For the truth
Open in Telegram
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ት/ቶችን መንፈሳዊ ጹሑፎችን መንፈሳዊ መጽሐፍትንና የተለያዩ አባባሎችን ያገኛሉ ለ እውነት ለመቆም አንታክትም!
Show more402
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
‘The Church falters in her mission when we begin to think that the success of her mission depends on us.’
— Jeff Kingswood
የንጋት ኮከብ የሆነው ክርስቶስ በልባችን እንደ ውጋጋን ብርሃን ይፈነጥቅ ዘንድ ራሳችንን በቃለ እግዚአብሔር ውስጥ እናጠልቃለን።
ኬቭን ዲያንግ
ጸሎት በራሱ አይከፍትም አይዘጋምም፤ ጸሎትን ሰምቶ የሚከፍት የሚዘጋም እግዚአብሔር ብቻ ነው። ታዲያ ሰምቶ በሚመልስ በልዑሉ እንጂ በጸሎታችን አንታመን!
Barnabas bekelle
በብዙ በሽታ፣ ደዌ፣ መከራ እና ሥቃይ ስናልፍ፣ ከእኛ ጋር አብሮ የሚወዛገብ፣ በጒዳዩ ላይ ቊብ አጥቶ ግራ የሚጋባ፣ ነገ ምን እንደምትይዝ የማያውቅ እና ነገን የማይቈጣጠር አምላክ የለንም።
“በአንድ ሳንቲም ከሚሸጡት ሁለት ድንቢጦች አንዲቷ እንኳ ያለ አባታችሁ ፈቃድ ምድር ላይ አትወድቅም።” (ማቴ. 10፥29)
ይህ በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ቋንቋ፣ በዓለም ላይ በጣም የማይረባውን እና አናሳውን ኩነት (Insignificant event) ተመልክቶ፣ እርሱንም የሚገዛው እግዚአብሔር ነው ብሎ ማወጅ ነው። በሌላ በኲል ደግሞ፣ ሕማማታችን ምንም የማይገደው፣ ስንሠቃይ ከሩቅ ሆኖ የሚያይ እና ለራሳችን የሚተወን አምላክ የለንም። የምናመልከው ንጉሥ፣ “የሕማም ሰው” የተባለውን ነው። ይህችን የሥቃይ ምድር ጐብኝቶ፣ የውርደትን እና የሥቃይን ጥግ ያየ፣ ስብራትን ጠንቅቆ የሚያውቅ (በልምምድ) አምላክ ነው ያለን። ጌታችን ያለፈበት ታዋቂው መንገድ፣ “የሕማም መንገድ” (Via Dolorosa) ነው። ማንም ዘልቆ ሊዳስስ የማይችለውን ስብራት የመዳሰስ ዐቅም አለው። ለልጆቹ ደግሞ ሁሉን ነገር በመጨረሻው (Ultimately) ለበጎ ይሠራል። “ሁሉን ነገር” ስል፣ ኢ-ፍትሓዊ እና መጥፎ የሚመስሉንን ነገሮች ጨምሮ ማለቴ ነው።
አር.ሲ. ስፕሮል፣ “If God Is Good, Why Do I Suffer?” በተሰኘው ትምህርቱ ማገባደጃ እንዲህ ብሏል:-
አንድ ሐኪም የተወሰኑ ዓመታትን በጣር እና በሥቃይ እንደማሳልፍ ቢነግረኝ፣ ያ ያልጠበቅኩት ነገር ይሆናል። መስማት የማልፈልገው ነገር ይሆናል። በተኛሁበት ሞት ቢወስደኝ እመኝ ይሆናል። የሰው ዘር መደበኛ ዕጣ ከሆነው፣ ከሕመም እና ከጣር እድን ዘንድ ተስፋ አደርግ ይሆናል። ነገር ግን በጭራሽ መስማት የማልፈልገው የመጨረሻ ነገር ቢኖር፣ እያለፍኩ ያለሁበት መከራ ለከንቱ እንደሆነ፣ እንዲሁ በአጋጣሚ የተከሰተብኝ እና እኔ ዕድለ ቢሱ የመከራው ተጠቂ እንደሆንኩ ነው። መከራ ቢገጥመኝ፣ በዛ ውስጥ ማለፍ (መጽናት) የምችልበት ብቸኛ መንገድ፣ ወደ እግዚአብሔር ሄጄ እንዲህ በማለት ነው፣ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ለምን በዚህ መከራ እንደጐበኘኸኝ አላውቅም፤ ነገር ግን በሕይወቴ የአንተ ጥሪ እስከሆነ ድረስ፣ ልቋቋመው እችላለሁ፤ ልታገሠው እችላለሁ።” በዚህ መከራ እንዳልፍ የእግዚአብሔር ዐላማ መሆኑን እስከተገነዘብኩ ድረስ፣ ምክንያቱ ደግሞ ሁሉም ተደምሮ ለበጎ እንዲሠራልኝ እንደሆነ ዐውቃለሁ።
በመከራ ስንናጥ፣ እግዚአብሔር ለጥሪው ታማኝ፣ በመከራ ደግሞ ዐላማው ቅዱስ መሆኑን አንዘንጋ።
ክርስቲያን አወል
"አስበኝ ጌታ ሆይ እኔን ምናምንቴውን ፥ ምንም የለለኝን ፥ ምንም ማድረግ የማልችለውን። በእኔ ውስጥ መልካም አንተ ብቻ ፥ ጻዲቅ አንተ ብቻ ፥ ቅዱስ አንተ ብቻ ነህ።" ታመስ ኬምፕስ
"ኃጢአት ሠርተሃልን? ወደ ቤተ ክርስቲያን ግባ ኃጢአትህንም አርቃት፡፡ በአደባባይ የምትወድቀው ቊጥሩ ከምትነሣው ጋር እኩል ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ በደል ኃጢአት የምትሠራውን ያህልም ፍጹም ተስፋ ሳትቈርጥ ንስሐ ግባ፡፡ ኹለተኛ ብትበድል ኹለተኛ ንስሐ ግባ፡፡ በስንፍና ተይዘህ በፍጹም ምግባር ትሩፋት መሥራት አይቻለኝም አትበል፡፡ በእርግና ዘመን ብትኾንና ብትበድልም እንኳን ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተህ ንስሐ ግባ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሆስፒታል እንጂ ፍርድ ቤት አይደለችምና፡፡ እዚህ ስትመጣ ካህናት [“እግዚአብሔር ይፍታሕ” ብለው] ከኃጢአት እስራት ፈትተው ይቅርታ ይሰጡሃል እንጂ “ለምን በደልህ?” ብለው አይፈርዱብህምና፡፡ ስለዚህ፡- “አንተን ብቻ በደልሁ፤ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ” ብለህ ለእግዚአብሔር ንገረው፤ ኃጢአትህም ይቀርልሃል።
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
