en
Feedback
For the truth

For the truth

Open in Telegram

በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ት/ቶችን መንፈሳዊ ጹሑፎችን መንፈሳዊ መጽሐፍትንና የተለያዩ አባባሎችን ያገኛሉ ለ እውነት ለመቆም አንታክትም!

Show more
402
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
በእግዚአብሔር ማመን አንድ ነገር ነው፤ እግዚአብሔር እንዳለ ማመን። እግዚአብሔርን ማመን ደግሞ ሌላ ነገር ነው። ሕያው እምነት ግን በእግዚአብሔር ተስፋዎች መታመንን ይጨምራል። ምንም እንኳን በዙሪያችን ያለው ነገር ሁሉ የህይወታችንን ከንቱነት የሚመሰክር በመምሰል ተስፋ እንድንቆርጥ ቢያደርገንም፥ ከእግዚአብሔር ጋር የቃልኪዳን ግንኙነት ውስጥ ነን። ስለዚህ እኛ በእግዚአብሔር ተስፋዎች በመታመን የምንኖር ሰዎች ነን። እኛ እርስ በርሳችን የገባነውን ቃል ስናፈርስ እንገኛለን። ለእግዚአብሔር የገባነውን ቃልም ስናፈርስ እንገኛለን። እግዚአብሔር ግን በፍፁም የገባውን ቃል አያፈርስም። በዚህም በታሪክ ውስጥ እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ሊታመን የሚገባው መሆኑን አሳይቷል። ለዚህም ነው፥ በአንድ በኩል በእግዚአብሔር ተስፋዎች ላይ ካለመታመን የበለጠ ሞኝነት የማይኖረው። RC Sproul

ጸጋ ይቅርታም ነው፣ ኃይልም ነው! |
ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ አሁን የሆንሁትን ሆኛለሁ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋ ከንቱ አልሆነም፤ እንዲያውም ከሁሉም በላይ በትጋት ሠርቻለሁ፤ ዳሩ ግን እኔ ሳልሆን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው። (1ኛ ቆሮንቶስ 15፥10)
ጸጋ ኃጢአት ስንሠራ የሚደረግልን ምህረት ወይም ማቅለያ ብቻ አይደለም። ጸጋ ኃጢአትን እንዳናደርግ የሚያስችለን የእግዚአብሔር ስጦታ እና ኃይል ጭምር ነው። ይቅርታ ብቻ አይደለም፣ ኃይልም ጭምር ነው። ለምሳሌ፣ በ1ኛ ቆሮንቶስ 15፥10 ላይ ይህ በግልጽ ተቀምጧል። ጳውሎስ ሥራውን እንዲሰራ የሚያስችለው ኃይል ጸጋ እንደሆነ ይናገራል። በጸጋ ያገኘው የኃጢአቱን ይቅርታ ብቻ አይደለም፤ በመታዘዝ ለመቀጠል የሚያስችለውን ኃይልም ጭምር እንጂ። “እንዲያውም ከሁሉም በላይ በትጋት ሠርቻለሁ፤ ዳሩ ግን እኔ ሳልሆን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው” ይላል።  ስለዚህ፣ እግዚአብሔርን ለመታዘዝ የምናደርገው ጥረት በራሳችን ኃይል የሚሆን አይደለም። ይልቁንም፣ “እግዚአብሔር በሚሰጠው ብርታት፣ ይኸውም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንዲከብር ነው” (1ኛ ጴጥሮስ 4፥11)። ከእምነት የሚመነጭ ታዛዥነት ነው። ማድረግ የሚገባንን ለማድረግ በሚያስችለን፣ በሚያስፈልገን ጊዜ ሁሉ በሚመጣው የጸጋ ኃይል ላይ ያለ እምነት ነው። ጳውሎስ በ2ኛ ተሰሎንቄ 1፥11-12 ላይ፣ እያንዳንዱን የመልካምነት ተግባሮቻችንን “ከእምነት የሆነ ሥራ” ብሎ በመጥራት ይህንን ያረጋግጣል። ከዚያም ይህ ለኢየሱስ የሚሰጠው ክብር “እንደ አምላካችን … ጸጋ መጠን ነው” ምክንያቱም የሚሆነው “በኃይሉ” ነውና በማለት ይናገራል። እያንዳንዱን ሐረግ በሚገባ አድምጡ፦ ይህን እያሰብን አምላካችን ለጥሪው የበቃችሁ አድርጎ እንዲቈጥራችሁ፣ መልካም ለማድረግ ያላችሁን ምኞትና ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን ሁሉ በኀይሉ እንዲፈጽምላችሁ ዘወትር ሾለ እናንተ እንጸልያለን። ደግሞም እንደ አምላካችንና እንደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ መጠን የጌታችን የኢየሱስ ስም በእናንተ ዘንድ እንዲከብርና እናንተም በእርሱ እንድትከብሩ ይህን እንጸልያለን። እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘው መታዘዝ የሚመነጨው፣ በእግዚአብሔር የጸጋ ኃይልና በእምነት አማካኝነት ነው። በሁሉም የክርስትና ሕይወት ደረጃዎች ውስጥ ይህ እውነት ይሠራል። በእምነት የሚያድነን የእግዚአብሔር የጸጋ ኃይል፣ ያው ልሹ በእምነት በኩል የሚቀድሰን የእግዚአብሔር የጸጋ ኃይል ነው (ኤፌሶን 2፥8)። ያዳነን ያው ጸጋ በቅድስና እንድንኖር ኀይልን ይሰጠናል።

