GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
//////በይ አልቅሽ\\\\\\\
-------------------------------------
እውነት ተወልደን ነው?
ልጆችሽ አንመስልም፤
ከጥንቱ ታሪክም አንመሳሰልም፤
አይገርምም፤
ይገርማል? ይገርማል አልሽ?
አንቺም።
እኔ ምለው ጦብያ
የኔ ውድ ኢትዮጵያ፤
የያኔው ትውልድሽ
ያንቺ መታወቂያ።
ለማን አስረከበሽ
ከማን እጅስ ወደቅሽ፤
አልፀለይሽም ነበር
ፈጣሪ እንዳይጥልሽ።
ምን አልባት ፀልየሽ
ድንገት አልሰማሽም፤
ግን፤ ይኼ አያሳምንም።
ለምን? ለምን አልሽኝ?
ፀሎት እንደማይንቅ
አምላክ ይታወቃል፤
ባይሆን ካንቺ እንዳይሆን
ወይስ እጅሽ ታጥፏል፤
ወደአምላክ ምሰጂው
እጅሽ ከየት ደርሷል፤
ተይው አትንገሪኝ
ለካ በኛው ታስሯል፤
ግን፤ እንባሽን አሳዪው
ቶሎ ላንቺ ይራራል።
ለራሄል እንባ ሲል
አምላክ ዝም አላለም፤
እንባዋ ተሰምቶ
ዳነ እስራኤልም፤
እድሜን አስጨመረ
ለንጉስ ህዝቅኤልም፤
ስለዚህ ሀገሬ በይ አልቅሺ አቺም፤
ከአምላክ ባይደርስ እንኳን
እኛ እኛን ይጥረገን፤
ሰላም ሆንሽ ሲባል
ጠብ አላልቅ ያለንን።
በይ አልቅሽ!!😭
6 749
ንገሩት ❗️❗️❗️
አይምሮን ህሊናን ሽጦ ለጠጣጠበት
ምንም የማይመስለው ጭካኔ ያለበት
በጉልበት በጡንቻ የሰለጠነበት
ስሜቱን ለማርካት እንዲህ ያለ ሀጥያት
እሱስ......ለስጋው ነው ለስሜት አቀበት
ያለማየት ጉድለት የህሊና መሞት
ለፈፀመው በደል ህይወት ሲጠፍበት
ምን አለበት ፈትህ ለሷ ቢባልበት
አይ....💔
በ አቅም ተመክቶ ያችን ትንሽዬ
የሰውነቷም ድምጿም ሆኖ ቀጭንዬ
ምንም በማታውቀው በዝምታ ልሳን
አፋኖ ሲወስዳት ጠብቆ መንገድ ላይ
ጨርሶ ፈጽሞ አጎሳቅሎ ጣላት
ያቺን ትንሽዬ መኖርን ነፈጋት
ፍትህ ፍትህ ፍትህ ፍትህ ለሚገባት❗️❗️❗️❗️
#ፍትህ ለሔቨን❗️
6 749
የተወሰኑ እህቶች እያወሩኝ ነው ሌሎቻቹም ባለጉዳይ ከሆናቹ ያለምንም መሸማቀቅ ያለ ምንም ፍርሀት ሀሳባቹን መግለፅ ትችላላችሁ በገሀዱ አለም በብዙኦች ውስጥ ያለ ነገር ነው ግን በአንዳንድ ምክንያት ብዙኦች የህክምና ክትትሉን እና መድሀኒት የሚያዛቡ በዝተዋል እየተጎዱ ነው ኤኔም እንደጉዳያቹ ያለኝን መረዳት አወራቹሀለሁ ልክ እንደዲያሪያቹ ቆጥራቹኝ በግልፅ አውሩ በድጋሚ @abrish_t3
6 749
ዛሬ አንድ ለየት ያለ ነገር እናድርገው በጤና ጉዳይ እናወራለን በተለይ በሰዎች ዘንድ ጥያቄ የሚፈጥር ለምሳሌ hiv ይህ ነገር በደማቹ የሚገኝ እህት ወንድሞች ስለዚህ ገዳይ መረዳት ፈልጌ ብዙ ጠየኩኝ ብዙ አወኩኝ ይሄን ነገር ከሳይኮ ሶሻል ጋር አድርገነው እንዴት ማኔጅ እንደሚደረግ እናውራለን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ያላቹ ሰዎች በቁምነገር ቆጥራቹ እናወራበታለን ይኸው @abrish_t3
6 749
(በእርሳስ..)
