en
Feedback
Warka Times

Warka Times

Open in Telegram

Warka Times is a multi-platform bi-lingual global online media service where credibility is a priority. We will keep you both informed and entertained. The infotainment presented on WT comes from wide variety of sources. FB 👉fb.com/warkatimesofficial

Show more
4 899
Subscribers
+124 hours
-177 days
-7130 days
Posts Archive
አርሚ 24 እና አርሚ 31 ወያኔ የምትመካባቸው አርሚዎች ነበሩ። ያው "ነበሩ" ነው ያልኩት   === ከጥቂት ቀናት በፊት እነዚህ የወያኔ "ምርጥ" አርሚዎች ከእነ ሴኩ ሃይል ጋር በመጣመር ጥቃት ለመክፈት በላሊበላ ገጥ ወደ አማራ ክልል ዘልቀው ትንኮሳ ፈፅመው ነበር። ወደ ገደለው ስገባ ...  ጥምዶ ለጀመረው ትንኮሳ በተሰጠው ግብረመልስ ሳቢያ ከክፍለጦር እስከ ቦጦሎኒ ድረስ የነበሩት የሁለቱም የወያኔ አርሚዎች አዛዦች አሁን የሉም።ከነሱ መካከል በህይወት የተረፈ ያለ አይመስልም። ከሞትና ከጉዳት የተረፈው የሁለቱም አርሚዎች ታጣቂ ደግሞ ወደ ጅማዶ ማርያም አፈግፍጎ እስከ ትናንት ድረስ እዛው ጅማዶ ማርያም ነበር። ታጣቂዎቹ ጅማዶ ማርያምን ጥለው ሌላ ማፈግፈግ ማድረጋቸውን ዛሬ ሰማሁኝ። #wlkayi

የጦርነት ስጋት እየጨመረ ሲመጣ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ መጣች፣ በልቶ ለማደር ጥቃቅን ዕቃዎችን ማዞር ጀመረች፣ ዕቃ የሚገዛት ሰው በምታስስበት በአንደኛው ክፉ ቀን ከሀገሪቱ ገዥዎቹ ጋር ተላተመች፣
የጦርነት ስጋት እየጨመረ ሲመጣ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ መጣች፣ በልቶ ለማደር ጥቃቅን ዕቃዎችን ማዞር ጀመረች፣ ዕቃ የሚገዛት ሰው በምታስስበት በአንደኛው ክፉ ቀን ከሀገሪቱ ገዥዎቹ ጋር ተላተመች፣ በስህትት ከተማ የገባች አንድ ወሬ የፖሊሲ ዩኒፎርም አጥልቃ መንገዷ ላይ ጠበቀቻት፣ የንግድ ፈቃድ ጠየቀቻት፣ በእግሯ እየዞረች ለምትሸጠው ነገር ነው የንግድ ፈቃድ የጠየቀቻት፣ እንደሌላት ገልጻላት ስታበቃ የምታዝንላት መስሏት ከትግራይ መምጣቷንና ዕቃ የምታዞረው ራሷን ለማገዝ መሆኑን ነገረቻት፣ የጠበቀችውን አዘኔታ አላገኝችም፣ ትግሬ መሆኗን ስታውቅ የበለጠ ጨከነችባት፣ ይህቺ ትንሽ ልጅ ንግግሯን የቋጨችው "ዘረኝነት ይቅር፣ ጥሩ አይደለም" በሚል ወሳኝ መልዕክት ነው፣ ይህን ቃል ከትግራይ ብሔር ተወላጆች አይሰማም፣ ከሷ ትውልድ መሰማቱ ተስፋ ሰጪ ነው፣ ይህቺን ምስኪን ልጅ ባገኛት የምነግራት ነገር ነበረኝ፣ እየገፋቻት ያለችው ኢትዮጵያ ወያኔ የፈጠራት ኢትዮጵያ መሆኔን አስረዳት ነበር፣ ወያኔ የሚባል የትግራይ እረኛ መንጋ በጸጉሩ ቁጥር ልክ የሚሆን ተባይ ተሸክሞ አዲስ አባባ ከመድረሱ በፊት የወርቅ ገበያ monopoly ተብሎ ሊገለጽ በሚቻል ደረጃ በትግራይ ተወላጆች እንደተያዘ፣ አንድ ትግሬ ወደ ፈለገው የሀገሪቱ ክፍል ገብቶ ቢሰራ "እንኳን ደህና መጣህ" እንጂ ለምን መጣህ እንደማይባል አሳውቃት ነበር፣ ዘርና ኃይማኖት ሳትለይ፣ እንደሷ የተቸገሩ ታዳጊዎችን ሰብስባ እንደ እናት የምታሳድግ፣ የምታስተምር፣ የምትኩልና የምትድር፣ አበበች ጎበና የምትባል የኦሮሞ ሴት እንደነበረች ልነግራት እወድ ነበር፣ ከጉሮሮዋ ላይ የነጠቀቻት ወያኔ የፈጠራት ኦሮሞ መሆኗን አስረዳት ነበር፣ *** እንድታውቀው በሚል እንጂ የወያኔ ስህተት እሷን ይመለከታል ለማለት አይደለም፣ #ካሳአንበሳው

