en
Feedback
For the truth

For the truth

Open in Telegram

በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ት/ቶችን መንፈሳዊ ጹሑፎችን መንፈሳዊ መጽሐፍትንና የተለያዩ አባባሎችን ያገኛሉ ለ እውነት ለመቆም አንታክትም!

Show more
402
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
" አንተ ጐበዝ፥ በጕብዝናህ ደስ ይበልህ፥ በጕብዝናህም ወራት ልብህን ደስ ይበለው፥ በልብህም መንገድ ዓይኖችህም በሚያዩት ሂድ፤ ዳሩ ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንዲያመጣህ እወቅ። " (መጽሐፈ መክብብ 11:9)

"ውሸት አቋራጭ ብትመስልም፣ ያልተገባ ጥቅም ልታስገኝ ብትችልም፣ ከተጠያቂነት ልታስመልጠን ብትችልም በሞት ጎዳና ላይ ያለብርሃን የምትተወን ጨካኝ አገልጋይ ነች። ከእግዚአብሔር ዕይታ ምንም ላይሠወር፣ ከፍርዱም ማንም ላያስጥለን ውሸት በሽንገላዋ የሐሰት ዋስትናን ትሰጠናለች። ውሸት ተዋግተን ከሕይወታችን ልናስወግደው የሚገባን ክፉ የዐመጽ ሥርዓት ነው።" ተስፋጽዮን አለማዬሁ

"ፍጹም ነፃ የሆነ ፍቅር | ግንቦት 17 ............................... ሰማያት፣ ሰማየ ሰማያት፣ ምድርና በእርሷም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር አባቶች ህን ስላፈቀረ፣ ወደዳቸው፤ ዛሬም እንደ ሆነው የእነርሱ ዘር የሆናችሁትን እናንተን ከአሕዛብ ሁሉ ለይቶ መረጣችሁ። (ዘዳግም 10፥14-15) ............................... እግዚአብሔር በምርጫው ያሳየው ፍቅር — ማለትም ሰዎችን ለራሱ የሚመርጥበት ፍቅር — ፍፁም ነፃ የሆነ ፍቅር ነው። ወሰን የለሽ ከሆነው ደስታውና ጥበቡ ያለማቋረጥ የሚፈስስ ነው። ዘዳግም 10፥14-15፣ እግዚአብሔር እስራኤልን ከሌሎች የምድር ሕዝቦች ሁሉ በመምረጡ የተሰማውን ደስታ ያብራራል። እነዚህን ሁለት ነገሮች አስተውሉ፦ መጀመሪያ፣ በቁጥር 14 እና 15 መካከል ያለውን ልዩነት ተመልከቱ። ሙሴ፣ የእስራኤልን መመረጥ ዓለማት ሁሉ የእግዚአብሔር ከመሆናቸው ጋር አያይዞ ለምን ተናገረ? በቁጥር 14 ላይ፣ “ሰማያት፣ ሰማየ ሰማያት፣ ምድርና በእርሷም ያለው ሁሉ የአምላክህ የእግዚአብሔር ነው” ካለ በኋላ፣ በቁጥር 15 ላይ፣ “እናንተን ከአሕዛብ ሁሉ ለይቶ መረጣችሁ” ያለበት ምክንያት ምንድን ነው? የዚህ ምክንያት እግዚአብሔር አማራጭ ስላልነበረው፣ ወይም በሆነ ምክንያት ስለተገደበ ብቻ እሥራኤልን እንዳልመረጠ ለማሳሰብ ይመስላል። “አንድ አምላክ የራሱ የሆነን አንድ ህዝብ ብቻ ይኖረዋል እንጂ፣ ሌላው ሁሉ የእርሱ ሊሆን አይችልም” የሚለውን በዘመኑ የነበረው ጣኦታዊ አስተሳሰብ ከንቱ አድርጎታል። እውነቱ ይህ ነው፦ ያህዌ ብቸኛና እውነተኛ አምላክ ነው። አጥናፈ-ዓለሙ ሁሉ የእርሱ ነው። ስለዚህም፣ የፈለገውን ህዝብ ለራሱ መርጦ የመውሰድ መብትና ስልጣን አለው። እናም ለእስራዔላውያን ሊነገር የማይችል አስገራሚ እውነት የሆነላቸው፣ እግዚአብሔር እነርሱን መምረጡ ነው። ግዴታ አልነበረበትም። የፈለገውን ሕዝብ መምረጥ ይችል ነበር። የማዳን ሥራውን ለመግለጥ ደስ ያሰኘውን ሕዝብ የመጥራት መብትም እድልም ነበረው። ካሻው ሁሉንም መምረጥ፣ ካልፈለገ ደግሞ ማንንም አለመምረጥ ሙሉ መብቱ ነበር። ስለዚህ፣ እግዚአብሔር ራሱን “የእነርሱ አምላክ” ብሎ ሲጠራ፣ ከግብፅ ወይም ከከንዓን አማልክት ጋር ራሱን እኩል እያደረገ አይደለም። ሕዝቦቹም ሆነ አማልክቶቻቸው ሁሉ የእርሱ ናቸው። ቢፈልግ፣ ፈፅሞ የተለየ ህዝብን ለሥራው መምረጥ ይችል ነበር። ቁጥር 14 እና 15ን እንደዚህ ባለው መልኩ ማስቀመጥ የተፈለገው፣ ፍፁም መብት እና ሉዓላዊ ሥልጣን ሁሉ የእግዚአብሔር ብቻ መሆኑን አጽናዖት ለመስጠት ነው። ልናስተውለው የሚገባው ሁለተኛው ነገር፣ በቁጥር 15 ላይ፣ እግዚአብሔር ሉዓላዊ ነፃነቱን ተጠቅሞ አባቶቻቸውን መውደዱን ነው። “ብቻ እግዚአብሔር ስለ አባቶችህ ደስ ብሎታል፥ እነርሱንም ወድዷል“። የእስራኤልን አባቶች በመውደድ ደስ እንዲለው መረጠ። እግዚአብሔር ለእስራኤል አባቶች የነበረው ፍቅር ፍፁም ነፃ እና በምህረት የተሞላ ነበር እንጂ፣ በእነርሱ አይሁዳዊ ባህርይ ወይም ብቃት ላይ የተመሰረተ አልነበረም። ይህ በክርስቶስ ለምናምን ለእኛ ትምህርት ነው። እግዚአብሔር እንዲሁ በነፃ መርጦናል። አንዳች መልካም ነገር ስለተገኘብን ሳይሆን እንዲሁ ይህን ማድረግ ደስ ስላለው ብቻ በነፃ መርጦናል።"