==========
በስተመጨረሻ
ሲጻፍ የያዘውን
አልለቅም እያለ ት'ግል እንዳያፋፍም
ሰው ልቤ ሲገባ...
በእርሳስ ካልሆን በቀር
በቀለም አልጽፍም !
#abrilo
@JESUSlovingly142
6 749
አንዳንዴ በህይወት መንገድ ውስጥ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ትገባለህ የዛኔ ስንዴው ከንክርዳድ እንደሚለይ ስላንተ ግድ ማን እንደሚሰጠው ማን እንደሚጨነቅልህ ማን የአፉን ቃል እንደሚጠብቅ ማን የምር እንደሚወድህ ትለያለህ አንተም ለማን ዋጋ ስትከፍል እንደነበር ማን ይገባዋል እሱን ትለያለህ የዛኔ ለማን ምን መሆን እንዳለብክ ለማን ልክ መሆን እንዳለብክ ትገነዘባለህ
በህይወት መንገድ ይሄን ትማራለህ ህይወታቸው ሲበላ የዛኔ ያደረክላቸው የሆንክላቸው እያንዳንዱ ነገር ይረዱታል ግን በመጨረሻም አንተን መተካት ያቅታቸዋል ይረፍድባቸዋል በሌላ በኩል ህሊናቸው እለት እለት ይወቅሳቸዋል ህሊና ደግሞ ፍትህ አያውቅም አንተ ሰው በዘመኑ መለወጥ አልተለወጥክም ስለሰው ታስባለህ እንደራስህ ትጨነቅላቸዋለህ ያንን እነዛ ሰዎች አይረዱትም እሚገባቸው ሲረፍድ ነው አንተ ግን ልብህን ጠብቅ ብድራትህ ከሰማይ ነው የገባኝ ነገር ለሰዎች በተገኘህላቸው ልክ አይገኙልህም ያሰብክላቸውን ያክል አያስቡልህም የተጨነክላቸው ያህልም አይጨነቁልህም ህይወት ሚዛናዊ መሆኑዋ ቀርቶዋል ሰው ስለራሱ ብቻ መጨነቅን መርጦዋል ሰውኛ ባህሪም ጠፍቶዋል በራስ ወዳድነት ሰው የሰው ልብ በማሳዘን ተጠምዶዋል አንተ ልባቸውን ስለመጠበቅ ስታስብ እነሱ አንተን ለማሳዘን ሁለቴ አያስቡም ይሄንን ተረዳ እንደኔ አይነት ሰው ከሆንክ ንቃና እራስህን ደና አድርግ ዋጋ የምትከፍልልላቸው ሰዎችን ለይ
ለማን ምንና እንዴት እስኬት መሆን እንዳለብክ ለይ።
6 749
አንዳንዴ በህይወት መንገድ ውስጥ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ትገባለህ የዛኔ ስንዴው ከንክርዳድ እንደሚለይ ስላንተ ግድ ማን እንደሚሰጠው ማን እንደሚጨነቅልህ ማን የአፉን ቃል እንደሚጠብቅ ማን የምር እንደሚወድህ ትለያለህ አንተም ለማን ዋጋ ስትከፍል እንደነበር ማን ይገባዋል እሱን ትለያለህ የዛኔ ለማን ምን መሆን እንዳለብክ ለማን ልክ መሆን እንዳለብክ ትገነዘባለህ በህይወት መንገድ ይሄን ትማራለህ ህይወታቸው ሲበላ የዛኔ ያደረክላቸው የሆንክላቸው እያንዳንዱ ነገር