ጌታ በመንፈሱ በቃሉ መርምሮ ስራችንን ቢነግረን ዘርዝሮ በእዉቀቱ ተደንቀን በኑሯችን አፍረን ንስሃ ገብተናል ይቅር በለን ብለን ፓ/ር ተስፋዬ ጋቢሶ @savedbygracealone @savedbygracealone

ጌታ ሆይ ጨርቅህን ይዤ እማጸናለሁ ካንተ ወዴት ከቶ ሄዳለሁ ደጃፍህ ብኖር ተጥዬ ክብሬ ነው ለእኔ ደስታዬ ዶ/ር ደረጀ ከበደ @savedbygracealone @savedbygracealone

የእግዚአብሄርን ፈቃድ ያለመታዘዝ አሁን ቀላላል ነገር ቢመስልም ጌታ በሚመለስበትና  ሥራችንን በሚመረመርበት ግዜ ግን እጅግ ከባድ ችግር ያስከትላል ። @savedbygracealone

እግዚአብሔር እንድያይብህ የማትፈልገውን ነገር አታድርግ። እግዚአብሔር እንዲሰማብህ የማትፈልገውን ነገር አትናገር። እግዚአብሔር እኖዲያነብብህ የማትፈልገውን ነገር አትጻፍ። እግዚአብሔር እንዲያገኝህ በማትፈልገው ቦታ አትሂድ። እግዚአብሔር ሲታነበው እንድደርስህ የማትፈልገውን መጽሐፍ አታንብብ።                 ጄ.ራየል

ኃጢአትን እንደከንቱ የምታስቡ ክፉን እንደምንም የምትቆጥሩ የኃጢአትን ክፋት ተመልከቱ ታላቅ ጥፋቱን ገምቱ የቀረበውን መስዋዕት አስተውሉ ማን ላይ እንዳረፈ አስፈሪ ፍርዱ ቃል በሆነው በመሢሑ ላይ በሰው ልጅ በአምላክም ልጅ ላይ ነው። ይሽሩን ግርማ

Repost from For the truth
ኃጢአትን እንደከንቱ የምታስቡ ክፉን እንደምንም የምትቆጥሩ የኃጢአትን ክፋት ተመልከቱ ታላቅ ጥፋቱን ገምቱ የቀረበውን መስዋዕት አስተውሉ ማን ላይ እንዳረፈ አስፈሪ ፍርዱ ቃል በሆነው በመሢሑ ላይ በሰው ልጅ በአምላክም ልጅ ላይ ነው። ይሽሩን ግርማ

እውነተኛ ንስሐ እግዚአብሔርን በመውደድ ተጀምሮ ኀጢአትን በመጥላት ይጠናቀቃል። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን ••••••••••••••••

ንስሐ የገባንበት የኀጢአት ቢዘረዘር የእግዚአብሔርን ጸጋ እናያለን እንጂ አንሸማቀቅም። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን ••••••••••••••••

ለኀጢአት ጥላቻ የሌላቸው ሰዎች ለንስሐ እንግዶች ናቸው። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን ••••••••••••••••

ዳግመኛ የተወለደ ሰው ኀጢአትን የሚጠላው ስለ ሲኦል ሲል ብቻ አይደለም፤ እንደ ሲኦልም ጭምር ነው። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን ••••••••••••••••

