ru
Feedback
ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር

ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር

Открыть в Telegram

ኦ አሐውየ እለ አፈቅረክሙ ጸልዩ ዲበ ድካምየ ከመ ይዕቀበኒ እግዚእ በዐቢይ ሣህሉ በሃይማኖት ርትዕት እስከ ፍጽሜ ደሓሪት እስትንፋስ። ወዝንቱ ውእቱ ባሕቲቱ ተስፋየ። ወስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ለዓለመ ዓለም አሜን። ሃይ. አበ. ዘቴዎዶስ. ፹፫፡፵፬ https://t.me/joinchat/SWWiqKcuci79Brh9

Больше
2 111
Подписчики
-224 часа
-37 дней
-330 день
Архив постов
ሃይማኖተ አበው ፹፫፡፳፭-፵፬

"እለ ውስተ ሞቅሕ አድሕን ወለኵልነ ኩን ጸወነ።"
"እለ ውስተ ሞቅሕ አድሕን ወለኵልነ ኩን ጸወነ።"

ቅዱስ ጳውሎስም “አገልግሎታችን እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም” ሲል ምክንያት እየፈጠርን ከመንፈሳዊ ሕይወትና ከአገልግሎት ወደ ኋላ ማለት እንደሌለብን አስተምሮናል። ፪ ቆሮ. ፮፥፫። በጾም ወቅት መጸለይ፣ መመጽወትና መስገድ በጾም የምናገኘውን ዋጋ ከፍ ያደርገዋል። ሁላችንም ጾሙን በደስታና በፍቅር ጾመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እናገኝ ዘንድ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ምልጃና ጸሎት አይለየን! አሜን! “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ - ጾምን እንጹም! ፤ እርስ በርሳችንም እንዋደድ!” ቅዱስ ያሬድ

