GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
#ችርስ
እውነት ስንናገር ለሚገለምጡን
የታባቱ ብለው አውተው ለሚጥሉን
.....................ችርስ..................
በየስራ ጣቢያው ዘመድ ላሰማሩት
እድሜ ለቀበሌ ትግስት ላስተማሩት
.....................ችርስ..................
ለፖለቲካ ቅስቀሳ ማልደው ለሚያነቁን
በሀገረ እረፍት እንቅልፍ ለሚያሳጡን
...................ችርስ..................
ወደድናቹ ስንል ሚገፉን ቀልባችን
ቅናት ላስተማሩን ለሴት ልጆቻችን
...................ችርስ..................
ራሱን ሳይዳኘው እኛን ለሚዳኘን
በተሳሳተ ፍርድ ዘብጥያ ለጣለን
.....................ችርስ.................
@JESUSlovingly142
6 749
መጠበቅ
መጠበቅ መጠበቅ አሁንም መጠበቅ
አይታክትም እንዴ በባዶ ተስፋላይ በሀሳብ
መማቀቅ
ከማይበጅ ስዎች ፋይዳ ከሌላቸው ሄዶውን
መጣበቅ
ልብን ሚያህል ነገር አሳልፎ መስጠት
እዲዘብቱበት እረግጠው አንዲያልፉት
አሳዘኑኝ ብለህ ሌላ ላይ ስትጣድ
እሳቱን ቅስቁሶ ይጠብቃል ሊያነድ
አንተ አትማርም አንደ ሎተሪ እጣ ሰዎች ትገዛለ
ምን ያደርጋል ግና ሚበጅ አይወጣልህ
እራስህን ግዛው ከማንም አጠብቅ
ለራስህ ሚሰጥህ ከራስ በላይ ወዳጅ አታገኝም
እወቅ
@JESUSlovingly142
6 749
ለውድ ምቀኞቼ😁
ቅንጣት ስህተቴን ጓግቶ ለሚጠብቅ
ውድቀቴን ለሚሻ
ከአኗኗሬ ይልቅ ሊያይ ለሚናፍቅ
የኔን መጨረሻ
በታይታ ላማረ ለግዑዝ አካል ሁሉ
ገርበብ በሉ እና ይችን ቃሌን ስሙ።
ምንም ብትለፉ ሺህ ጊዜ ብጥሩ
ከስኬቴ አጥናፍ ከቶ እኔን ላጥሉ።
ደርሶ ብትንጋጉ ሴራ ብታሴሩ
የፈጠራችሁን አምላክ ሳትፈሩ።
መሰናክል ቢነጉድ ቢቆለል በላዬ
ስሙን የጠራሁ ዕለት ያልፋል በጌታዬ።
@JESUSlovingly142
6 749
ይቅርታ ጠይቅ
"ክህደት"መሆኑን አውቆ ባይከዳም።
"ገነት"ተባሮ ሔዋን አስታው ልቡ
ቢጎዳም።
"ጥፋት" መሆኑን ተግንዝቦ ነው
የተማረ አዳም።
"እናም" በስህተታችን ባንገባም ገዳም።
"ይቅርታ" መጠየቅን እንማር ከ አዳም።
6 749
እንፀልይ
ሰላም ለሀገራችን ሰላም ለኢትዮጵያ።
ከድህነት አውጣት ከጦርነት ትቢያ።
እባክህ ፈጣሪ መከራዋን ቋጨው።
በዝቷል እያደረ ለሞት የሚታጨው።
ያ የደጉን ዘመን መልስና ካሳት።
ሀገራችን ይብቃት ደዌና ትኩሳት።
የጦሩን ጫፍ ሰብሮ ተራምዶት ይቅርታ።
ሰይጣንም ይዋረድ በፀሎት ይረታ።
እናም እንፀልይ በ አንድነት ቆመን።
የባሪያ ግዳጁ ጌታውን መለመን።
ጌታው ደግሞ ማድረግ ነውና ግዳጁ።
ሰላሙም አማኑም ሁሉም ነገር በእጁ።
እናም ፈጣሪየ
በጦርነት ህዝብ ያልቃል።
ሰው ቀየውን ግድ ይለቃል።
እንስሳውም ይጨነቃል።
እባክህን ፈጣሪየ መከራችን ይበቃል።
ይብቃችሁ በለን በ አንድ ቃል።
