en
Feedback
GRACE_TUBE ™✍

GRACE_TUBE ™✍

Open in Telegram

🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142

Show more
6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
ዝምታን... በራሳችን ፈልገን ካገኘነው ጥበብ ነው በሰዎች ተገደን ካገኘነው ደግሞ የቁም እስር ነው ::

ከቤቱ ሲነፃፀር በር ትንሽ ነው፤ ከበር ሲነፃፀር የቁልፍ ጋን ትንሽ ነው፤ ከቁልፉ ጋን ሲነፃፀር መክፈቻ ቁልፏ ከሁሉም ትንሽ ናት ግን ትልቁን ቤት ትከፍታለች በመሆኑም ትንሽ እና ማስተዋል የታከለበት መፍተሄ ትልቁን ችግር ሊፈታ ይችላል! @JESUSlovingly142

እንድፅፍላቹ የምትፈልጉትን ጉዳይ እንደ እርዕስ ተጠቅማቹ inbox አድርሱኝ👉🏽 @Abrelo_23

አስተዉል . . ያየኸው በሙሉ፤        የሰማኸው ሁሉ፤ የህይወት አመሉ፤       እዉነት እንዳይመስልህ፤ በዉስጣዊ አይንህ፤             በሶስተኛ ጆሮህ፤ በጥሞና አዳምጥ፤           ሳትሮጥ አታንጋጥ፤ ሳትጎርስ አታላምጥ፤             ግራና ቀኝህን፤ ግብር ኑረትህን፤                ከኋላና ከፊት፤ አጥብቀህ ተመልከት፤               ከሁሉ አትገኝ፤ የሌላን አትመኝ፤           ለመፍረድ አትቸኩል፤ በጥሞና አስተዉል፤        ይከትሃል ገደል፤ ይህንን ልብ በል!!!! @JESUSlovingly142

አመመኝ ስትለው ሰዉ አካልህን ይመስለዋል ፈለጠኝ ስትለዉ ግንባርን ቀርቦ ይነካዋል እራበኝ ስተለው ሙቅ አቅጥኖ ቤትህ ያመጣል ደከመኝ ስትለው ተኛ ብሎ አልጋ ይገልጣል እንዴት ታስረዳዋለህ ? ምግብ አይደል ያስፈለገኝ ተትረፍርፏል ሞልቷል ቤቴ አልተጎዳም  አልቆሰለም የምትነካው ሰውነቴ እንቅልፍ አይደል የቸገረኝ እስትንፋሴን የቆረጣት ሰው መውደድ ነው ያደከመኝ የገደለኝ ወዶ ማጣት ብለህ አትነግረው አያስችልህ አፍህ ሀቁን አያወጣ ፈርዶብሃል ትኖራለህ ለፍቅር ሙቅ ስትጠጣ *-----------*

ለተወሰነ ሰዐት online አለሁ ልታወሩኝ ልትጠይቁኝ የፈለጋቹ በዚህ 👇🏾 @Abrelo_23

ሰው ላይ አትፍረድ #አንዳድ ሰው ደህና ነኝ የሚለው የእውነት ደህና ስለሆነ ሳይሆን አሞኛል ቢልም ህመሙን የሚረዳለት ሰው ስለሌለው ነው \ አንዳድ ሰው ዝም የሚለው የሚያወራው ስለሌላው ሳይሆን ቢያወራው የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው *አንዳድ ሰው ብቸኝነትን የሚመርጠው ሰው ጠፍቶ ሳይሆን ለእርሱ ልክ የሚሆን እርሱ #በእርሱነቱ የሚቀበለውና የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው #አንዳድ ሰው ከ ፍቅር አለም እራሱን የሚያገለው በንፁህ ልብ ሰው አፍቅሮ በአመነው ሰው ስለተከዳ ነው     

ሰው ላይ አትፍረድ #አንዳድ ሰው ደህና ነኝ የሚለው የእውነት ደህና ስለሆነ ሳይሆን አሞኛል ቢልም ህመሙን የሚረዳለት ሰው ስለሌለው ነው \ አንዳድ ሰው ዝም የሚለው የሚያወራው ስለሌላው ሳይሆን ቢያወራው የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው *አንዳድ ሰው ብቸኝነትን የሚመርጠው ሰው ጠፍቶ ሳይሆን ለእርሱ ልክ የሚሆን እርሱ #በእርሱነቱ የሚቀበለውና የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው #አንዳድ ሰው ከ ፍቅር አለም እራሱን የሚያገለው በንፁህ ልብ ሰው አፍቅሮ በአመነው ሰው ስለተከዳ ነው      ሰናይ ቀን ተመኘውላችሁ::

ጨለማው ከብርሀኔ በላይ #አይደለም ህመሜ ከመድሀኒቴ በላይ #አይደለም #ኢየሱስ ነው ብርሀኔ #ኢየሱስ ነው መድሀኒቴ🥰 ዛሬም ኢየሱስ ይሰራል።

