GRACE_TUBE ™✍
Open in Telegram
🗣የማይረዱህ ሰዎች ስላላዩህ ላንተ ምንም የማይፈይዱልህ ስዎች አልፈውክ ስለሄዱ ግራ ልትጋባ አይገባም ከወደክበት ልትነሳ እግዚአብሔር አንተን ለማንሳት በማን አይን መታየት እንዳለብክ የሚያውቅ ጌታ ነው!! ቢመችህም ባይመችህም ቦታው ቦታህ ካልሆነ መነሳትህ አይቀርም!! በመጥፎ ሰዎች ትብታብ በተናጠች ሀገር ውስጥ በጎ ሰዎች እንዳሉ አትዘንጉ share @JESUSlovingly142
Show more6 749
Subscribers
No data24 hours
-287 days
-7930 days
Posts Archive
6 749
#የትኩረት_መዛባት!
ከእቅድህ ክልል ውጪ በሆነው ነገር ላይ ትኩረትህን በመጣል ዘመንህን አታቃጥል፡፡ በየእለቱ የምታሰላስለው፣ የምታየው፣ የምትመኘውና ስሜትህንና ጊዜህን የምታሳልፈበትን ነገር አስበው፡፡ ይህ ነገር በወደፊት እቅድህና ዓላማህ ውስጥ የተካተተ ነገር ካልሆነ ወይም ከዚያ ጋር ግንኙነት ከሌለው የትኩረት መዛባት ውስጥ ነው ያለኸው፡፡
ወደ አንድ አቅጣጫ ለመድረስ ዓላማን ይዞ ወደፊት የሚሄድ ሰው የትኩረቱ ቅኝትና የስሜቱ ግለት በዚያው አቅጣጫ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የሚገሰግሰው ወደፊት፣ የሚያየውና የሚመኘው ግን የጎንዮሽ ወይም ወደኋላ ከሆነ የትኩረት መዛባት አለ፡፡ ከእቅድህና ከዓላማህ ውጪ ስለሆነ የሕይወት ዘይቤ ሲያወጡና ሲያወርዱ መዋል . . . ልታገኛቸው የማትችላቸውንና በሕይወትህ ምንም መዋጮ ሊያደርጉ ስለማይችሉ ሰዎች ሁኔታ ሲደመሙ ውሎ ማደር . . . ካለህ ወቅታዊ እውነታም ሆነ ከወደፊት እቅድ ጋር በፍጹም ሊጣጣምና ሊዋሃድ በማይችል አለም ውስጥ በሃሳብ ሲዋዥቁ መኖር . . . የተዛባ ትኩረት!
ዓላማህን ለይተህ እወቅ . . . እውነታህን ተቀበል . . . ትኩረትህን በዚያ ላይ ሰብስብ . . . ሃሳብህን፣ ምኞትህን፣ ስሜትህንና ያለህን አቅም ሁሉ በዚያ ላይ አውለው! የሆንከውን፣ ያለህን ነገርና ሁለንተናህን አስተባብረህ ወደፊት በመገስገስና እደርስበታለሁ ብለህ በማመን ባላቀደከው ነገር ላይ አይንህንና ሃሳብህን በመትከል ጊዜህን አታባክን፡፡ የትኛው ንስር ነው ከፍታው ላይ መብረሩንና መናጠቁን ትቶ የሜዳ እንስሶችን ሩጫ ሲመኝ የሚውለው? የትኛው አንበሳ ነው ደኑን እየገዛና እያደነ ከመኖር ይልቅ በውሃ ዳር ሆኖ የአሳዎችን ዋና በማየትና በመመኘት ጊዜውን የሚያሳልፈው? . . . እነዚህ ምሳሌዎቻችን የወደፊታቸው በሌለበት ነገር ላይ ጊዜያቸውን አያባክኑም፡፡ ትኩረትህን ወደ ማንነትህና ወደ ነገው ዓላማህ መልስ!