“ወአንትሙኒ ጹሙ ወሰአሉ ኀቤሁ ሥርየተ ኃጢአት = እናንተም ጹሙ፤ የኃጢአትንም ሥርየት ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) ዘንድ ለምኑ።” ዲድ. ፴፡፷፮። ጾም ማለት “መተው፣ መጠበቅ፣ መከልከል” ማለት ነው። ጾም ከምግብ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ተግባር ሁሉ መቈጠብ ጭምር ነው። ሠለስቱ ምእትም “ጾምሰ ተከልኦተ ብእሲ እመብልዕ በጊዜ ዕውቅ በውስተ ሕግ - ጾምስ በታወቀው ሰዓት፣ በታወቀው ዕለት ሰው ከምግብ የሚከለከለው መከልከል ነው” በማለት የጾምን ትርጕም አስረድተዋል። ፍት. መን. ፲፭፡፭፻፷፬። ጾም በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን የታወቀ፣ በነቢያት የነበረ፣ በክርስቶስ የጸና፣ በሐዋርያት የተሰበከ እና የተረጋገጠ መንፈሳዊ ሕግ፤ ፈጣሪን መለመኛ መንፈሳዊ መሣሪያ ነው። ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን ልዑል እግዚአብሔር የመሠረተው፣ ከእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የተሰጠ የመጀመሪያው ትእዛዝ ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰብዓቱ አጽዋም የምንላቸው፡- ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)፣ ጾመ፣ ነነዌ፣ ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ሐዋርያት ቀዳማይ (የሠኔ ጾም)፣ ጾመ ሐዋርያት ካልኣይ (የፍልሰታ ጾም)፣ ጾመ ድኅነት እና ጾመ ገሃድ ናቸው። ዛሬ ግንቦት ፳፬/፳፻፲፰ ዓ/ም የጀመርነው ጾምም ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የአገልግሎታቸው መጀመሪያቸው ያደረጉት ጾም ነው። ይህንም ጾም ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት ስለ ሁለት ዓላማ ነው። አንደኛው ስለ ተሰጣቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ አምላካቸውን ለማመስገን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በዓለሙ ሁሉ ዞረው ለሚሰብኩት ወንጌል ራሳቸውን ለማዘጋጀት ነው። ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ መጾማቸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አብነት አድርገው ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማየ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ሲጠመቅ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ጌትነቱን ለመመስከር ከወረደ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ በዚያ ፵ መዓልትና ፵ ሌሊት ጾሟልና እነርሱ ደግሞ ኀይል ይሆናቸው ዘንድ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ከተቀበሉ በኋላ ጾምን የሥራቸው ሁሉ መጀመሪያ አድርገዋል። ከሐዋርያት በመቀጠል የተነሡ ክርስቲያኖችም ይህን የሐዋርያትን ጾም በየዓመቱ ይጾሙ ነበር። እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስም የሐዋርያት ጾም የሚጀምረው ከጰራቅሊጦስ አንድ ሳምንት በኋላ ነበር። “ወእምድኅረ በዓለ ኀምሳ ግበሩ በዓለ ሰቡዐ ዕለተ ወእምዝ ጹሙ እስመ መፍትው እንከ ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ እስመ ከፈለነ ንንሣእ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ።” (ዲድ. ፴፥፷) እንዲልም እስከ ድሜጥሮስ ዘመን ድረስ በዓለ ጰራቅሊጦስ በዋለ በሳምንቱ ጾመ ሐዋርያት ይጾም ነበር። በኋላ ግን ድሜጥሮስ የአጽዋማትን ቀመር ሲቀምር በዓለ ጰራቅሊጦስ በተከበረ በማግስቱ ጾመ ሐዋርያት እንዲጾም አድርጓል። እንደ ቅዱስ ድሜጥሮስ ቀመርም በ258 ዓ/ም ከበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግሥት አንሥቶ የሐዋርያት በዓለ ዕረፍት እስከሚውልበት እስከ ሐምሌ ፭ ድረስ (The Feast of the Holy Apostles) እንዳጾም አባቶች ወስነዋል። ሐምሌ ፭ የጾሙ ማጠናቀቂያ እንዲሆን የተወሰነበት ምክንያትም ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ በኔሮን ቄሳር በሮም ዐደባባይ ሰማዕትነት የተቀበሉበትን ዕለት ዐብሮ ለማሰብ ነው። በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ተገለጸው