የሚጠሉትን አማርኛ ሊናገሩት አዲስ አበባ የገቡት ጀነራል .... " አማርኛ ለመማር ያጠፋሁት ጊዜ ይቆጨኛል" ያሉትና ጠ/ሚ አብይ አህመድን በማንቋሸሽና በመናቅ ትግራይ ሲኖር ሲሳደቡ የነበሩት ሜጀር
የሚጠሉትን አማርኛ ሊናገሩት አዲስ አበባ የገቡት ጀነራል .... " አማርኛ ለመማር ያጠፋሁት ጊዜ ይቆጨኛል" ያሉትና ጠ/ሚ አብይ አህመድን በማንቋሸሽና በመናቅ ትግራይ ሲኖር ሲሳደቡ የነበሩት ሜጀር ጄኔራል ተክለብርሃን ወልደአረጋይ (ጄኔራል ሳንቲም) "ወደ አዲስ ጦርነት መግባት አልፈልግም" በሚል ከህውሃት አምልጠው አዲስ አበባ ገቡ " የሚል ወሬ አየሁ። እርግጥ ነው አዲስ አበባ ከገቡኮ ቆይተዋል የሚሉ ቢኖሩም ....ብቻ ጉድ ነው። .....የድሃ ልጅ ሲያስጨርሱ ኖረው ወደ አ.አ ገብተው ጠላቴ ያሉት አማራ እና የአገሪቱ መሪ ጋር ሲገናኙ ያስገርማል።... ዶ/ር አብይ ቻይ ነው። ጀነራሉ ከእንግዲህ የአዲስ አበባ ሰው ጋር በሚጠሉት አማርኛ እያወሩ ይኖራሉ ። ንዴት እንዳይደፋቸው ሰጋሁ 😜

ወፍ እና ድሮን 😂 😂 “ቅድም ተኩስ መሰማቴን ነግሬያችሁ ነበር።አሁን አጣርቼዋለሁ።መለስ ፋውንዴሽን አይናለም አካባቢ ሆነው ነው የተኮሱት። ዙ-23 ነው 2 ጊዜ የተኮሱት። ወፍ አይተው ነው የተኮሱት” ... ድሮን መስላቸው ነው

Expelicitly and implicitly, Opdo-PP, Jawar Mohammed, OMN, Kush Media . .have been preaching hatred and calling an attack on t
+1
Expelicitly and implicitly, Opdo-PP, Jawar Mohammed, OMN, Kush Media . .have been preaching hatred and calling an attack on the Amhara people in Oromiya, particularly in Wollega. And now with in few days, hundreds of Amharas were killed, thousands displaced, churches and houses were burned....As you can see in these pics, these criminals were recording and posting their crime. Via Abenezer B. Yisihak #AmharaGenocide