የአንተው ቃል ሰውን ከፈጠረ።
ሰማዩንም በከዋክብት ካሳመረ።
መከራ ይብቃሽ በላት ለዚች ዓለም።
ባንተ ቃል ሁሉ ይድናል
ካንተ በላይ ሀይል የለም።
ኢየሱስ
@JESUSlovingly142
6 749
“እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥20
6 749
ጩኸት መሰል ስብከት
ጴጥሮስ ጌታን ክዶ አምላኩን ሲረሳ
አውራ ዶሮ ጮኾ ንስሓን ሲያወሳ
ትዝ ይለው ጀመረ የበደለው በደል የሰራው አበሳ፤
ጌታ ሁሉ ካንተ ርቀው ቢሄዱም
እኔ ካንተ ጋር ነኝ መቼም አልተውህም
ምን ቢያበዙብኝ ፃዕርና ህማም
ሞት እንኳን ቢመጣ ከቶ አልክድህም
ሲል እንዳልነበረ ሆኖ በስሜት
ሲመጣ ያ ጊዜ የጭንቁ ሰአት
አላውቀውም ብሎ ሲምል ሲገዘት
ቃሉን አስታወሰው የዶሮው ጩኸት፤
ይህ ሰባኪ ዶሮ በእውነት የታደለው
ምእራፍ ቁጥር ሳያውቅ ወንጌሉ ሳይገባው
ጴጥሮስን ታድጎ ለንስሐ አበቃው፤
ዛሬም በኛ ጊዜ በኃጢአት ለምንደክም
እልፍ ሰባኪ ጮኾ ለማይመስለን ምንም
ይህንን ምሳሌ ካስተዋልነው ዳግም
ትልቅ መልእክት አለው ሀጢያትን ለማከም፤
እዥ እንባን አንብቶ ጴጥሮስን ባይተካ
ሰው ሀጢያቱን አምኖ ልቡ ከተነካ በአውራ ዶሮም ሰብከት ይለወጣል ለካ::
@JESUSlovingly142
6 749
ትናንት ባልዋልኩበት ሰዎች አጥብቀዉ ገፉኝ
የትም አትደርስም ብለዉ እጅጉን አጥብቀዉ ጠሉኝ
ግድ የለም በሚል ዝምታ ዘግቼ በውስጤ አነባሁ
አንባየ መሰላል ሆነኝ ከዛሬ መንገዴ ገባሁ
ካሰብኩት ለመድርስ ብዬ ሲገፉኝ አሜን አልኳቸው
ትንሽም መራራት ቢያቆም ቢጨክን በእኔ ልባቸዉ
ፈጣሪን ምርኩዝ አድርጌ ሲገፉኝ ተገፈሁዋቸው
ስወድቅ ምርኩዝ ሆነልኝ አምላኬ ከእኔ ጋራ ነዉ
የልቤን ስለሚያዉቅልኝ መሻቴን ሁሉ ፈጠመዉ
እንደ እነሱማ ቢሆን ተስፋዬ ከዛው ባቆመ
ፀሀይም ባልወጣች ነበር ባስቀሩት እንደጨለመ
ትናንትን ዞር ብዬ ሳስብ ያን ሁሉ ችግር ፈተና
አምላኬ አስችሎኝ እንጂ በእራሴስ ልቤ ባልጠና
ይን ሁሉ ላደረገልኝ ለአምላኬ ላቅርብ ምስጋና
ይድረስ ለገፊዎቼም ከግቧ አትደርስም ላሉኝ
ዛሬን ለማየት በቃሁ ያአምላኬን ፍቅር ስሙልኝ
✍Written by Abraham sisay
@JESUSlovingly142
6 749
ትናንት ባልዋልኩበት ሰዎች አጥብቀዉ ገፉኝ
የትም አትደርስም ብለዉ እጅጉን አጥብቀዉ ጠሉኝ
ግድ የለም በሚል ዝምታ ዘግቼ በውስጤ አነባሁ
አንባየ መሰላል ሆነኝ ከዛሬ መንገዴ ገባሁ
ካሰብኩት ለመድርስ ብዬ ሲገፉኝ አሜን አልኳቸው
ትንሽም መራራት ቢያቆም ቢጨክን በእኔ ልባቸዉ
ፈጣሪን ምርኩዝ አድርጌ ሲገፉኝ ተገፈሁዋቸው
ስወድቅ ምርኩዝ ሆነልኝ አምላኬ ከእኔ ጋራ ነዉ
የልቤን ስለሚያዉቅልኝ መሻቴን ሁሉ ፈጠመዉ
እንደ እነሱማ ቢሆን ተስፋዬ ከዛው ባቆመ
ፀሀይም ባልወጣች ነበር ባስቀሩት እንደጨለመ
ትናንትን ዞር ብዬ ሳስብ ያን ሁሉ ችግር ፈተና
አምላኬ አስችሎኝ እንጂ በእራሴስ ልቤ ባልጠና
ይን ሁሉ ላደረገልኝ ለአምላኬ ላቅርብ ምስጋና
