GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
ጊዜን ሸጥኩት ለብር ፥ጊዜም ሸጠኝ ለሞት፣
ሞት ሸጠኝ ለእግዜር ፥እግዜር ሸጠኝ ለእውነት፣
ፅድቅ ገዛ እንጂ ፥መሸጥ አያውቅ እምነት፣
@JESUSlovingly142
6 749
መልከ ቀና አድርገኝ
ህይወቴ ቢቀለኝ.. .
አውለኝ በክብር
ቀባኝ ሞገስ ቅባት
ቀኖቼ ላይ ልንገስ
በሌሎች ፍርሀት።
ስጠኝ የመሪ ድምፅ
አጥር የሚሻገር...
መንገዴ እንዲሳለጥ
እንዲሆን ገር በገር ።
አልያ አልገፋትም...
ይህችን ስንኩል ዕድሜ
ለአይን አስቀይሜ፥
ቀልዬ ያለ ሞገስ...
ሰው ሰሚ ሲያጣ ነው
ከሞት ደጅ የሚደርስ !!
6 749
#🥰
፡
፡
፡
ተናፍቀሻል እቴሜቴ፤
ከናፍቆትሽ ማገገሚያ መድሀኒቱ ይኖር ቤቴ?
እንጃ ብቻ!
አልድን ነገር እንደዘበት ናፍቆት ልቤን ሰነበጠው፤
መድሀኒቱ እቤት ካለ በቀን ስንቴ ነው ሚዋጠው?
ንገሪኝ!
6 749
#ይነበብ አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል 😊ገበሬው በአቅራቢያው ካለ ጃምቦ ቤት ውስጥ በቀን አረቄ በጃንቦ ይጨልጣል። አንድ ሌላ የሚያውቀው ሰው ይመጣና "በዚህ የእርሻ ሰዓት መጠጥ ቤት ምን ታደርጋለህ?" ብሎ ይጠይቀዋል። ገበሬው ጭንቅላቱን እያወዛወዘ
"አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል።" ይለዋል።ሰውዬው ግራ በመጋባት ወንበር ስቦ ተቀመጠና "ግዴለም ምን ሆነህ ነው ንገረኝ ሲያወሩትኮ ይቀላል" አለው። "እሺ ካልክ ...!" ብሎ ገበሬው መናገር ጀመረ፣ "እሄውልህ ዛሬ ጠዋት ተነስቼ ግብርና በብድር የሰጠንን ነጯን ላም እያለብኩነበር። አንድ እቃ እንደሞላሁ ግራ እግሯን አንስታ የታለበውን በሙሉ ደፋችው" "እሺ ግን ይሄ እኮ ታድያ ብዙ አያስከፋም ለዚህ ሁኔታም አይዳርግህም " አለ ሰውየው
"አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል።" ብሎ ገበሬው አሁንም ይተክዛል ...ጭማሪ አረቄም ያዛል።"እሺ ከዛስ ምን ሆነ" ብሎ ሰውየው አለሳልሶ ጠየቀው ገበሬው አረቄውን ጭልጥ እያደረገ ንግግሩን ቀጠለ፣ " ከዛ ያው ግራ እግሯን ከአንዱ ቋሚ ጋር አሰርኩት" "ከዛስ....?" "ከዛማ ድጋሚ ተቀምጬ ማለብ ጀመርኩ....በሌላ እቃ ሞልቼ እንደጨረስኩ ቀኝ እግሯን አንስታ ድጋሚ የሞላሁትን እቃ ደፋችው" ሰውዬው ከት ብሎ ስቆ "እንዴ ድጋሚ?" ይለዋል
ገበሬው አሁንም፣ "አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል" አለ።"ከዛስ ምን አረክ?" ሰውዬው በጉጉት ይጠይቃል። "ያው ከዛ በጣም ተማርሬ ቀኝ እግሯንም ከሌላ ቋሚ ጋር አስሬ ማለብ ጀመርኩ...የሚያሳዝነው ይቺ የተረገመች ላም ይሄኛውንም በጥንቃቄ እንደጨረስኩ በጭራዋ ደፋችው" "ያሳዝናል በእውነቱ " አለ ሰውዬው ጭንቅላቱን እየነቀነቀ።
"አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል" አለ አሁንም ገበሬው እየተናደደ"ከዛስ?" አለው ሰውዬው የገበሬው ችግር መጨረሻው እያጓጓው "ከዛማ ሌላ ገመድ ፈልጌ ስላጣሁ ቀበቶዬን ፈትቼ ጭራዋን አስሬ እንደጨረስኩ ሱርዬ ወለቀ፣ በዚች ቅጽበት ሚስቴም ወደ ውስጥ እየገባች ነበር" 🙈
"አንዳንድ ነገሮችን ማብራራት ይከብዳል።"✍️🙄🙄🙄🙄 @JESUSlovingly142
6 749
ራስን መቆጣጠር ላይ እንዴት ነህ አለኝ?
መልሴ፦በሚፈጥን ታክሲ ውስጥ ሆኜ ሳለ ከርቭ በሆነ መንገድ ላይ ፡ ሰው ላይ ሳልለጠፍ እሔዳለው አልኩት!!!
6 749
ከትላንት የተሻለች ዛሬን ኑሩ!ወደፊት የህይወታቹ ታሪክ ሲጻፍ በዛሬዋ ቀን ምን አድርጋቹ ተብሎ ይጻፍ ይሆን? የራሳቹ ምርጥ ሁኑ!