ድምፃዊው *** አባትህ ፣ ቤተሰብህ ፣ ጉረቤት ፣ አስተማ ማሪ መምህርህ እኝህ ሰው ቢሆኑ አሁን ላይ እየሰሩ ባሉት ስራ ብዙ ቢባል ሊሰማህ / ሽ /የሚችለው ምን ይሆን ? በኢትዮጵያ ባሉበት የስራ ኃ
ድምፃዊው *** አባትህ ፣ ቤተሰብህ ፣ ጉረቤት ፣ አስተማ ማሪ መምህርህ እኝህ ሰው ቢሆኑ አሁን ላይ እየሰሩ ባሉት ስራ ብዙ ቢባል ሊሰማህ / ሽ /የሚችለው ምን ይሆን ? በኢትዮጵያ ባሉበት የስራ ኃላፊነት ይዘውት በነበረው የስልጣን ዘመን ለቀጣይ ኑሮአቸው ብዙ ማድረግ ይችሉ ነበር ነገር ግን የስራ ክቡርነትን ስለተረዱ በስልጣን ዘመናቸው ህሊናቸው መልካም በመሆኑ ዛሬ ላን ሳይሰጉ ስራን ሲሰሩ ስናይልናከብራቸው ልናመሰግናቸው ይገባል ። ለሌሎች ምሳሌ በመሆናቸው ከልብ ብንኮራባቸው ብሎም መልካም ብንመኝላቸው ምን ይጎልብናል ። ደግሞ በጥሩ አቋም ላይሽንቅጥ ብለው ከማየት በላይ ምን አለ ። ከኝህ ታላቅ ሰው የምንማር እንማር እላለው ። የተከበሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በባሉበት እግዚአብሔርዓምላክ ጤናና ዕድሜን አብዝቶ ይስጦት ሰላም ከርሶጋ ይሁን ጌታቸው ጋዲሣ ሰላም ለሁላችን ይሁን።

ጃዋር ቅኔውን ጨርሶ ቀረርቶ ጀምሯል። የጎነጎናቸው ሴራዎች ሲጨናገፉበት፥ የቋጠራቸው የውሸት ድሪቶዎች ሲፈቱበት፥ ምክንያት ያላቸው ሲመክኑበት፥ ለራሱ አምኖ ሌላውን ለማደናገር የበተናቸው ፌክ መረጃዎች ሲከሽፉበት አካኪ ዘራፍ ዓይነት ጨዋታ ጀምሯል። ፋኖ ላይ ሀሰተኛ ዶሴ አዘጋጅቶ 'እንተያያታለን' እያለ ነው። ጃዋር ነገሮች መለወጣቸውን ልብ ያለው አይመስልም። የትላንቱ ዜማ ዛሬ ቅኔው ተቀይሯል። ትላንት ከቤቱ ቁጭ ብሎ ሞቱን ሲጨልጥ የነበረው ህዝብ 'ዝም ብዬ አልሞትም' ከሚል መራር ውሳኔ ላይ ደርሶ ራሱን ለማዳን ታጥቋል። ዝም ብሎ ወደ ሞት ግዞት የሚነዳ ህዝብ አሁን የለም። እኛም አውቀናል ጉድጓድ ምሰናል' የሚል ምላሽ እየሰጠ ነው። ጃዋር ወደ ቀልቡ ቢመለስ ከማንም በላይ ተጠቃሚው እሱ ነው። የትላንት ጥፋቱን በይቅርታ ሊያሽረው የሚያስችለውን እድል በተደጋጋሚ አግኝቷል። ''አልጸጸትም'' በተሰኘው ዳጎስ ያለ መጽሀፉ የይቅርታን ጸጋ ያቆሽሸ ቢሆንም አሁንም የጸጸት እድል ከደጃፉ ቆሟል። ሌላ ዙር ሴራ መጎንጎን አደገኛ ነው። ተጨማሪ ዕልቂት መደገስ ለማንም አይበጅም። ሰከን ማለት ጥሩ ነው። ጊዜው ተቀይሯል። ሰዎች ቆርጠዋል። ጃዋር ተረጋጋ። ገና ወጣት ነህ። ብዙ ይጠበቅብሃል። የሰላም ወኪል እንጂ የሞት አዋጅ ነጋሪ ከመሆን ራስህ ቆጥብ። ከማንም በላይ የሚጠቅመው አንተን ነውና። ወንድማዊ ምክሬ ነው።