ኀጢአት ካላስጠላህ ክርስቶስን አትወደውም፤ መንግሥቱንም አትናፍቅም። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን

ኀጢአት ከመረረን ኢየሱስ ጣፍጦናል ማለት ነው። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን ••••••••••••••••

በዚህ ምድር ለቅዱሳን የተሰጡ ሁለት ታላላቅ ጸጋዎች እምነትና ንስሐ ናቸው። •••••••••••••••• ቶማስ ዋትሰን •••••••••••••••

"ይድረስልኝ ለውድ ማንም ማይደግፈን እና ያላጨበጨበልን! አይዞህ ያላለን ፣ መንገዳችን የተወሰነልን፣ ለሌላው ፍቅር እና ክብር ተሰቶ ክብር የተነፈግን፣ ይህ ነው መንገዳቹ የተባልን፣ ህልሞቻችንን የደበቅን፣ ለብቻችን ነን ላልን... ይድረስልኝ "ልያ ዐይነልም ስትሆን" ባሏ አሳንሷ ሚወዳትን ልያን፣ አባቷ ከዘለፋ ለመትረፍ ደብቆ ያለፈቃዷ የዳራትን፣ በማህበረሰቡ ራሔል እስክትመጣ ለመጠበቂያ የተዳረች፣ የአባት እና የባል ቁማር ፣ ፀሐፊው ሲገልፃት"ራሔል ግን ቁመነዋ ያማረ መልኳም የተዋበም ነበር" (ዘፍ 29:17) "ልያ ግን ዐይነ ልም" ነበረች። "እግዚአብሔር ልያ እንዳልተወደደች ባየ ጊዜ" ... ከማህበረሰብ እና የኪዳን ሰው ነው ብሎ ከያዕቆብ ስሜት ጋር አልቆመም፣ ውብ የሆነች አለች ሁሉም የሚወዳት ብሎ ጀርባውን ለልያ አልሰጠም።"እግዚአብሔር ልያ እንዳልተወደደች ባየ ጊዜ ማህፀኗን ከፈተላት"(ዘፍ 29:31)። እግዚአብሔር እንደአባቷ፣ እንደ ያዕቆብ እና እንደ አደገችበት ማህበረሰብ እንዳልሆነ ስታውቅ፡ ከተገፉት ጋር፣ ማንም ከሌላቸው ጋር እንደሚቆም፣ ማንም ለማይፈልጋቸው ጋሻ እንደሆነ ስታውቅ "እግዚአብሔር መከራዬን ተመለከተልኝ" አለች። እግዚአብሔር መገፋትን ሲመለከት ዝም ብሎ ልጅ ብቻ አደለም ሚሰጠው፤ ከልያ ልጆች ከሆኑት ከሌዊ የክህንነት ዘር ፣ ከይሁዳ ደሞ የነገስታት ዘር ፡ በመጨረሻም ንጉሱ ክርስቶስ መጣ። ይድረስልኝ ማንም በመንገዳቹ እና በማህበረሰባቹ በዘራቹ ባይኖር፣ ማንም ያልነበራትን ልያን የተመለከተ፣ ያከበረ አምላክ ዛሬም ህያው ነው። ያያል፣ ይሰማል! ይመልሳል።እግዚአብሔር ጎብኝቶ እንደ ልያ ለምስክርነት ያደርሳናል። ይጎብኘን ሌላው ሁሉ ይቅር እግዚአብሔር ብቻ ይጎብኘን። ይጎበኘናል።" Robel solomon

"በእናንተ መካከል ማንም ስራፈት አይሁን፥ ስራፈትነት የእጦት እናት ነው።" (የአንጾኪያው ኢግናጢየስ፥ ለጠርሴስ ቅዱሳን በጻፈው ደብዳቤ የተናገረው፥ ምዕራፍ 9 ላይ ተመልከት) "Let no one among you be idle; for idleness is the mother of want." (Ignatius of Antioch, In his epistle to the Tarsians, see on chapter 9) የጥንት የቤተ ክርስቲያን አባቶች በቅዱሳን ማህበር መካከል ስራፈትነት እንዳይነግስ ሰራተኝነትን ያበረታቱ ነበር። በዚህም በመካከላቸው እርስ በእርስ ያላቸውን እንዲከፋፈሉ በማድረግ ክርስቲያናዊ ህብረትን አጎልብቱዋል። ለሌላው የሚቆረስ ነገር የሚኖርህ በቅድሚያ ሰራተኛ ስትሆን ጭምር ነው። ተነስተ ስራ፥ ስንፍናን አሶግድ። |ከ Eyosiyas Eyoael የfb ግድግዳ ላይ የተወሰደ|

