GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
ከቤቱ ሲነፃፀር በር ትንሽ ነው፤ ከበር ሲነፃፀር የቁልፍ ጋን ትንሽ ነው፤ ከቁልፉ ጋን ሲነፃፀር መክፈቻ ቁልፏ ከሁሉም ትንሽ ናት ግን ትልቁን ቤት ትከፍታለች በመሆኑም ትንሽ እና ማስተዋል የታከለበት መፍተሄ ትልቁን ችግር ሊፈታ ይችላል!
@JESUSlovingly142
6 749
አስተዉል
.
.
ያየኸው በሙሉ፤
የሰማኸው ሁሉ፤
የህይወት አመሉ፤
እዉነት እንዳይመስልህ፤
በዉስጣዊ አይንህ፤
በሶስተኛ ጆሮህ፤
በጥሞና አዳምጥ፤
ሳትሮጥ አታንጋጥ፤
ሳትጎርስ አታላምጥ፤
ግራና ቀኝህን፤
ግብር ኑረትህን፤
ከኋላና ከፊት፤
አጥብቀህ ተመልከት፤
ከሁሉ አትገኝ፤
የሌላን አትመኝ፤
ለመፍረድ አትቸኩል፤
በጥሞና አስተዉል፤
ይከትሃል ገደል፤
ይህንን ልብ በል!!!!
@JESUSlovingly142
6 749
አመመኝ ስትለው
ሰዉ አካልህን ይመስለዋል
ፈለጠኝ ስትለዉ
ግንባርን ቀርቦ ይነካዋል
እራበኝ ስተለው
ሙቅ አቅጥኖ ቤትህ ያመጣል
ደከመኝ ስትለው
ተኛ ብሎ አልጋ ይገልጣል
እንዴት ታስረዳዋለህ ?
ምግብ አይደል ያስፈለገኝ
ተትረፍርፏል ሞልቷል ቤቴ
አልተጎዳም አልቆሰለም
የምትነካው ሰውነቴ
እንቅልፍ አይደል የቸገረኝ
እስትንፋሴን የቆረጣት
ሰው መውደድ ነው ያደከመኝ
የገደለኝ ወዶ ማጣት
ብለህ አትነግረው አያስችልህ
አፍህ ሀቁን አያወጣ
ፈርዶብሃል ትኖራለህ
ለፍቅር ሙቅ ስትጠጣ
*-----------*
6 749
ሰው ላይ አትፍረድ
#አንዳድ ሰው ደህና ነኝ የሚለው የእውነት ደህና ስለሆነ ሳይሆን አሞኛል ቢልም ህመሙን የሚረዳለት ሰው ስለሌለው ነው
\ አንዳድ ሰው ዝም የሚለው የሚያወራው ስለሌላው ሳይሆን ቢያወራው የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው
*አንዳድ ሰው ብቸኝነትን የሚመርጠው ሰው ጠፍቶ ሳይሆን ለእርሱ ልክ የሚሆን እርሱ #በእርሱነቱ የሚቀበለውና የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው
#አንዳድ ሰው ከ ፍቅር አለም እራሱን የሚያገለው በንፁህ ልብ ሰው አፍቅሮ በአመነው ሰው ስለተከዳ ነው
6 749
ሰው ላይ አትፍረድ
#አንዳድ ሰው ደህና ነኝ የሚለው የእውነት ደህና ስለሆነ ሳይሆን አሞኛል ቢልም ህመሙን የሚረዳለት ሰው ስለሌለው ነው
\ አንዳድ ሰው ዝም የሚለው የሚያወራው ስለሌላው ሳይሆን ቢያወራው የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው
*አንዳድ ሰው ብቸኝነትን የሚመርጠው ሰው ጠፍቶ ሳይሆን ለእርሱ ልክ የሚሆን እርሱ #በእርሱነቱ የሚቀበለውና የሚረዳው ሰው ስላጣ ነው
#አንዳድ ሰው ከ ፍቅር አለም እራሱን የሚያገለው በንፁህ ልብ ሰው አፍቅሮ በአመነው ሰው ስለተከዳ ነው
ሰናይ ቀን ተመኘውላችሁ::
6 749
ጨለማው ከብርሀኔ በላይ #አይደለም
ህመሜ ከመድሀኒቴ በላይ #አይደለም
#ኢየሱስ ነው ብርሀኔ
#ኢየሱስ ነው መድሀኒቴ🥰
ዛሬም ኢየሱስ ይሰራል።
6 749
ትኩረት አጥቻለው ምን ላድርግ? የምንል ከሆነ ስለዛሬ ብቻ እናስብ፣ የቀን ውሎአችንን ለማሳመር እንሞክር። ለነገ ክፋቱ ይበቃዋል አይደል የሚለው ታላቁ መፅሀፍ?