በነገራችን ላይ፣ ይህ ቪዲዮ የተቀረፀው የሸረሪና የመልሶ ማጥቃት ኦፕሬሽን በተካሄደ በነጋታው ነው። “ሸረሪና ሰሞኑን ነው እንዴ የተያዘው?” እንዳይባል ግልጽ ለማድረግ ያህል ነው። ህወሓት ለ4 ዓመታት ያደራጀውን የምሽግና የመሳሪያ ክምችት ገምግሞ “አሁን ዝግጁ ነኝ” በሚል፤ ትንኮሳ በፈጸመ በ40 ደቂቃ ውስጥ ነበር በግንባሩ የነበረው ዝግጅት እንዳልነበር የተደረገው። በቦታው የተያዘውን የመሳሪያ ክምችትና ዓይነት ላስተዋለ ደግሞ ከጀርባ የብዙ ኃይሎች እጅ እንዳለበት ለመረዳት አይከብድም። ጦርነት በፍጹም የሚመከር ባይሆንም፣ ራስን መከላከል ግን ተፈጥሯዊ መብት ነው። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትም ሊከበር ይገባል። የሰው ልጅ ከጦርነት ጋር ሙሉ በሙሉ ሊለያይ ስላልቻለ፣ ጦርነትን ለማስቀረት ብቸኛው አማራጭ ለጦርነት ሁልጊዜ ዝግጁ ሆኖ መገኘት ነው። ✊

ሺሻው አይቀር ሱረቱ አይቀር ሃሽሹ አይቀር ሁሉንም ዓይነት ጭሳጭሶችን በመሸታ ቤትህ ምሽቱን ስታስጨስ ከርመህ በጠዋቱ ተነስተህ ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ስፖርት ቢሮ ጋር የ45 ሚሊዮን ብር የስፖርት ማስታወቂያ sponsorship ስራዎችን ስትፈራረም የምትጨፍረው ጭፈራ ይህንን ይመስላል ኢትዮጵያዊው ፓብሎስ ኢስኮባር ይመችዎት አባቴ በርስዎ መጀን ብለናል።

"የጨረቃ ቢሮ" የብልፅግና ደጋፊ እንደሆነ የሚነገርለት አቤ ቶክቾው አዲስ የአበባ የሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ቢሮ በህገወጥ መንገድ የተቀመጠ "የጨረቃ ቢሮ" ነው ብሎታል። ጥሩ ምስክርነት ነው። ምክንያ
"የጨረቃ ቢሮ" የብልፅግና ደጋፊ እንደሆነ የሚነገርለት አቤ ቶክቾው አዲስ የአበባ የሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ቢሮ በህገወጥ መንገድ የተቀመጠ "የጨረቃ ቢሮ" ነው ብሎታል። ጥሩ ምስክርነት ነው። ምክንያቱ ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ህገ መንግስትም የኦሮሚያን መቀመጫ ናዝሬት እንደሆነ ነው የሚገልፀው። አዲስ አበባ መቀመጫችን ነው ያሉት በህገወጥ መንገድ ነው። እናም አፅድቁልን የሚሉት የጨረቃ ቢሮ ነው ይላል ደጋፊያቸው። በዚህ ጉዳይ እውነቱን ነው። ምስኪኖች የሰሩትን ኮንዶሚኒዬም ሁሉ የወረሰ ኃይል በህገወጥ መንገድ የተቀመጠበትን ከተማ ነው ጭራሽ የእኔ ነው የሚለው።

በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተሳታፊዎች ወደ አዳራሽ እንዳይገቡ ታገዱ ​ በዛሬው ዕለት ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን የምክክር መድረክ ላይ የተሳተፉ ተወካዮች ቅሬታቸውን ለማቅረብ ወደ ኮንቬንሽን ማዕከል ለመግባት ሲሞክሩ በፌደራል ፖሊስና በብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አባላት መታገዳቸው ተገለጸ። ​እንደ ምንጮች ገለጻ፣ ተመካካሪዎች በወሰኑት መሠረት ቅሬታቸውን ለማቅረብ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ቢሰበሰቡም፣ ወደ ኮንቬንሽን ማዕከል የስብሰባ አዳራሽ ግቢ እንዳይገቡ ከተደረጉ በኋላ በዛቻና በማስፈራራት ጭምር ወደ ግቢው እንዳይገቡ መከልከላቸው ተጠቅሷል። ​ይህ እገዳ ሊጣል የቻለው ትላንትናው ዕለት በብልጽግና ፓርቲ በኩል የተላለፈውን የ94 ፐርሰንት የድምፅ ውሳኔ በመሻር፣ በአዲስ አበባን አሳልፎ ለመስጠት የኦሮሞ ብልጽግና ጥቅምን ለማስከበር አዳዲስ አንቀጾችን ለማካተት የተወሰነውን የብልጽግና ውሳኔ ተከትሎ የተነሳውን ቅሬታ ለማቅረብ ሲሄዱ እንደሆነ ታውቋል።