"ኃጢአት አሸፍቶት ጫካ የገባውን ጸጋውን ተገፎ የተራቆተውን ወዳለበት ሄዶ ድምፁን ያሰማና ዳግም ያቆመዋል ያለባብስና ፍቅር ነው እግዚአብሔር ፍቅር ነው"

የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ጽነት ራስን ማታለል እና መሸወድ ነው። በኀልዩ፣ በነቢብና በገቢር (በአስተሳሰብ፣ በንግግር እና በሥራ)፣ ራሳችንን ፍጹም ጸዐዳ አድርገን እንቈጥራለን። በእግዚአብሔር ፊት ወድቀን፣ ኀጢአታችንን መናዘዝ በሚገቡን ዕልፍ ጒዳዮች፣ ዐመፃችንን መሸምጠጥ፣ ራሳችንን ማጽደቅ እና ከንቱ ውዳሴን መፈለግ ይጣፍጠናል። አነሣሽ ምክንያታችንን (our motive)፣ እኛ ራሳችን በትክክል የምናውቀው አይመስለኝም። ራስን ማታለል ከሰው ልጅ ጋራ ዐብሮ የሚኖር ፈተና ይመስላል። መንገዳችንን የኋሊት ስንቃኘው፣ ምንም እንኳ ትክክል ያልሆነ አነሣሽ ምክንያት ቢኖረንም፣ ለእኛ ግን ንጹሕ መስሎ ይታየናል። ራስን መፈተሽ በጎ ቢሆንም፣ በራስ ከመታለል ጨርሶ የሚያድነን አይመስለኝም። “ራሴን፣ አነሣሽ ምክንያቴን ፈትሻለሁና ንጹሕ ነኝ።” የሚለው ምክንያት፣ ራስን ከማታለያ ዘዴዎች መኻል አንዱ ነው። መፍትሒው ምንድን ነው? እኛ ልንደርስበት በማይቻለን ጥልቀት ዘልቆ ልብን በሚመረምር፣ ትክክለኛ አነሣሽ ምክንያቶቻችንን ጠንቅቆ በሚያውቅ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችንን ማስጣት። ልባችንን ወደ ትክክለኛ መንገድ ለሚያቀና ለእርሱ ብቻ ዐደራ መስጠት። ክርስቲያን አወል

"የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ጽነት ራስን ማታለል እና መሸወድ ነው። በኀልዩ፣ በነቢብና በገቢር (በአስተሳሰብ፣ በንግግር እና በሥራ)፣ ራሳችንን ፍጹም ጸዐዳ አድርገን እንቈጥራለን። በእግዚአብሔር ፊት ወድቀን፣ ኀጢአታችንን መናዘዝ በሚገቡን ዕልፍ ጒዳዮች፣ ዐመፃችንን መሸምጠጥ፣ ራሳችንን ማጽደቅ እና ከንቱ ውዳሴን መፈለግ ይጣፍጠናል። አነሣሽ ምክንያታችንን (our motive)፣ እኛ ራሳችን በትክክል የምናውቀው አይመስለኝም። ራስን ማታለል ከሰው ልጅ ጋራ ዐብሮ የሚኖር ፈተና ይመስላል። መንገዳችንን የኋሊት ስንቃኘው፣ ምንም እንኳ ትክክል ያልሆነ አነሣሽ ምክንያት ቢኖረንም፣ ለእኛ ግን ንጹሕ መስሎ ይታየናል። ራስን መፈተሽ በጎ ቢሆንም፣ በራስ ከመታለል ጨርሶ የሚያድነን አይመስለኝም። “ራሴን፣ አነሣሽ ምክንያቴን ፈትሻለሁና ንጹሕ ነኝ።” የሚለው ምክንያት፣ ራስን ከማታለያ ዘዴዎች መኻል አንዱ ነው። መፍትሒው ምንድን ነው? እኛ ልንደርስበት በማይቻለን ጥልቀት ዘልቆ ልብን በሚመረምር፣ ትክክለኛ አነሣሽ ምክንያቶቻችንን ጠንቅቆ በሚያውቅ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችንን ማስጣት። ልባችንን ወደ ትክክለኛ መንገድ ለሚያቀና ለእርሱ ብቻ ዐደራ መስጠት።" Christian awel