Q:ከእናንተ መካከል የታመመ ሰው አለ? A: የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎችን ይጥራ፤ እነርሱም በጌታ ስም ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት።  ያዕቆብ 5:14 NASV from @Christisallsufficient

እግዚአብሔር ታማኝ ነው!

እጅግ ካስጨነቀኝ ጨቋኝ ሸክም ነፃ ወጥቻለሁ። የሀዘን መንፈስ ከእኔ ተወስዷል። በእውነት በአምላኬ በመድኃኒቴ መደሰት ምን እንደሆነ አወቅሁ።     __ጆርጅ ዋይትፊልድ

ስለ ፍቅር ግንኙነት... ከምን አይነት ሰው ጋር የ ፍቅር ግንኙነት እንጀምር...... ፍቅር ግንኙነት ውስጥ ምን ማድረግ አለብን ግንኙነቱ እንዳይፈርስ....... ስለ masterbation(ሴጋ ) ምጥፎነት ይዞት እሚመጣው በሽታ የ ስለልቦና ምክር ለማገኘት..... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

• ምንም አይነት ኃጢአተኛ ብትሆኑ ወደ እርሱ ቅረቡ፣ ያበራላችኋል፣ ይምራችኋል። • መሰበር ቢያደክማችሁ፣ ጸጋ ይጠግናችኋል። • ኃጢአት ቢያዋርዳችሁ፣ ምሕረት ያከብራችኋል። • በደል ቢያቆሽሻችሁ፣ የደሙ መርጨት ንጹሕ ያረጋችኋል። • ለምንም እንዳማትሆኑ ቆጥሮ ይሄ አለም ቢወረውራችሁ (ቢያሽቀነጥራችሁ)፣ ክርስቶስ ኢየሱስ በፀጋው ሞልቶና አስታጥቆ እንደገና ያነሳችኋል። • ዓለም ከዝርዝሩ ቢሰርዛችሁ፣ የዘላለም አባት በሕይወት መዝገብ ላይ ያሰፍራቹኋል። ⨳ ወደ እግዚአብሔር ስትቀርቡ የሰራችሁት ማንኛውም አይነት በደልና ኀጢአት በናንተ ውስጥ ቢገኝ ራሳችሁን በመክሰስ አራንቋ ውስጥ አትጨምሩ። ወደ እግዚአብሔር ፀጋ ቅረቡ። እግዚአብሔር ምሕረቱን ፍለጋ በሚቀርቡት እንጂ ሸሽተው በሚሮጡት ደስ አይለውም።... ልቡ ከሰማያት ይልቅ የሰፈው እግዚአብሔር ይቅር ይላችኋል።     __ሰለሞን አበበ ገብረመድህን

• ምንም አይነት ኃጢአተኛ ብትሆኑ ወደ እርሱ ቅረቡ፣ ያበራላችኋል፣ ይምራችኋል። • መሰበር ቢያደክማችሁ፣ ጸጋ ይጠግናችኋል። • ኃጢአት ቢያዋርዳችሁ፣ ምሕረት ያከብራችኋል። • በደል ቢያቆሽሻችሁ፣ የደሙ መርጨት ንጹሕ ያረጋችኋል። • ለምንም እንዳማትሆኑ ቆጥሮ ይሄ አለም ቢወረውራችሁ (ቢያሽቀነጥራችሁ)፣ ክርስቶስ ኢየሱስ በፀጋው ሞልቶና አስታጥቆ እንደገና ያነሳችኋል። • ዓለም ከዝርዝሩ ቢሰርዛችሁ፣ የዘላለም አባት በሕይወት መዝገብ ላይ ያሰፍራቹኋል። ⨳ ወደ እግዚአብሔር ስትቀርቡ የሰራችሁት ማንኛውም አይነት በደልና ኀጢአት በናንተ ውስጥ ቢገኝ ራሳችሁን በመክሰስ አራንቋ ውስጥ አትጨምሩ። ወደ እግዚአብሔር ፀጋ ቅረቡ። እግዚአብሔር ምሕረቱን ፍለጋ በሚቀርቡት እንጂ ሸሽተው በሚሮጡት ደስ አይለውም።... ልቡ ከሰማያት ይልቅ የሰፈው እግዚአብሔር ይቅር ይላችኋል።     __ሰለሞን አበበ ገብረመድህን    

ከምንም ሁሉን ያስገኘ ፣ ካለመኖር ፍጥረትን ወደ መኖር የጠራ ፣ በደካማው ብርቱ ሼል ፣ በተናቀው ድንቅ ተግባር የከወነ እርሱ ብርቱ ነው። ውቅያኖስን በርምጃ የሚሻገር ፣ ውኃን እንደ ክምር የሚያቆም ፣ ባሕር ከፍሎ የሚያሳልፍ ፣ በወጀብ ውስጥ መንገድ የሚሰጥ እርሱ ብርቱ ነው። መረቡን በዓሳ ፣ ጓዳን በበረከት የሚሞላ ፣ በባዶ የሚያኖር እርሱ ብርቱ ነው። የዛሬውን ቀን የሚገዛ እርሱ ብርቱ ነውና በእግዚአብሔር የምትታመኑ በርቱ ልባችሁ ይጽና !!!    from @one_died_for_all   

How can we love sin when we remember that because of our sins Jesus died? Surely, no one could be so holy as the disciples of a crucified Lord. J.C. Ryle