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalDialogue🇪🇹 አከራካሪው የአዲስ አበባ ህጋዊ ጉዳይ፥ የአዘጋጅ ቡድኑ ቃለጉባዔ ትናንት ከተነበበ በኋላ ቅሬታ ቀርቦበትበክልል ምክር ቤት እንዲወሰን ዛሬ ኮሚቴ ተቋቋመበት። ተመካካ
+1
#NationalDialogue🇪🇹 አከራካሪው የአዲስ አበባ ህጋዊ ጉዳይ፥ የአዘጋጅ ቡድኑ ቃለጉባዔ ትናንት ከተነበበ በኋላ ቅሬታ ቀርቦበትበክልል ምክር ቤት እንዲወሰን ዛሬ ኮሚቴ ተቋቋመበት። ተመካካሪዎችን እያከራከረ የቆየውን የአዲስ አበባ ጉዳይ ጭምር ያካተተ የምክረ ሀሳብ ቃለጉባዔ ለተመካካሪዎች ትናንት የተነበበ ሲሆን፤ ዛሬ ለ4ሺሕው ጉባያተኞች ተነቦ የመረሻው ሰነድ ይጠናቀቃል ቢባልም፣ በአዲስ አበባ ጉዳይ ቅሬታ በመቅረቡ ክርክሩ ቀጥሏል። ቅሬታውን ተከትሎ የከተማዋን ጉዳይ የሚወስን የክልል ምክር ቤት ጉባዔ እንዲቋቋም የተወሰነ ሲሆን፣ ይህ የሆነው የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች የትናንቱ ቃለ ጉባዔ ከተነበበ በኋላ ለኮሚሽኑ ቅሬታ በማስገባታቸው መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተመካካሪዎች ተረድቷል። ትናንት ለ8ቱም ቡድኖች ከተነበበው የ8ቱ አጀንዳዎች የአዘጋጁ ቡድኑ ቃለጉባዔ የአዲስ አበባን ህጋዊ ጉዳይ በተመለከተ ከተማዋ ተጠሪነቷ የፌዴራል ይሁን የሚለው ተመካካሪዎችን አስማምቶ፣ ከተማዋ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ እንድትሆን ህገመንግስቱ እውቅና ይስጥ" በሚል ሲያከራክር የሰነበተው ጉዳይ ግን አማራጮች ቀርበውለት ነበር። አብዛኛውን ተመካካሪዎች ስላላስማሙ ስለከተማዋ በአማራጭ የቀረቡት ሁለት ሀሳቦች"፣ ሁሉም ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን መምረጥ እንዲችሉ" በሕግ ይደንገግ እና በአንቀጽ 49/5 "አዲስ አበባ የኦሮሚያ መቀመጫ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ" በከተማዋና በክልሉ መካከል ያለው ግንኙነት በሕግ ይደንገግ የሚሉ ናቸው። ከዚያ በኋላ ምን ተፈጠረ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተሳታፊዎች እንደተረዳው፣ "አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫም እንድትሆን በሕገ መንግስቱ እውቅና ይሰጥ" የሚለው ምክረ ሀሳብ አማራጭ ሀሳቦች ቀርበውለት ሳይሆን "ይፈቀድ" ወይም "አይፈቀድ" በሚል እንዲወሰን ለኮሚሽኑ ቅሬታ አቅርበዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአንድ የምክክሩ ተሳታፊ እንደተረዳው፣ ወደ "350" የሚሆኑ ተመካካሪዎች የአዲስ አበባን ጉዳይ በተመለከተ ትናንት በቀረበው ቃለጉባዔ "አንስማማም" ብለዋል። ይህን ተከትሎ ኮሚሽኑ ዛሬ የክልል ምክር ቤት ጉባዔ ጠርቶ ባደረገው ገለጻ፣ "እዚህ የመጣው ለውሳኔ ተቸግረን ነው። 'አዲስ አበባ የኦሮሚያ መቀመጫ እንድትሆን ህገ መንግስቱ እውቅና ይስጥ ወይስ አይስጥ'" ለሚለው የክልል ምክር ቤት ጉባዔ ውሳኔ እንዲሰጥ መጠየቁን በዚሁ ውይይት ከነበሩ ተሳታፊ ገለጻ ተረድተናል። ይህንንም ዛሬ ምሽቱን አጠናቆ ነገ ውሳኔውን ለኮሚሽኑ እንዲያቀርብ ማሳሰቢያ ተሰጥቶ፣ ምሽቱን ኮሚቴ ተዋቅሯል። በውይይቱ የሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች፣ የክልል ምክር ቤት ፕሬዚዳንቶች፣ የፓርቲ ካውንስልና ሌሎችም ነበሩበት። ከእነዚህ መካከል ጉዳዩ "መንግስታዊ" እንዳይሆን ወደ ተወያዮች ተመልሶ ቢመከርበት የሚል ሀሳብ ያቀረቡ መኖራቸው ተመልክቷል። በሌላ በኩል፣ ከዚያ በፊት በነበሩ ቡድኖች ሲያከራክር የቆየው፣ በኋላም 500 ሰዎችን በያዘው ቡድን በሰፊው ያከራከረው፣ ከዚያም 120 አባላት ባሉት ምክረ ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን በቀረበው ቃለጉባዔ የአዲስ አበባ ጉዳይ በስምምነትና አማራጭ ሀሳብ ቀርቦለት እያለ፣ እንደገና ዛሬ ለውሳኔ መቅረቡን የተቃወሙ ተመካካሪዎች ተስተውለዋል። ይህን የተቃወሙ ተመካካሪዎች ምክክሩን "ረግጠው" እስከመውጣት ውሳኔ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ሲያስጠነቅቁ የተስተዋሉ ሲሆን፣ በኮንቬንሽን ማዕከል የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ወዳሉበት ጊዚያዊ ቢሮ ምሽቱን ቅሬታ ለማቅረብ ማምራታቸውም ተመልክቷል። በ120 የ8ቱም አጀንዳ አዘጋጆች የተዘጋጀውና ትናንት ለስምንቱም ቡድኖች የተነበበው ቃለጉባዔ ዛሬ ለ4ሺሕው ጉባያተኞች ተነቦ ይጸድቃል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ለጉባያተኞቹ ሳይነበብ ቀርቷል። ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ባሳወቀው መሰረት፣ ቃለጉባዔው ባለፉት ቀናት ለ4ሺሕው ጉባያተኞች ተነቦ ይጠናቀቃል ብሎ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬም ለሦስተኛ ጊዜ ሳይነበብ ቀርቶ ጉባያተኞች ሲጉላሉ ውለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