ይረዱታል ግን በመጨረሻም አንተን መተካት ያቅታቸዋል ይረፍድባቸዋል በሌላ በኩል ህሊናቸው እለት እለት ይወቅሳቸዋል ህሊና ደግሞ ፍትህ አያውቅም አንተ ሰው በዘመኑ መለወጥ አልተለወጥክም ስለሰው ታስባለህ እንደራስህ ትጨነቅላቸዋለህ ያንን እነዛ ሰዎች አይረዱትም እሚገባቸው ሲረፍድ ነው አንተ ግን ልብህን ጠብቅ ብድራትህ ከሰማይ ነው የገባኝ ነገር ለሰዎች በተገኘህላቸው ልክ አይገኙልህም ያሰብክላቸውን ያክል አያስቡልህም የተጨነክላቸው ያህልም አይጨነቁልህም ህይወት ሚዛናዊ መሆኑዋ ቀርቶዋል ሰው ስለራሱ ብቻ መጨነቅን መርጦዋል ሰውኛ ባህሪም ጠፍቶዋል በክፋት ሰው የሰው ልብ በማሳዘን ተጠምዶዋል አንተ ልባቸውን ስለመጠበቅ ስታስብ እነሱ አንተን ለማሳዘን ሁለቴ አያስቡም ይሄንን ተረዳ እንደኔ አይነት ሰው ከሆንክ ንቃና እራስህን ደና አድርግ ዋጋ የምትከፍልልላቸው ሰዎችን ለይ
ለማን ምንና እንዴት እስኬት መሆን እንዳለብክ ለይ።
6 749
እነዛ ተስፋዎች ደረጃ ነበሩ ፤ እነዛ ተስፋዎች በባህር ላይ እንደመራመድም ነበሩ። ያንን ተስፋ ያሳዩን ቀሙን፤ አሁን ባህር ውስጥ እየሰመጥን እጃችንን የሚይዝ እጅ ጓጉተን እንደ መጠበቅ እንደዛ ነው እየኖርን ያለነው…!!!
6 749
የራቁህን ሰዎች ወደ ራስህ ለመመለስ ፤ ለማስቆጨት ስትል በየ አደባባዩ ራስህን አትግለጥ ያን ካደረክ ለሽያጭ ከወጣ ሸቀጥ በምን ትለያለህ?!
6 749
😜🤣
ለጨዋታ
----------
ሰሞንኛ
የማራቶን አሰልጣኝነት ቀላል የሚመስላችሁ ሰዎች ግን ክፉኛ ተሳስታችሁዋል!
የማራቶን አሰልጣኝ ከሆንክ ሲነጋጋ ትነሳለህ፤ አትሌቶች እንጦጦ መግቢያው ላይ ተከማችተው ይጠብቁሀል፤ ከዛ ታጣፊ ክላሽ ታወጣና ወደ ላይ ተኩሰህ ታስጀምራቸዋለህ ፤ እነሱ መሮጥ ሲጀምሩ ቀለል ባለች ፎርድ ትራክ መኪና ቀስ እያልህ ትከተላቸዋለህ፤ እንደመዘግየት ሲሉ በ”ክላክስ” እያስደነበርህ ታሯሩጣቸዋለህ፤ ዳገቱ ላይ ስትደርስ፥ የፌሮ ከዘራህን መዘዝ አድርገህ በጋቢና መስኮት በኩል ታሾልክና ከሁዋላ የቀረውን አትሌት ትዠልጠዋለህ ፥ የተኮማተረ ትከሻውን እያሻሸ ዞር ሲል “ ገና መሮጥ ከጀመርክ እኮ አንድ ሰአት አልሞላም፤ ምናባህ እግርህን እንደ ተሳቢ መኪና ትጎትታለህ፤ ከዚህ በላይ ከዘገየህ የጫንኩትን ጀርመን ሼፓርድ ውሻ ነው ፈትቼ የምለቅብህ፤ ” ብለህ ታስቦካዋለህ፤
እና በዚህ መንገድ የሰለጠነ አትሌት እንኳን ሪከርድ የጎረቤት አገር ድንበር አይሰብርም?