ቤዛዬ! በይሁዳ ቤተልሔም በአናጢው ዮሴፍ ቤት ተወልዶ ያደገው ብላቴናው ኢየሱስ ፥እንደ ዕብራዊያንም የመንጻት ልማድ በስምንተኛው ቀን ሲገረዝ የበግ ጠቦትን መሰዋት ካልቻለ ይልቁኑ የእርግብ ጫጩቶችን ካቀረበ ጉስቁል ቤተሰብ መሃል የኖረ እሱ የዓለማቱ ጌታ፥የመላለሙ ፈጣሪ፥ የፍጥረቱ ሁሉ ገዢ ነው እያልኩህ ነው። ወንድን ከማታውቅ ታዳጊ ወጣት፤ ትውልድም ሁሉ ብጽእት ከሚላት ድንግል የተወለደ እሱ በህይወት ለመሰንበት የእናቱ ጡቶች ላይ ጥገኛ ሆኖ ቢገኝም ህያዋን ሁሉ የሚደገፉበት የህይወት ሁሉ ራስ ነው እያልኩህ ነው።ሽንት ጨረቁን እናቱ የቀየረችለት ያ ኢየሱስ ከዋክብትን በስም የሚጠራ፣ ነጎድጓድም የሚታዘዝለት ሃያል ነው። ከፈለክህ ነሆለል ነህ በለኝ። አሊያም ጨርቁን የጣለ ወፈፌ። ጌታዬ ብዬ ግን ምሰግደው ለእሱ ነው! በእድሜው ማለዳ የንጉስ ድንፋታን ሸሽቶ ወደ ግብጽ በስደት የወረደ እሱ የነገስታትን ልብ እንደ ፈሳሶች ወደ ፈለገበት የሚያቀና ነው። በመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ በዮርዳዮስ የተጠመቀ እሱ ባህር አይታ የሸሸችው፣ ዮርዳኖስም ወደ ኋላ የሚሸሽለት ራሱ ነው። ''የሰማይ ወፎች ጎጆ፣ ቀበሮዎችም ጉድጓድ'' አላቸው የሰው ልጅ ግን መጠለያ እንኳ የለውም ብሎ የቆዘመው ያ ከገሊላ አውራጃ የሆነው ረቢ ሰማያትን እንደ መጋረጃ የዘረጋ፣ ውሆችንም በእፍኙ የሰፈር ነው።ከፈለክ የአይምሮ ጤና መቃወስ አለብህ ብለህ ክሰሰኝ። አሊያም ጨርቁን የጣለ ንቅል በለኝ። ቤዛዬ ብዬ ግን ማወራህ ስለ እሱ ነው! የቀራጮች ወዳጅ፣ የአመንዝሮች ጓደኛ ተብሎ የተከሰሰው እሱ በህያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ በዙፋን ሚሰየም ነው። በጌተሰማኒ ፍርሃት አቆራምዶት ነፍሱ እስከ ሞት የተከዘችበት እሱ የሞትን መውርወሪያ የሰበረ የሲኦልም ደጅ የገለበጠ ነው። ራስ ቅሉን በእሾኽ ተበስቶ፣ጎኑን በጦር ተወግቶ፣ በግራፋት ብዛት ጀርባው ተልጦ፣ ደም ግባት አጥቶ በእንጨት ላይ ተንጠልጥሎ ያየኸው እሱ ሰማያትን በክብሩ የሸፈነ፣ ምድርንም በሞገሱ የሞላ፣ የውበትም መደምደሚያ ነው። መስቀል መሸከም ከብዶት ሲንገዳገድ ያየኸው፤ በወንበዴዎች መሃል የዋለው እሱ አለማትን በሃያል ቃሉ የደገፈ ነው። ቤዛዬ ነው ምልህ እሱን ነው! የነፍሴ ቤዛ!!! Ebsa burka