የደብረፅዮን ፀረ ድሮን ምላስ ላይ ብቻ ቀረ?! ዛሬም ከበድ ያለ ምት አስተናግደዋል።

የcollateral damage ሰለባዎቹ በመጋዘኑ አካባቢ ሰፍረው የነበሩ የአርሚ 92 ታጣቂዎች ናቸው።

ከኤርትራ ተሻግሮ መቀሌ የተራገፈው የጦር መሳሪያ ዛሬ ጧት የድሮን ቁርስ ሆኗል። ተያያዥ ከፍተኛ ጉዳትም collateral damage አድርሷል 😂

Repost from Meseret Media
#ዜናመሠረት በአማራ ክልል ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ ታስረው የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞችን ከማይካድራ ጭፍጨፋ ፍርደኞች ጋር በይቅርታ አንድ ላይ ለመፍታት መታቀዱ ተቃውሞ አስነሳ "እጅግ ዘግናኝ የሆነ
#ዜናመሠረት በአማራ ክልል ካለው ግጭት ጋር በተያያዘ ታስረው የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞችን ከማይካድራ ጭፍጨፋ ፍርደኞች ጋር በይቅርታ አንድ ላይ ለመፍታት መታቀዱ ተቃውሞ አስነሳ "እጅግ ዘግናኝ የሆነ ግድያና ጭፍጨፋ ፈጽመው ፍርድ ካገኙ ግለሰቦች ጋር እኩል በማሰለፍ በሕዝብ ዘንድ በተመሳሳይ እይታ እንዲታዩና የወንጀሉ ተካፋይ ተደርገው እንዲሳሉ ሆን ተብሎ የተሸረበ ሴራ ነው" ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/d8c

እነ ገቢሳ፦ አድምጡ! ከተማችን አዲስ አበባን የብሄር ንብረት እንድትሆን በፍፁም አንፈልግም የከተማው ነዋሪ ስለከተማው እጣ ፈንታ ራሱ መወሰን ይችላል። ከተማው የተሰራው ኦሮሚያ አማራ የሚባል ክልልሏች በኢሀዲግ ከመፈጠራቸው ረጅም ግዜ በፊት ነው። ኒውዬርክ ላይ ከዩጋንዳ የመጣ ሰው ከንቲባ ይሆናል እዚህ ደግሞ ሰግሪጌሸን እና አፓርታይድ ስርአት ለማስረፅ ሰው በዘሩ ፕሪቪሌጅ ለማድረግ ትጋጋጣላችሁ!

While ordinary Ethiopians wrestle with relentless inflation, a so-called "Dada Cadre", Sandokan Debebe, hailed as Abiy's poli
While ordinary Ethiopians wrestle with relentless inflation, a so-called "Dada Cadre", Sandokan Debebe, hailed as Abiy's political offspring, enjoys a gilded path. He secured a plush home in Maryland, whisked away his fortune from Ethiopia, and stepped straight into a coveted diplomatic post at Ethiopia's UN Office. These days, Arat Kilo appears more interested in orchestrating lavish escapes than shaping foreign policy. By the way, who was it who said "all successful reformers eventually wear the robes of the tyrant they deposed"

"ቀይ ባሕር ላይ ጠብቁን እንዳላሉ፣ የቀበና ወንዝ ነፃ አውጭ ሆነው ተገኙ" ዳምጠው ተሰማ አዲስ አበባን ካልዋጥን ለሚሉት ከፃፈው