ለማንኛውም ሽልማት አይናቅም፤ ባይሆን ወደ ዶላር ተርጉሙና አስቀምጡልኝ ማለት ይቻላል፤ አበበ ቢቂላ በቸርኬ ነድቶ( በባዶ እግሩ ሮጦ) የግልገል ፈረስ ጉልበት ያላት ቮልስዋገን፥ ካጼ ሀይለስላሴ ሲሸለም እንኳ አልደበረውም ፤ “ ጃንሆይ ለኔ ቮልስ እንደሸለሙኝ የእርስዎም መጨረሻዎ በቮልስ ይሁን “ ብሎ አልተራገመም🙂
እደግመዋለሁ ሽልማት አይናቅም! እኔ ይሄን ዘመን ያህል በስነጽሁፍ ለናት አገሬ ተሩዋሩጫለሁ፤ በየመድረኩ እየተጋበዝኩ፤ የቀበሌ የባህር መዝገብ የሚያክል ሰርተፍኬት ከመሰብሰብ ውጭ ምን አገኘሁ? ኮለኔል መንግስቱ እንዳሉት “Nothing”
ይልቅ ታምራት ቶላ ሰባት ሚሊዮን ብር በመሸለሙ ደስ ብሎኛል! ታሜ በቅርቡ የራስህን የኮሪደር መሮጫ እንደምትገነባ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ !
©
6 749
አንዳንዴ ራስን በጣም የተሻለ አድርጎ ማሰብ ሌላውን የበታች እንደማድረግ ነው እናም ኋላ ለይ ልብህ እንዳይሰበርና እንዳትፀፀት ይህን እይታ ማስተካከል ይገባህል! ዝቅ ያደረከው ሰው ቀን የሆነ'ለት ለታ በልጦህ ዝቅታህን ያሳየኻል!!!
6 749
#እኔ፦አምሮብሻል😊
#እሷ፦አዎ ለህይወቴ ይሄኛው ይሻለኛል 😊
#እኔ፦ኸረ ደስ ብሎኛል ስላማረብሽ ምንድነው ሚስጥሩ ምን ተገኘ ባክሽ?
እሷ፦እንደድሮው የለም ፍቅሬን የሚረብሽ ካንተ እንደተያየሁ መልካም ሰው ልቤን አየው።አሁን ደስተኛ ነኝ የማፈቅረው አለኝ የሚያፈቅረኝ🥰
ተመስገን🙏
አንተስ ከኔ በኋላ......
እኔ?????
ምን የመለስኩላት ይመስላቹሀል
ግምታችሁንም አድሮሱኝ የተሰማችሁን ካላገኛቹት መልሴን እነግራችኋለሁ👇
inbox @Abrelo_23
6 749
ብዙ ማላውቀዉ ነገሮች አሉ ገና መኖር አልጨረስኩም ብዙ ፈተና ብዙ ሳቅ ይኖራል በዚህ ሁሉ ጊዜ መውደቅ መነሳት አለ ብዙ የተውኩት የለቀኩት ሰዎችም ነገሮች አሉኝ ግን እንደ መተው የመሰለ ደና ሊያደርግ የቻለ ነገር የለም ምንም እንኳን መጋፈጡ ቢከብድም ብዙ ጊዜ ብጎዳ ብታመም እኔ ለሰዎች በማስበው ሀሳብ እና በተገኘሁላቸው ልክ ሲሆን ለማንም ገደብ የለኝም ምንም ሳደርግም ነው የኖርኩት ግን ምላሹ በጣም መጥፎ ነው የሰውን ልብ ጥሩ አድርጎ ማሸነፍ ከባድ የሆነበት ጊዜ ላይ ነን
ማንም ስለማንም ግን የማይልበት ጊዜ በዚ ሁሉ ውስጥ ለሰዎች እንደመገኘት የበዛ ህመም የለም መልካም ማድረግ መጥፎ ሆኖ አይደለም ግን አንዳንዴ ለራስም የሚያስፈል ነገሮች አሉ ያንን ሰዎች አይረዱት መጠቀምን እንጂ መጥቀምን አያስቡም
አንዳንዱ በተስፋ እና በቃል እድሜ ልክ የማይረሳ መጥፎ ጠባሳ ጥለው ያልፋሉ አንዳንዱ እራስን በሰጠኸው ልክ ያወርድሀል ለአንዳንዱ ብዙ ስትሆን ከጥቅማቸው ቡሀላ የሆንክላቸውን ይረሳሉ ወረተኞች ይሆናሉ ብቻ ብዙ ግን በዚህ ሁሉ መሀል እግዚአብሔር መልካም ነው💔
@Abrelo_23