ትኩረት አጥቻለው ምን ላድርግ?   የምንል ከሆነ ስለዛሬ ብቻ እናስብ፣ የቀን ውሎአችንን ለማሳመር እንሞክር። ለነገ ክፋቱ ይበቃዋል አይደል የሚለው ታላቁ መፅሀፍ? ስለዚህ ነገ የት እንደምደርስ አውቃለው እንጂ ስለ ነገ በመጨነቅ ዛሬዬን አላባክንም! ዛሬን የሌለ ለነገ አይደርስም✌️ አሪፍ ቀን ተመኘሁላችሁ

ኸረ ኢየሱስ ልዩ ነው

በእግዚአብሔር የማይታለፍ ትላንት የለም።

ስንካሰስ መሸ ፡ በደል ስንቋጠር፣ እፍኝ ለምንኖር፡        ስንገነባ ኖርን ፡ መጋረጃ ጠጠር፣ መሸነፍ ሞት ሆኖ ፡ መከበር ስንሻ፣ እንደ መሰበሩ፡         ውስጣዊ ፍቅራችን                                  የት አለን ወጌሻ?!                                                  የትም!!! ይልቅ እንታረቅ፡       አይዳኝን፡               አንዳች ሰው፡                       አይውጣን ገበና፤ ከሚዘራ ወሬ ፡ ከሰሚ አንደበት                                ፍሬ የለምና።           

ቅርበት የቀነሰ ወዳጅነት መለየት ለመፍጠር ነው ዳር ዳር የሚል! ይዘህ ላታስቀር አትታገል!!!

ደርሶ ያለ ክስ  ያለ ዳኛ ያለ ፍርድ  ደርሶ እስረኛ ወታደር ሳይኖር  ደርሶ መማረክ አስገዳጅ ሳይኖር  ደርሶ መንበርከክ ዘራፊ ሳይኖር  መሰረቅ ደስታ ደርሶ መታመም  ሳይኖር በሽታ ጠበቃ ሳይኖር  ፈራጅም ዳኛ ማረሚያ ሳይገቡ  የነፍስ እስረኛ እራስን ሰጥቶ  ማንነት ማጣት ደርሶ መኮነን  ሳያጠፉ ቅጣት ቅኔው የማይገባ  ሰም እና ወርቁ የስሜት ጋጋታ   እየተፈራረቁ ከሌላ አድሮ  ፈቅዶ መታፈን ደርሶ መቃጠል  በእሳት ወላፈን

ተስፋ የማጣት መርዝ ህይወቱ ላይ ፈሶ ከላይ ግራጫ ሱፍ ከስር ከፈን ለብሶ ምንም ሰውነቱን መቃብር ባይከድን አንዳንድ ሰው አለ እየኖረ በድን! *-----------*

ዝምታ......... ካላዋቂ ወሬ፣ ከሌለበት ፍሬ፣ ጊዜን ከሚገድለው፣ እውቀት ከማይሰጠው፣ ከውሸት ጋጋታ፣ ይበልጣል ዝምታ። <><><><><><><><><> @JESUSlovingly142

የተወኝ መስዬ የዳንኩ ያገገምኩኝ ከ  ረ  ም  ኩ ኝ። ጠ  በ  ኩ  ኝ። ስመለስ ስቃኘው አልቂያለሁ ለካ ስጋዬ ሲለካ። ናፍቆት ገዘገዘኝ መራራቅ ገነዘኝ ልላወስ አልችልም ና ስልህ አትችልም። እስከየት ዝምታ ? መቼ ትመጣለህ መቼ ታቅፈኛለህ የት አገኝሃለሁ መቼ እጠግብሃለሁ እንጃ ግን አሞኛል  መቼ  ትመጣለህ? መች ታክመኛለህ ?! #ኢየሱስ

("አለማወቅ ") ============= ተጠራርተው ሰማይ አርያም የሄዱት ደጋግ ሊቃውንቱ ታውቋቸው ይሆን ወይ ሲመረምሩ አይተው ማርጀቷን ምድሪቱ  ??? ክፉ ቀን መምጣቱ  ?? እንጃ እኛ ብኩኖችን ያንከራትተናል አለማወቅ ከንቱ  ! #

#እሰይ ፡ ፡ ፡ ከመሳሳት ይልቅ ትክክል መሆንን ሰርክ ስለሚመርጥ፤ ይላል ያገሬ ሰው “ አስር ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ”። ፡ ፡ እኔ ግን እላለው... በመሳሳትክ ውስጥ የሚገኘው እክል፤ እሱ ነው ቁምነገር እሱ ነው ትክክል። ፡ ፡ አሁንም እላለው... ከትናንቱ ዛሬ በስለ እንድትጎመራ፤ “ አንድ ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ ” እሰይ ስህተት ስራ።