ስለዚህ ነገ የት እንደምደርስ አውቃለው እንጂ ስለ ነገ በመጨነቅ ዛሬዬን አላባክንም! ዛሬን የሌለ ለነገ አይደርስም✌️
አሪፍ ቀን ተመኘሁላችሁ
6 749
ስንካሰስ መሸ ፡ በደል ስንቋጠር፣
እፍኝ ለምንኖር፡
ስንገነባ ኖርን ፡ መጋረጃ ጠጠር፣
መሸነፍ ሞት ሆኖ ፡ መከበር ስንሻ፣
እንደ መሰበሩ፡
ውስጣዊ ፍቅራችን
የት አለን ወጌሻ?!
የትም!!!
ይልቅ እንታረቅ፡
አይዳኝን፡
አንዳች ሰው፡
አይውጣን ገበና፤
ከሚዘራ ወሬ ፡ ከሰሚ አንደበት
ፍሬ የለምና።
6 749
ደርሶ
ያለ ክስ ያለ ዳኛ
ያለ ፍርድ ደርሶ እስረኛ
ወታደር ሳይኖር ደርሶ መማረክ
አስገዳጅ ሳይኖር ደርሶ መንበርከክ
ዘራፊ ሳይኖር መሰረቅ ደስታ
ደርሶ መታመም ሳይኖር በሽታ
ጠበቃ ሳይኖር ፈራጅም ዳኛ
ማረሚያ ሳይገቡ የነፍስ እስረኛ
እራስን ሰጥቶ ማንነት ማጣት
ደርሶ መኮነን ሳያጠፉ ቅጣት
ቅኔው የማይገባ ሰም እና ወርቁ
የስሜት ጋጋታ እየተፈራረቁ
ከሌላ አድሮ ፈቅዶ መታፈን
ደርሶ መቃጠል በእሳት ወላፈን
6 749
ተስፋ የማጣት መርዝ
ህይወቱ ላይ ፈሶ
ከላይ ግራጫ ሱፍ
ከስር ከፈን ለብሶ
ምንም ሰውነቱን
መቃብር ባይከድን
አንዳንድ ሰው አለ
እየኖረ በድን!
*-----------*
6 749
ዝምታ.........
ካላዋቂ ወሬ፣
ከሌለበት ፍሬ፣
ጊዜን ከሚገድለው፣
እውቀት ከማይሰጠው፣
ከውሸት ጋጋታ፣
ይበልጣል ዝምታ።
<><><><><><><><><>
@JESUSlovingly142
6 749
የተወኝ መስዬ
የዳንኩ ያገገምኩኝ
ከ ረ ም ኩ ኝ።
ጠ በ ኩ ኝ።
ስመለስ ስቃኘው
አልቂያለሁ ለካ
ስጋዬ ሲለካ።
ናፍቆት ገዘገዘኝ
መራራቅ ገነዘኝ
ልላወስ አልችልም
ና ስልህ አትችልም።
እስከየት ዝምታ ?
መቼ ትመጣለህ
መቼ ታቅፈኛለህ
የት አገኝሃለሁ
መቼ እጠግብሃለሁ
እንጃ ግን አሞኛል
መቼ ትመጣለህ?
መች ታክመኛለህ ?!
#ኢየሱስ
6 749
("አለማወቅ ")
=============
ተጠራርተው ሰማይ
አርያም የሄዱት ደጋግ ሊቃውንቱ
ታውቋቸው ይሆን ወይ
ሲመረምሩ አይተው
ማርጀቷን ምድሪቱ ???
ክፉ ቀን መምጣቱ ??
እንጃ
እኛ ብኩኖችን ያንከራትተናል
አለማወቅ ከንቱ !
#
6 749
#እሰይ
፡
፡
፡
ከመሳሳት ይልቅ ትክክል መሆንን ሰርክ ስለሚመርጥ፤
ይላል ያገሬ ሰው “ አስር ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ”።
፡
፡
እኔ ግን እላለው...
በመሳሳትክ ውስጥ የሚገኘው እክል፤
እሱ ነው ቁምነገር እሱ ነው ትክክል።
፡
፡
አሁንም እላለው...
ከትናንቱ ዛሬ በስለ እንድትጎመራ፤
“ አንድ ግዜ ለካ አንድ ግዜ ቁረጥ ” እሰይ ስህተት ስራ።