@JESUSlovingly142
6 749
፡
፡
የሰው ልጅ ከንቱ ነው ባህሪው ደባሪ፣
ድርጊቱ አስጠሊታ ቅስምንም ሰባሪ፣
ወድቆ እየሰገደ በፍቅር ተጎድቶ፣
ሊንከባከባት ሲሻ ፤ ሁሉ ነገሩን ሰቶ፣
ልቡን አስረክቧት በድኑን በባዶ ሰፍቶ፣
፡
ትገፋዋለች እሷ ልቡንም ጠልዛ፣
እንዳያይ አድርጋ አንገቱን ጠምዝዛ፣
፡
በሱ ጨክና እንዲያ ከሚወዳት፣
ቅንጣት ያክል ክብር በወጉ ላልሰጣት፣
ሴትነቷን ክብሯን አውርዶ ላየው ሰው፣
እንካ ትለዋለች በለሴን ቅመሰው፣
6 749
የሚረዱዋቹ የሚያግዙአቹ ሰዎች ያላቹ እግዚአብሔር የሰጣቹ ሰዎች በጣም እድለኞች ናቹ አትጡዋቸው አታሳዙኑዋቸው ተንከባከቡዋቸው እነሱን እግዚአብሔር ስለሰጣቹ አመስግኑት ፍቅራቹን ግለፁላቸው አብረኸኝ ስላለህ/ሽ አመሰግናለሁ በሉዋቸው
6 749
አንተ ስለሰዎች መምጣት እና መሄድ ትነግረኛለህ እኔ ግን ልንገርህ እድሜን ሙሉ ማለት ይቻላል እግዚአብሔር ለሌላው እንድኖር ስል እንድሰጥ ሲሰጠኝ ነበር ሰዎችን በእኔ ምክንያት ያግዛል ይረዳል ካለሁበት ስፍራ አስነስቶ ሩቅ ድረስ ልኮኝ እንድረዳ ያደርገኛል የሚገርመው ግን እኔ ሰው ባስፈለገኝ ጊዜ ማንም ነበር የሌለው ከብዙኦች አንድም አልነበረም አልደረሰልኝ አሁን ስላለሁት ሁኔታ ብታየኝ ደና ነኝ ምንም የሆንኩ የደረሰብኝ አይመስልም እውነታው ግን እኔና ጌታ ነን እምናውቀው አንዳንዴ የተፈጠርንበት አላማ ለራስ ሳይሆን ለሌላው ይሆናል መቻል ነው እስካለን ምንም ሳናሳብብ ምንም ሳንል ዘመም ለደበቅነው ህመም...... ቺርስ
6 749
አሁን ላይ ለነገሮች ብዙ ፍላጎት የለኝም ሰማይ ሁላ የሚናፍቀኝ በዛ #ኢየሱስ ስላለ ነው እንጂ እሱንም አልናፍቅም
#ኢየሱስ ስሙ ሲጠራ በራሱ ውስጥንን ያሳሳል ደስታን ይሰጣል ፈገግታን ይፈጥራል #ኢየሱስ_ይናፈቃል ናፍቆኛልም
6 749
አሁን ላይ ለነገሮች ብዙ ፍላጎት የለኝም ሰማይ ሁላ የሚናፍቀኝ በዛ #ኢየሱስ ስላለ ነው እንጂ እሱንም አልናፍቅም #ኢየሱስ ስሙ ሲጠራ በራሱ ውስጥንን ያሳሳል ደስታን ይሰጣል ፈገግታን ይፈጥራል #ኢየሱስ_ይናፈቃል
6 749
በፊት ያልነበረ ሳይታሰብም ሆነ በሆነ አጋጣሚ በሆን ምክንያት የገባቹበት ነገር ያንን ነገር ግን ማቆም ፈልጋቹ ያልቻላቹ ጉዳዩ ምንም ሊሆን ይችላል አለሁ እናውራበታለን 👉@Abrelo_23