ይድረስ ለገፊዎቼም ከግቧ አትደርስም ላሉኝ
ዛሬን ለማየት በቃሁ ያአምላኬን ፍቅር ስሙልኝ
@JESUSlovingly142
6 749
ትናንት ባልዋልኩበተኝ ሰዎች አጥብቀዉ ገፉኝ
የትም አትደርስም ብለዉ እጅጉን አጥብቀዉ ጠሉኝ
ግድ የለም በሚል ዝምታ ዘግቼ በውስጤ አነባሁ
አንባየ መሰላል ሆነኝ ከዛሬ መንገዴ ገባሁ
ካሰብኩት ለመድርስ ብየ ሲገፉኝ አሜን አልኳቸው
ትንሽም መራራት ቢያቆም ቢጨክን በእኔ ልባቸዉ
ፈጣሪን ምርኩዝ አድርጌ ሲገፉኝ ተገፈሁዋቸው
ስወድቅ ምርኩዝ ሆነልኝ አምላኬ ከእኔ ጋራ ነዉ
የልቤን ስለሚያዉቅልኝ መሻቴን ሁሉ ፈጠመዉ
እንደ እነሱማ ቢሆን ተስፋዬ ከዛው ባቆመ
ፀሀይም ባልወጣች ነበር ባስቀሩት እንደጨለመ
ትናንትን ዞር ብየ ሳስብ የን ሁሉ ችግር ፈተና
አምላኬ አስችሎኝ እንጂ በእራሴስ ልቤ ባልጠና
ይን ሁሉ ላደረገልኝ ለአምላኬ ላቅርብ ምስጋና
ይድረስ ለገፊዎቼም ከግቧ አትደርስም ላሉኝ
ዛሬን ለማየት በቃሁ ያአምላኬን ፍቅር ስሙልኝ
@JESUSlovingly142
6 749
"ነበር "ይሆናሉ
.
.
.
ቁርጥራጭ ሃሳቤን፣
ዉስጣዊ ንዳዴን፣
ማንም የማያዉቀዉ ጥልቅ ሰቀቀኔን፣
በነጭ ወረቀት ላይ ሰብስቤ ላሰፍረዉ፣
በቃላቴ ድርድር ጭንቀቴን ላበርደዉ፣
የልቤን ተንፍሼ መዳኔን እያመንኩ፣
ብዕሬን አንስቼ ለመፃፍ ተጣደፍኩ።
............................
ትርጉም አልባ ፊደላትን ቀጣጥዬ፣
በሀዘን ብሶት በመከራ ተከልዬ፣
ማባሪያ በሌለው በመሪር ለቅሶዬ፣
ወረቀቴ ራሰ በትኩስ እንባዬ።
..............................
ለካ..........
የዉስጥን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥራሉ፣
ካይን ተሰዉረዉ በነዉ ይጠፋሉ፣
ፍቺ ታጥቶላቸዉ ኢምንት ይሆናሉ፣
ተስፋን አጠዉልገዉ ሲቃን ያበዛሉ።
.............................
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ዘላለም አለሜን ሙሾ አላወርድም፣
ዛሬዬን ለነገ አሳልፌ አልሰጥም።
...........................
ፅልመት የዋጣቸዉ አያሌ ቀናቶች፣
እንቅልፍ የራቃቸው ረጃጅም ሌቶች፣
በማይነጥፍ እምነት፣
በማይጎድል ትዕግሥት፣
በማይሟሽሽ ፅናት፣
በጊዜ መሪነት ተጥለው ያልፋሉ፣
በአዲስ ተተክተዉ ነበር ይባላሉ፣
ለልጅ ልጅ ሚነገር ታሪክ ይሆናሉ።
......................................................
@JESUSlovingly142
6 749
..ምንድን ነው መለኪያህ
ያንተነት መለኪያህ ሚዛን የአምሮህ
ልጠይቅህ እስኪ ምንድን ነው መለኪያህ
መልክ ነዉ ቁመና ዉፍረት ወይስ ቅጥነት
በዉሀ ለቃቂ አብረቅራቂ ዉበት
ወይስ የማይታይ ዉስጣዊ ቅንነት
ምንድን ነዉ መለኪያህ ሚዛን የአምሮህ
Written by abrilo
የጥያቄ መልስ
በዚህ👉🏽 @AMEN_23b