"የእኛ መሠረታዊው ችግራቸን ኢኮኖሚያዊ ቢኾን ኖሮ፥ እግዚአብሔር ኢኮኖሚስት ይልክልን ነበር። ችግራችን መዝናኛ ቢኾን ኖሮ፥ እንዲሁ አዝናኝ የሕዝብ አጫዋች ወይም ምርጥ ተዋናይ በላከልን ነበር። ታላቁ አስፈልጎታችን ፖለቲካዊ መረጋጋት ቢኾን ኖሮ፥ ፖለቲከኛ ይልክልን ነበር። የሚያስፈልገን ታላቁ ነገር ጤና ቢኾን ኖሮ፥ ሐኪም ይልክልን ነበር። ነገር ግን፥ ታላቁ ችግራችን በኀጢአታችን ምክንያት ከርሱ ተለይተን መጥፋታችን፥ አስፈሪው ዐመፃችንና ሞታችን ነበርና እግዚአብሔር መድኅን ላከልን።"¹ ዕንኾ፥ የምሥራች። ከዘላለም ጥፋት እንድተርፍ ትርፍ ልጅ ሳይኾን አንድያ ልጁ የሞተልኝ ኀጢአተኛ ነኝ። ይህን ጠንቅቄ ዐውቃለሁ። ከእኔ ትልቅነት ሳይኾን ከሞተልኝ ጌታ ታላቅነት የተነሣ የእግዚአብሔር ልጁ እንጂ ትርፍ እንግዳው አይደለሁም። ማሟያ ሳልኾን በአብ የተመረጥኹ የልጁ ሥራ ውጤት ነኝ። ክብር ለዘላለም ለስሙ ይኹን! ፍቅሩ ወደር የለውም። ¹Donald A. Carson, A Call to Spiritual Reformation: Priorities from Paul and His Prayers (Grand Rapids: Baker, 1992), 109. "ችንካሩ እኔ ነኝ" ከተሠኘው የSolomon Abebe Gebremedhin ጽሑፍ የተወሰደ።