ጾም የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፦ • ሰማያዊ ክብርንና ጸጋን ያስገኛል። (፩ ነገ. ፲፱፥፰) • አጋንንትን ያስወጣል። (ማር. ፱፡፳፱፤ ኢያ. ፯፡፮-፱) • በመንግሥተ ሰማያት ለመኖር የሚያስችል ምግባርን ያሠራል። (ሉቃ. ፮፥፳፩) • ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቅርታንና ምሕረትን ለማግኘት ይረዳል። • አጋንንትና ጠላትን ድል ለማድረግ ያግዛል። (ማቴ. ፬፥፲፩)፤ • ፈቃደ እግዚአብሔርን ለመፈጸም ይረዳል። (፩ ነገ. ፲፱፥፩) • ከእግዚአብሔር ቍጣ ለመዳን ያስችላል። (ዮና. ፫፥፩) • የተደበቀ ምስጢርን ይገልጣል። (ዳን. ፲፥፲፬) • መንፈሳዊ ኀይልን ያሰጣል። (፩ኛ ሳሙ. ፯፥፭) • ጥበብን ይገልጣል። (ዕዝ. ፯፥፮፤ ዳን. ፱፥፪) • በመላእክት ጠባቂነት ለመኖር ያስችላል። (ዘፀ. ፲፬፥፲፱. ሐዋ. ፲፥፫) • ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ያስገዛል። (ፍት. ነገ. ፲፭፥፭፻፷፬) • የሥጋን ምኞት ያጠፋል። • የነፍስ ቊስልን ያደርቃል። • መላእክትን መስሎ ለመኖር ያስችላል። • ልዩ ልዩ መከራን ያቃልላል። • ጸጥታን እና ርጋታን ያስተምራል። • ከቅዱሳን በረከት ያሳትፋል። • ሕይወትን ያድሳል። • ክሕደትንና ጥርጥርን በማጥፋት እምነትን ለማጠንከር ይረዳል። • ዕድሜን ያረዝማል። • ትዕግሥትን ያስተምራል። ጾም ከሚያስገኘው መንሳዊ ጸጋና በረከት ባሻገር በርካታ ሥጋውያን ጥቅሞችም እንዳሉት በጾም ዙሪያ የተደረጉ ልዩ ልዩ ሳይንሳዊ ጥናቶች ያሳያሉ። በጥናቶቹ መሠረትም ጾም፡- የደምና የስኳር መጠንን ይቈጣጠራል፤ የአንጎል እንቅስቃሴ የተቀላጠፈ እንዲሆን ያደርጋል፤ የስብ ክምችትን ይቀንሳል፤ የምግብ መፍጨት ሥርዐታችንን ያስተካክላል፤ የካንሰር ሕዋሳት ዕድገትን ይከላከላል፤ የጠራ የሰውነት ቈዳ እንዲኖረን ያደርጋል፤ በሽታ የመከላከል ዐቅምን ይጨምራል። በአጠቃላይ ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ አይደለም፤ የመሠረተውም ራሱ ልዑል እግዚአብሔር ነው። አምላካችን አዳምና ሔዋንን “ዕፀ በለስን አትብሉ!” ብሎ ባዘዛቸው ጊዜ የጾም ሕግን ሠርቶልናል። በዚህም “ጾም የመጀመሪያ ትእዛዝ ናት” እንላለን። አዳም በመብል ምክንያት ሕገ እግዚአብሔርን በመጣሱ ነው ከክብሩ የወረደው። እኛም ብንጾም እንጠቀማለን፤ ባንጾም ደግሞ በረከትን እናጣለን። ቅዱስ ዳዊት “ሥጋዬ ቅቤ በማጣት ከሳ” (መዝ. ፻፱፥፳፬)፤ ነቢዩ ዳንኤልም “ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም፤ ሥጋ እና ጠጅም በአፌ አልገባም” (ዳን. ፲፥፫) ብለው እንደ ተናገሩ በጾም ወቅት ከጥሉላት ምግቦች ሊከለከሉ ይገባል። ቅዱስ ጳውሎስ “መብል ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጐድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም” ብሎ ማስተማሩም ከመብል ተከልክለን መጾማችን ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት መንገድ መሆኑን ያመላክታል። ሮሜ. ፲፬፥፯፤ ፩ ቆሮ. ፰፥፰። የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ብንያሚ’ም “ንኩን ድልዋነ ይእዜ ኦ አኀውየ ወፍቁራንየ ለጾም ወለመልእክተ እግዚአብሔር ወለኵሉ ምግባረ ሠናይ ዘምሉእ ትሩፋተ ወፈድፋደሰ ለሃይማኖት እንተ ኢትጸንን ዘሥሉስ ቅዱስ - ወንድሞቼና ወዳጆቼ ሆይ! አሁንም ለጾም፣ እግዚአብሔርን ለማገልገል፣ ትሩፋትን ለተመላ በጎ ሥራ ሁሉ፣ ይልቁንም ጽነት ለሌለባት (በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ ብለን) ለምናምንባት ሃይማኖት የተዘጋጀን እንሁን።” ብሏል። ብንያ. ሃይ. አበ. ፹፱፡፪። ጾም ቍስለ ነፍስን የምትፈውስ፣ ኀይለ ፍትወትን የምታደክም፣ የበጎ ምግባራት ሁሉ መጀመሪያ፣ ጸጋ እግዚአብሔርን የምታሰጥ፣ ለፅሙዳን ክብራቸው፣ ለደናግል የንጽሕና ጌጣቸው፣ የጸሎት እናት፣ የዕንባ መገኛ ምንጭ፣ አርምሞን የምታስተምር፣ ለበጎ ሥራ ሁሉ የምታነቃቃ፣ ሰውነትን በእግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ትሕትናን ገንዘብ ለማድረግ የምትረዳ መድኃኒተ ነፍስ ናት። ማር ይስሐቅ አን. ፬፤ ምዕ. ፮። ጾም ለሁሉም ክርስቲያን ሕግ ሆኖ የተሰጠ የአምላክ ትእዛዝ ነውና አንድ ክርስቲያን “ጾም አልጾምም” የማለት ሃይማኖታዊ ሥልጣን የለውም። ምክንያቱም ነቢየ እግዚአብሔር ኢዩኤል “ጾምን ቀድሱ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ” በማለት መጾም፣ መጸለይ ክርስቲያናዊ ግዴታ መሆኑን ነግሮናል። ኢዩ. ፪፥፲፭።

ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃና የምስጋና መርሐ-ግብር! ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ዘጨጎዴ፤ ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ በጎጃም ጨጎዴ ሐና የሦስቱ ማለትም የዋድላ፣ የዋሸራና የጎንጅ—የቅኔ ምስክርና የትርጓሜ መጻ
ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃና የምስጋና መርሐ-ግብር! ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ዘጨጎዴ፤ ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ በጎጃም ጨጎዴ ሐና የሦስቱ ማለትም የዋድላ፣ የዋሸራና የጎንጅ—የቅኔ ምስክርና የትርጓሜ መጻሕፍት መምህር በመሆን፣ የሀገር ኩራት የሆነውን የግእዝ ቋንቋና የቅኔ ጥበብን እስከነ ዐዋጁ፣ አገባቡ፣ ግሱና ዕርባ ቅምሩ በማስፋፋት የሀገር በቀል እውቀት ማዕከል ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል። በዚሁ ታላቅ የትምህርትና የጥበብ ጉዞ ውስጥ ያፈሩትና አሻራቸውን ያሳረፉበት የሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሺፈራው “ሐመረ ቅኔ” የቅኔ እና አገባብ መጽሐፍ ምረቃ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በድምቀት ይመረቃል። በዕለቱ:- 🗞የመጽሐፍ ምረቃ እና ትንታኔ፦ በዕውቅ ተጋባዥ ምሁራን የሚቀርብ ጥልቅ የዳሰሳ ትንታኔ። 🗞የ50 ዓመታት የዕድሜ ልክ ምስጋና ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው ለግእዝ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ላበረከቱት የግማሽ ክፍለ ዘመን (50 ዓመታት) ታላቅ አበርክቶ የሚገባቸው የክብር ምስጋና ይቸራቸዋል። 🗞ደማቅ የቅኔ ማዕበል በሊቀ ሊቃውንት ያሬድ የቀድሞ ተማሪዎች (ደቀ መዛሙርት)፣ በሥጋ ልጃቸው መጋቤ አዕላፍ ቅዱስ ያሬድ (በባሕር ዳር ሰላም አርጊው የቅኔ ጉባዔ ቤት ከ6ሺህ በላይ ተማሪ ያላቸው) የሚቀርብ ልብን የሚያረሰርስ የቅኔ ድግስ። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍን ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ 3ኛ ዲግሪ (PhD) በማስተማር ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ለግእዝ ቋንቋ ዕድገትና ልማት አጠንክሮ መስራቱን ይቀጥላል። ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣ ምሁራን እንዲሁም የቅኔ ሊቃውንት በተገኙበት በዚህ ታላቅ መርሐ ግብር ይካሄዳል። 📅  ቅዳሜ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ 📍ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ዊዝደም (ጥበብ) ግቢ፣ በጥበብ አዳራሽ