@JESUSlovingly142
6 749
ሰው ካለ ምዕራፍ አይኖርም ምን አልባት መኖሩን አልተረዳውም እንጂ እየኖረበት ነው የለም ባለ ጊዜ!!!
ብዙ ጊዜ አንዱ ምዕራፍ ሲዘጋ ሌላኛው ይቀጥላል የተለያየ ታሪክም፡ ሊሆን ይችላል።
6 749
እኔ ብቻ ነኝ ግን ?
.
.
የልቤን ኡኡታ፣
ለራሴ 'ምነግር፣
በዉስጤ ጫጫታ፣
ሠርክ የምደናገር፣
ስብርብር ቆፈኔን፣
በእንባዬ የማሞቅ፣
ጭምቅምቅ ሀዘኔን፣
ከሰዉ የምደብቅ፣
ተስፋዬ ጨልሞ፣
ፅልመት የሚታየኝ፣
ነፍስያዬ ታሞ፣
መድሀኒት ያጣሁኝ
@JESUSlovingly142
6 749
#ሁለት_እውነት
:
:
ስሜት እንዲ ነው ሲል ስሌት ሌላ እያለ
ደርሰው ካልተስማሙ፤
በራሳቸው ቅኝት እዚህ ና እዛ ቆመው
ለየቅል ካዜሙ፤
ልብ እና አዕምሮ ሁለት እውነት ይዘው
የተገኙ እንደሆን፤
ያን ግዜ ነው በቃ ከራስ ጋር መጣላት
ሆነው አለመሆን።
6 749
🔸🔸🔸🔸እስከመቼ🔹🔹🔹🔹
አንዱ መርጦ...እንዲበላ..የስንቱ አንጀት..
....ሲታጠፍ
ወንበር ማሞቅ..ለናፈቀው..ህይወት ሁሌ
....እሚረግፍ
ቦታ ሰፍቶት...እንዲቀመጥ..ሌላው ቤቱን
....እየለቀቀ
የደላቸው እየተባሉ.......ምስኪን ደሀ.....
....ብዙ አለቀ
ቀጣይ ትውልድ...የሚመርዝ......
....ሀገር አፍራሽ...ሀሳብ በዝቶ
እስከመቼ ይቀጥላል...የሰው ህይወት
.....ክብር አቶ
<><><><><><><><><><><><
6 749
#የታል?
፡
፡
፡
ፈጣሪ ጥበቡን ሊያሳይ ውብ አርጎ ስለፈጠራት፤
መሬት አይንካኝ እያለች ይመሻል ቀኑ እያጠራት።
ኩራት ልቧን ወድሯት ምድር አንሷት ይመስል፤
አግዝፋው የራሷን ምስል፤
በመልኳ ስትጓደደው ያዙኝ ልቀቁኝ እያለች፤
ካንጀቴ ታስቀኛለች።
፡
፡
የፈጣሪ እደ ጥበብ የውበት ዳር የታየበት፤
ፍፁም ገላ ፍፁም ውበት፤
እግዜር ሰጥቷት ተላብሳለች፤
በራሷ አይል እሷ ለሷ አንዳች ቅጥል ምን አርጋለች?
፡
፡
ዓይኗን ሰራች?
ጥርሷን ሰራች?
ወይ ከንፈሯን?
ደም ግባቷን?
ወይስ መላ ሰውነቷን?
የፈጠራት በጥበቡ ቸሯት እንጂ ውብ ቁንጅና፤
ለማማሯ ለውበቷ ተጫውታለች አንዳች ሚና?
፡
፡
ካካላቷ ለሚታየው ለሰፈረው ውብ ታንጽኦ፤
የቱኛው ነው የሷ ድርሻ ያኖረችው አስተዋጽኦ?
ምንም የለም ካለም የታል?
ባልፈጠረው ሰው ሲጎበር ጭንቅላቱን ያስገምታል።
ንገሯት!
6 749
🪜🪜የመሰላል ጉዞ🪜🪜
ከፍታን በመሻት~መሰላል ተጠቅመው
ወደጫፍ ሲወጡ
ልማድ ሆኖ ቀርቷል~የላዩን ጨብጦ
የታቹን መርገጡ::
<><><><><><><><><><><><><><><
6 749
ስቄ ሸኝሀለው
ስቄ ሸኝሀለው መሄዱን ከመረጥክ
ለምኜ አላቆይህ ልብህ መንገድ ካለክ
ከእኔ ርቆ መሄድ ካልረበሸህ አንተን
ከእኔ መለየቱ ካስደሰተህ አንተን
ስቄ ሸኝሀለው
ግን ደሞ
ከዕለታት አንድ ቀን መመለስ ቢያሻህ
ከእኔ ያለህ ናፋቆህ መመለስ ቢያምርህ
ስቄ አልቀበልህም እንደሸኘውህ::
@JESUSlovingly142
6 749
(የፈሪ ዛቻ .. )
=========
ሲኖ'ር ነውና
ንዴትም በቀል ትርጉም የሚሰጥ
ሰው ሲበድልህ
አንገቱን ትተህ ወሽመጥ ነው መቁረጥ !
በህይወት ነውና
እየጣፈጠ.. ጠቡም ሚታለፍ
ሰው ቢያስመርርህ
ቆዳውን ትተህ ቆሌ ነው መግፈፍ !
ዛሬ አያምርና ....
ጥሎ መጀገን ገሎ መፎከር
ሰው ቢያስቀይምህ
እግር እግሩን ትተህ
ቅስሙን ነው መስበር !😁