ጌታችን "ተፈጸመ" (ዮሐንስ ወንጌል 19÷30) ብሎ በተናገረው ቃል ውስጥ ያሉ ሦስት ጠቃሚ እውነታዎችን ዐብረን እንመልከት፡፡ ከኹሉ አስቀድሞ ልናውቅ የሚገባው የተናገረው ቃል በወቅቱ ማኅበረ ሰብእ ዘንድ የተለመደ ቃል መኾኑን ነው፡፡ "ቴቴሌስታይ" የሚለው የግሪክ ቃል በርግጥ ለኛ የተለመደ ቃል አይደለም ነገር ግን ጌታችን በምድር በነበረበት ወቅት የተለመደ ቃል ነበር። ባሮች ጌታው ባርያውን አንድን ሥራ እንዲሠራ ያዝዘውና ባርያው ሥራውን ሠርቶ ሲጨርስ ጌታው ዘንድ ይቀርብና "ቴቴሌስታይ - የሰጠኸኝን ሥራ በሙሉ አጠናቅቄያለኹ" ይለዋል፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሠራው የሚገባው ሥራ ነበረው፡፡ በዮሐንስ ወንጌል 17÷4 "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርኹኽ" ብሎ ተናገረ፡፡ ካህናት ይህን ቃል ካህናትም ይጠቀሙት ነበር፡፡ አይሁድ መሥዋዕታቸውን በካህኑ ፊት ያቀርቡ ነበር ምክንያቱም ለእግዚአብሔር የሚቀርበው መሥዋዕት ምንም እንከን እንዳይገኝበት በካህኑ እንዲፈተሽ ሕጉ ያዝዛልና፡፡ ካህኑም ከተመለከተ በኋላ "ፍጹም ነው" ይላል፡፡ (በርግጥ ካህኑ የሚጠቀመው የዕብራይስጥ ወይም የአራማይክን ቋንቋ ነው ቃሉ ግን ቴቴሌስታይ ከሚለው የግሪክ ቃል ጋራ ፍችው ተመሳሳይ ነው። ቴቴሌስታይ! ካህናት ይህንን ቃል ይጠቀሙታል ትርጉሙም ንጹሕ፣ እንከን አልባ መሥዋዕት ማለት ነው፡፡ ማነው ንጹሕ? ማነው እንከን አልባ? ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው! የሥነ ጥበብ ሙያተኞች ባሪያዎች ይህን ቃል ይጠቀሙት ነበር፣ ካህናትም ይህን ቃል ይጠቀሙት ነበር፡፡ ይህን ቃል ሠዓሊዎችም ይጠቀሙት ነበር፡፡ አንድ ሠዓሊ ሥዕሉን ስሎ ሲጨርስ አንድ ርምጃ ወደ ኋላ ፈቀቅ ይልና ሥዕሉን በትኩረት እያየ "ቴቴሌስታይ - ተፈጸመ!" ይላል፡፡ ትርጉሙም ሥዕሉ አልቋል ማለት ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን ምንም እንኳን አንዳንድ ለመረዳት የሚያስቸግሩ ክፍሎች ቢኖሩትም አኽኹን ግን ብሉይ ኪዳንን መረዳት እንችላለን ምክንያቱም ክርስቶስን እናውቀዋለን ብርሃኑ ያበራልናል፡፡ በተግባር የተገለጡት ድርጊቶች ኹሉ ከዚህ በኋላ በጥላ ውስጥ አይደሉም የእግዚአብሔርን ሥዕል ሙሉ ለሙሉ ቁልጭ ብሎ ማየት ችለናልና፡፡ነው። ነጋዴዎች "ቴቴሌስታይ" የተለመደ ቃል ነው፡፡ ባሪያዎች ይጠቀሙት ነበር፣ ካህናት ይጠቀሙት ነበር፣ ሠዓሊዎች ይጠቀሙት ነበር፡፡ እንዲሁም ነጋዴዎችም በሥራቸው ይጠቀሙት ነበር፡፡ ለእነርሱ ያለው ትርጒም ደግሞ "ዕዳው ሙሉ በሙሉ ተከፍሏል" የሚል ነው፡፡ አንድን ዕቃ ስትገዙ ነጋዴው ብሩን ይቀበላችሁና ደረሰኝ ይሰጣችኋል፡፡ ደረሰኙም ላይ ያለው ጽሑፍ "ቴቴሌስታይ - ተፈጽጸመ" ሙሉ በሙሉ ተከፍሏል የሚል ነው። እኔና እናንተ በኀጢአታችን ምክንያት በእግዚአብሔር ዘንድ ባለዕዳዎች ነበርን፡፡ ይህን ዕዳችንንም መክፈል አልቻልንም ነበር፡፡ የእግዚአብሔርን ሕግ የጣስን አጭበርባሪዎች ነበርን፡፡ የኀጢአት ደመወዝ ሞት ነው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ መጣና ዕዳችንን ከፈለው፡፡ ቴቴሌስታይ ማለት ይህ ነው፡፡ የተለመደ ቃል ነው፡፡ ሠራተኛው ሥራውን ፈጽሟል፡፡ እንከን የሌለበት መሥዋዕት ቀርቧል፡፡ ሥዕሉም ተጠናቋል፡፡ ዕዳም ተከፍሏል፡፡ አሜን፣ ሃሌሉ ያ

የወልድን መከራውን የሚናገር ምን ዓይነት አፍ ነው? ምን ዓይነት #ከንፈር ነው? ምን ዓይነት አንደበት ነው? #የፍቅር #ጌታ #ሕማማቱ በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ፤ ሕሊናም ይመታል  #ነፍስም #ትንቀጠቀጣለች #ሥጋም #ይደክማል በእውነትም #የጌታችንን ሥቃይ ለመግለጽ ምንም ዓይነት ቋንቋ  ምንም ያህል ቅኔ አቅም አይኖረውም፡፡    ከቅዳሴ መጽሐፍ የተወሰደ

በእግዚአብሔር እንታመን!

እግዚአብሔር የጠራን (primarily) ወደ ራሱ እንጂ ወደ አገልግሎት አይደለም፤ So መንፈሳዊነት መለኪያው አማኙ ከእግዚአብሔር ጋር ያለው የግል ግኑኝነቱ እንጂ የመድረኮች ስኬቱ ሊኾን አይችልም። Barnabas bekelle

የወላጆችና የልጆች ግንኙነት በወንድም ተካልኝ ኃይለሚካኤል የቀን 13/8/2016 የሰንበት ስበሰባ HRBC