፤ የካንሰር ሕዋሳት ዕድገትን ይከላከላል፤ የጠራ የሰውነት ቈዳ እንዲኖረን ያደርጋል፤ በሽታ የመከላከል ዐቅምን ይጨምራል።
በአጠቃላይ ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ አይደለም፤ የመሠረተውም ራሱ ልዑል እግዚአብሔር ነው። አምላካችን አዳምና ሔዋንን “ዕፀ በለስን አትብሉ!” ብሎ ባዘዛቸው ጊዜ የጾም ሕግን ሠርቶልናል። በዚህም “ጾም የመጀመሪያ ትእዛዝ ናት” እንላለን።
አዳም በመብል ምክንያት ሕገ እግዚአብሔርን በመጣሱ ነው ከክብሩ የወረደው። እኛም ብንጾም እንጠቀማለን፤ ባንጾም ደግሞ በረከትን እናጣለን።
ቅዱስ ዳዊት “ሥጋዬ ቅቤ በማጣት ከሳ” (መዝ. ፻፱፥፳፬)፤ ነቢዩ ዳንኤልም “ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም፤ ሥጋ እና ጠጅም በአፌ አልገባም” (ዳን. ፲፥፫) ብለው እንደ ተናገሩ በጾም ወቅት ከጥሉላት ምግቦች ሊከለከሉ ይገባል።
ቅዱስ ጳውሎስ “መብል ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጐድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም” ብሎ ማስተማሩም ከመብል ተከልክለን መጾማችን ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት መንገድ መሆኑን ያመላክታል። ሮሜ. ፲፬፥፯፤ ፩ ቆሮ. ፰፥፰።
የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ብንያሚ’ም “ንኩን ድልዋነ ይእዜ ኦ አኀውየ ወፍቁራንየ ለጾም ወለመልእክተ እግዚአብሔር ወለኵሉ ምግባረ ሠናይ ዘምሉእ ትሩፋተ ወፈድፋደሰ ለሃይማኖት እንተ ኢትጸንን ዘሥሉስ ቅዱስ - ወንድሞቼና ወዳጆቼ ሆይ! አሁንም ለጾም፣ እግዚአብሔርን ለማገልገል፣ ትሩፋትን ለተመላ በጎ ሥራ ሁሉ፣ ይልቁንም ጽነት ለሌለባት (በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ ብለን) ለምናምንባት ሃይማኖት የተዘጋጀን እንሁን።” ብሏል። ብንያ. ሃይ. አበ. ፹፱፡፪።
ጾም ቍስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ ኀይለ ፍትወትን የምታደክም፣ የበጎ ምግባራት ሁሉ መጀመሪያ፣ ጸጋ እግዚአብሔርን የምታሰጥ፣ ለፅሙዳን ክብራቸው፣ ለደናግል የንጽሕና ጌጣቸው፣ የጸሎት እናት፣ የዕንባ መገኛ ምንጭ፣ አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ሥራ ሁሉ የምታነቃቃ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ መድኃኒተ ነፍስ ናት። ማር ይስሐቅ አን. ፬፤ ምዕ. ፮።
ጾም ለሁሉም ክርስቲያን ሕግ ሆኖ የተሰጠ የአምላክ ትእዛዝ ነውና አንድ ክርስቲያን “ጾም አልጾምም” የማለት ሃይማኖታዊ ሥልጣን የለውም። ምክንያቱም ነቢየ እግዚአብሔር ኢዩኤል “ጾምን ቀድሱ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ” በማለት መጾም፣ መጸለይ ክርስቲያናዊ ግዴታ መሆኑን ነግሮናል። ኢዩ. ፪፥፲፭።
ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃና የምስጋና መርሐ-ግብር!
ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ዘጨጎዴ፤ ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ በጎጃም ጨጎዴ ሐና የሦስቱ ማለትም የዋድላ፣ የዋሸራና የጎንጅ—የቅኔ ምስክርና የትርጓሜ መጻሕፍት መምህር በመሆን፣ የሀገር ኩራት የሆነውን የግእዝ ቋንቋና የቅኔ ጥበብን እስከነ ዐዋጁ፣ አገባቡ፣ ግሱና ዕርባ ቅምሩ በማስፋፋት የሀገር በቀል እውቀት ማዕከል ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል።
በዚሁ ታላቅ የትምህርትና የጥበብ ጉዞ ውስጥ ያፈሩትና አሻራቸውን ያሳረፉበት የሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሺፈራው “ሐመረ ቅኔ” የቅኔ እና አገባብ መጽሐፍ ምረቃ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በድምቀት ይመረቃል።
በዕለቱ:-
🗞የመጽሐፍ ምረቃ እና ትንታኔ፦
በዕውቅ ተጋባዥ ምሁራን የሚቀርብ ጥልቅ የዳሰሳ ትንታኔ።
🗞የ50 ዓመታት የዕድሜ ልክ ምስጋና
ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ለግእዝ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ላበረከቱት የግማሽ ክፍለ ዘመን (50 ዓመታት) ታላቅ አበርክቶ የሚገባቸው የክብር ምስጋና ይቸራቸዋል።
🗞ደማቅ የቅኔ ማዕበል
በሊቀ ሊቃውንት ያሬድ የቀድሞ ተማሪዎች (ደቀ መዛሙርት)፣ በሥጋ ልጃቸው መጋቤ አዕላፍ ቅዱስ ያሬድ (በባሕር ዳር ሰላም አርጊው የቅኔ ጉባዔ ቤት ከ6ሺህ በላይ ተማሪ ያላቸው) የሚቀርብ ልብን የሚያረሰርስ የቅኔ ድግስ።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍን ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ 3ኛ ዲግሪ (PhD) በማስተማር ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ለግእዝ ቋንቋ ዕድገትና ልማት አጠንክሮ መስራቱን ይቀጥላል።
ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣ ምሁራን እንዲሁም የቅኔ ሊቃውንት በተገኙበት በዚህ ታላቅ መርሐ ግብር ይካሄዳል።
📅 ቅዳሜ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ
📍ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ዊዝደም (ጥበብ) ግቢ፣ በጥበብ አዳራሽ
+4
"ኩኑ ገባርያነ ሕግ ለርእስክሙ፥ ወኩኑ መምህራነ ለካልኣኒክሙ = ለራሳችሁ ሕግን የምትጠብቁ ሁኑ፤ ሌሎችንም የምታስተምሩ ሁኑ!" ሃይ. አበ. ፻፳፭፡፲፮
📌 በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ በሳል አመራር በሚመራው በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዛሬ ሚያዝያ ፳፩/፳፻፲፰ ዓ/ም ስለ ሊቃውንት ጉባኤ አደረጃጀት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተከናውኗል።
📌 በዚህ ልዩ የሥልጠና መርሐ ግብርም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል፣ የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ #ዕንባቆም ገብረ ኪዳን፣ የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያው ክፍል ኀላፊዎች፣ የሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሓፊዎች፣ የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህራንና ሰባክያነ ወንጌል የተገኙ ሲሆን ሥልጠናው በጸሎት ተጀምሯል።
📌 በመጀመሪያው ክፍለ ትምህርትም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት ጸባቴ ቆሞስ አባ #ኀይለማርያም አረጋ "...ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ!" (፩ ጴጥ. ፪፡፩-፫) በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
📌 በሁለተኛው ክፍለ ትምህርትም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ "የሊቃውንት ጉባኤ አመሠራረት እና አሁን ያለበት" በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊና ጥልቅ ትምህርት ሰጥተዋል።
📌 የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤም በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ መመሪያ ሰጪነት እንደ ዐዲስ ተዋቅሮ ሰባት አባላት ያሉት ሲሆን ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ አመርቂ የሆኑ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ያለ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።
"ኢየሱስ ክርስቶስ የይሁዳ እግርን ጨምሮ የሁሉም ደቀ መዛሙርቱ እግሮችን ካጠበ በኋላ የደቀ መዛሙርቱን እግሮች ባጠበበት ውኃ የራሱን እግሮች በራሱ እጅ ዐጥቧል።"
"ኦ ትሕትና ዘመጠነ ዝ ትሕትና"
ዛሬ በዓለ እግዚአብሔር ነው። ዕለቱም የሕማማት ሁለተኛ ቀን ማክሰኞ ነው።
ለእግዚአብሔር የሚገባውን የአምልኮ ስግደታችሁን ስገዱ!
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