"ኩኑ ገባርያነ ሕግ ለርእስክሙ፥ ወኩኑ መምህራነ ለካልኣኒክሙ = ለራሳችሁ ሕግን የምትጠብቁ ሁኑ፤ ሌሎችንም የምታስተምሩ ሁኑ!" ሃይ. አበ. ፻፳፭፡፲፮ 📌 በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ በሳል አመራር
+4
"ኩኑ ገባርያነ ሕግ ለርእስክሙ፥ ወኩኑ መምህራነ ለካልኣኒክሙ = ለራሳችሁ ሕግን የምትጠብቁ ሁኑ፤ ሌሎችንም የምታስተምሩ ሁኑ!" ሃይ. አበ. ፻፳፭፡፲፮ 📌 በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ በሳል አመራር በሚመራው በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዛሬ ሚያዝያ ፳፩/፳፻፲፰ ዓ/ም ስለ ሊቃውንት ጉባኤ አደረጃጀት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተከናውኗል። 📌 በዚህ ልዩ የሥልጠና መርሐ ግብርም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል፣ የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ #ዕንባቆም ገብረ ኪዳን፣ የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያው ክፍል ኀላፊዎች፣ የሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሓፊዎች፣ የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህራንና ሰባክያነ ወንጌል የተገኙ ሲሆን ሥልጠናው በጸሎት ተጀምሯል። 📌 በመጀመሪያው ክፍለ ትምህርትም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት ጸባቴ ቆሞስ አባ #ኀይለማርያም አረጋ "...ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ!" (፩ ጴጥ. ፪፡፩-፫) በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። 📌 በሁለተኛው ክፍለ ትምህርትም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ "የሊቃውንት ጉባኤ አመሠራረት እና አሁን ያለበት" በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊና ጥልቅ ትምህርት ሰጥተዋል። 📌 የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤም በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ መመሪያ ሰጪነት እንደ ዐዲስ ተዋቅሮ ሰባት አባላት ያሉት ሲሆን ከተዋቀረበት ጊዜ ጀምሮ አመርቂ የሆኑ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ያለ መሆኑን ማወቅ ተችሏል።

ነገረ ትንሣኤ.pdf9.18 KB

"ኢየሱስ ክርስቶስ የይሁዳ እግርን ጨምሮ የሁሉም ደቀ መዛሙርቱ እግሮችን ካጠበ በኋላ የደቀ መዛሙርቱን እግሮች ባጠበበት ውኃ የራሱን እግሮች በራሱ እጅ ዐጥቧል።" "ኦ ትሕትና ዘመጠነ ዝ ትሕትና"

ዛሬ በዓለ እግዚአብሔር ነው። ዕለቱም የሕማማት ሁለተኛ ቀን ማክሰኞ ነው። ለእግዚአብሔር የሚገባውን የአምልኮ ስግደታችሁን ስገዱ!

Repost from N/a
ሆሣዕና.pdf4.47 KB

ሆሣዕና.pdf4.47 KB

ዛሬ መጋቢት ፳፫/፳፻፲፰ ዓ/ም በመጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ የተዘረፈ ሙሉ ቤት ቅኔ👇 ፩. ግእዝ ጉባኤ ቃና • ዘሥራይ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ አሕመሞ፥ • በሌሊት መንፈስ እስመ ይትረአዮ ቀዊሞ። ፪. ዕዝል ጉባኤ ቃና • ለእመ ኒቆዲሞስ አብ ምንትኑ ለኒቆዲሞስ ሕይወቱ፥ • እንዘ ወይነ ትምህርት ይሰቲ አምስዮ እስመ በሌሊት የአቱ። ፫. ዘአምላኪየ • ከመ መሐድምት ዘይብል ውስተ ባህለ አበው አእላፍ፥ • በሞጸፍ አሓዱ ክልኤቲ አዕዋፍ፥ • ቦ አዕዋፍ ክልኤቲ በኒቆዲሞስ ሞጸፍ። ፬. ሚ በዝሑ • ለዘእምኔከ ርሕቁ ትጸልኦሙ ለምንት ወትትቃወሞሙ ለምንትኑ፥ • ኒቆዲ ልብከ ዘክፉል በበ ዘመኑ፥ • አምጣነ ይቤ መጽሐፍ ጕየይ እኍ እምነ ዘክልኤ ልሳኑ። (አረ. መን. ፍና. ፲፰) ፭. ዋይ ዜማ • ጕይ ኒቆዲሞስ እስመ ዐማኑኤል ዘንም እስመ ኒቆዲሞስ ጕንድ፥ • መጽአ ስቡረ ኵለንታ ዐማኑኤል ዑድ፥ • አመ ከርመ ወንጌል ኮነ በቀመረ እሉ አይሁድ፥ • አመ መብረቀ ጽድቅ በረቀ ምስለ ነጐድጎድ፥ • ሃይማኖት ዘጴጥሮስ ሞገድ። ፮. ሐፂር ዋይ ዜማ • ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስሀ ዐማኑኤል ዑቅ፥ • ዐማኑኤልሀ ተወከፍ ከመ ዘተገድፈ ደ። • (ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስሀ ዐማኑኤል ዑቅ።) ፯. መስኮት ዋይ ዜማ • ዐማኑኤል በመትከፍትከ ኒቆዲሞስሀ ዘወድቀ እመልዕልተ ኦሪት ምርፋቅ፥ • ሱቅ፦ ወእንከ ኄሩ ወእንከ ሊቅ፥ • ወዲቤሁ ለፀርከ ደቅ። ፰. ሥላሴ • ኒቆዲሞስ ለኢየሱስ ወለኒቆዲሞስ ኢየሱስ እንተ ኒቆዲሞስ ቀርበ ወእንተ ኢየሱስ ኢርሕቀ፥ • እመ ኮነ ወለእመ ኮነ መርድአ ወሊቀ፥ • እመንበረ ኦሪት ተትሕተ ወዲበ ርእሰ ሕግ ረፈቀ፥ • እስመ ኢጠየቀ ወጠየቀ፥ • እንተ ኢየሱስ ጠየቀ ወጽሑቀ ጽሕቀ፥ • ወዘዝክቱ ኒቆዲሞስ ዖቀ። ፱. ዘይእዜ • መራር ብእሲት ቃለ ወንጌል ዘለመደት ጸብአ ወአሠነየት ሁከተ፥ • ምስለ ኒቆዲሞስ ብእሲሃ ሌሊተ ተንሢኣ ትትበአስ ሌሊተ፥ • ወበቃለ ወንጌል ብእሲት ሰላመ ወዕረፍተ፥ • ኒቆዲሞስ ኀጥአ እስከ አመ ሞተ፥ • ቃለ ሕገ ወንጌል ብእሲቱ አምጣነ ኢኮነት ኄርተ። • (ኒቆዲሞስ ኀጥአ እስከ አመ ሞተ፥) ፲. ሣህልከ • እመኒ ኢዘንመ ውስተ ሀገር፥ • ዝናመ ምሕረት ሰላም ምሉአ በረከት ቍር፥ • ሳዐ ክረምተ ጽልእ ድሕረ ተዘርአ መጽለወ እስከ አመ የብሰ ልበ ሰብእ ማዕረር። ፲፩. ሐፂር ሣህልከ • ነዊሕ ኦም ኒቆዲሞስ፥ • ለኀበ ክልኤ ተሰብረ በትምህርተ ወንጌል ነፋስ። • (ነዊሕ ኦም ኒቆዲሞስ፥) ፲፪. መወድስ • ሱባዔ ሀብተ ጽድቅ ፀሓይ እምድሕረ ሠረቀ እስመ እመጠኑ ፈድፈደ ሐሩረ ቃለ ጽድቅ ዘበድካም፥ • እለ ውስተ ገዳም ሀለዉ ለተግባረ ኵሉ ዓለም፥ • ግብረ እደዊሆሙ ሐዲጎሙ አጽለሉ ኀበ ዘለምለመ ጾመ ወልድ ኦም፥ • ምጽላለ ሕይወት እስመ ኮኖሙ ውእቱ ኦም ዘወልደ አምላክ ጾም። • ሶበሂ ተፈጸመ ሰዓተ ቅዳሴ ግሩም፥ • ለጸናጽለ ወርቅ ወከበሮ መሀይምናኒሁ ለበለዓም፥ • በብሂለ ስብሐት ዘጸግበ ላእከ ደብረ ሲና ምቅዋም፥ • አብሖሙ እንዘ ይብል እትዉ በሰላም። ፲፫. ኵልክሙ መወድስ • ኦ ዕሙቅ ብዕለ ስብሐቲሁ ለፈጣሬ ኵሉ ፍጡር እንተ ቅድምናሁ ምስለ ተድሕሮ፥ • እመ ለፀሓይ ጴጥሮስ አመ ጎሐ ጽባሕ ገብሮ፥ • አምጣነ ለወርሕ ኒቆዲሞስ ከመ ያብርህ ሰዓተ ሌሊት በሌሊት ፈጠሮ፥ • ወሌሊተ አኰነኖ እመ በሰማያት ይቁም አስተዳለወ መንበሮ። • መኑሂ ዘየኀሥሥ ምክረ ልበ ሰብእ ይምክሮ፥ • ወመኑ ዘይፈቅድ በተጥባበ ነገር ከመ ያእምሮ፥ • ከመ ልማደ ሰብእ ኢንርሳዕ በህላዌሁ አንክሮ፥ • ለሊሁ እስመ ረሰየ ጽልመተ ምስዋሮ፥ • መኑሂ ኢይኅሥሥ ለህላዌሁ ዐሠሮ። • (ለሊሁ እስመ ረሰየ ጽልመተ ምስዋሮ፥) ፲፬. ሐፂር ኵልክሙ መወድስ • ከመ ነሥአ ዝስኰ ጸብሐ ሕገ ኦሪት ቀሊል፥ • ተሰብረ ለኀበ ክልኤቱ ኒቆዲሞስ ጻሕል። ፲፭. ሐዋርያቲሁ ከበበ • ኅብስተ ሕይወት ወልድ፥ • ዘበዕፀ መስቀል ማእድ፥ • ውሑደ ኮነ ኀበ አይሁድ እንዘ ለካልኣን ፍድፉድ። ፲፮. ሕንጼሃ • አእምሮ ዘኒቆዲሞስ ዳሕንኑ፥ • መንፈቀ ሌሊት ይጐይይ አኮኑ።

ዛሬ ማታ በዚህ https://t.me/kineyared የቅኔ ዘረፋ ይኖረናል። ሰዓት 2:30