en
Feedback
etrade.gov.et

etrade.gov.et

Open in Telegram

ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel etrade.gov.et

Channel etrade.gov.et (@etrade_gov_et) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 715 subscribers, ranking 6 225 in the Business category and 1 835 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 715 subscribers.

According to the latest data from 23 July, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 73 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ቻናል በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና በክልል ንግድ ቢሮዎች ተጠቃሚ ደንበኞች ስለ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መረጃ ለመለዋወጥ ይረዳ ዘንድ የተፈጠረ ነው:: This channel was created to help users of the Ministry of Trade & Regional Integration and Trade Bureaus exchange info about OTRS...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 July, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Business category.

16 715
Subscribers
No data24 hours
+367 days
+7330 days
Posts Archive
ውድ ደንበኞቻችን ከሐምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች መሰጠታቸው ይታወሳል። ቢሆንም በረካታ ባለጉዳዮች አገልግሎት ጠይቃችሁ አገልግሎቱን ያላጠናቀቃችሁ በሙሉ፣ የመክፈያ ኮድ መሰረት በአስቸኳይ የአገልግሎት ክፍያ በመጸም የምስክር ወረቀታችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ Dear customers, since July 1, 2015 E.C, many business registration and license services have been provided. However, we urge all those who have requested service and not completed the service, to collect your certificate by paying the service fee immediately according to the payment code. =============================================================

ነጋዴዎች ለሚሸጡት አገልግሎት እና እቃ የዋጋ ዝርዝር የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው:: ============================== አዲስ አበባ 20/02/2016ዓ.ም(ንቀትሚ) የንግድ ተቋማት ለሚሸጡት አገልግሎትና የንግድ ዕቃዎች የዋጋ ዝርዝር የመለጠፍና የማሳወቅ ግዴታ እንዳለባቸው በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሸማቾች መብትና ጥበቃ ዴስክ ሀላፊ አቶ ሰይፉ አየለ ገለጹ፡፡ የእቃዎችን ዝርዘርና ዋጋ መለጠፍ ለግዥው ግንፅነትን የመፍጠርና አድሏዊነትን ይቀንሳል ያሉት የሸማቾች መብትና ጥበቃ ዴስክ ኃላፊ አቶ ሰይፉ አየለ የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ 813/2006 ክፍል ሶስት ከአንቀጽ 15 እስከ 18 የንግዱ ማህበረሰብ ለሚሰጡ አገልግሎቶችና ለሚሸጡ እቃዎች የዋጋ ዝርዝር የመለጠፍ ግደታ እንዳለበት መደንገጉን አብራርተዋል፡፡ የገዥዎችን የመከራከር አቅም ታሳቢ በማድረግ አንድን እቃ በተለያየ ዋጋ መሸጥ አድሏዊነት ነው ያሉት አቶ ሰይፉ ዋጋ መለጠፍ፣ የድርጅት ስም የማሳወቅ፣የንግድ ዕቃዎች መግለጫ ማቅረብ፣ ደረሰኝ መቁረጥ የነጋዴዎች ግደታ ሲሆኑ በሌላ በኩል እነዚህን የማግኘት የሸማቹ ማህበረሰብ መብት እንዴሆነም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የሸማቾች ጥበቃ መብት በማይተግብሩ ነጋዴዎች ላይ በገንዘብ ከ5ሺ እስከ 50ሺ ብር እና ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል እንደሆነም አቶ ሰይፉ ተናግረዋል፡፡ የሸማቹን ማህበረሰብ የግንዛቤ ለማዳበር ለሚመለከታቸው የክልል ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት፣ ከሚዲያዎች ጋራ በጋራ የመስራት፣ ከህብረተሰቡ ጋር የገፅ ለገፅ ውይይት በማድረግ እንዲሁም በተቋሙ የፌስ ቡክ ገፅ እና በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤውን ለማስፋት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

በአዳማ ከተማ 9127 የንግድ አገልግሎቶች በኦንላይን ተሰጥተዋል:: ================= አዲስ አበባ 10/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) በአዳማ ከተማ አስተዳደር ከሐምሌ1/2015 እስከ መስከረም/2016ዓ.ም መጨረሻ ድረስ 9127 የንግድ አገልግሎቶች በኦንላይን መሰጠቱን የከተማው ንግድ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ ሀገራዊ የንግድ ስርዓቱን ለማዘመንና አገልግሎት አሰጣጡን ለተገልጋዩ ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ተከትሎ ከሐምሌ1/2015 ጀምሮ በሀገር ደረጃ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች በኦንላይን እንዲሰጡ መደረጉ ይታወሳል፡፡ በአዳማ ከተማ አስተዳደር እስከ መስከረም 30/2016 ዓ.ም 9127 አገልግሎቶችን በኦንላይን መስጠቱን የአዳማ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጢሎ ዱግዳ ተናግረዋል፡፡ በኦንላይን የተሰጠው አገልግሎትም የደንበኞችን ጊዜ፣ ወጪና እንግልትን ያስቀረ መሆኑን ሀላፊው ጠቁመዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ኢትዮጵያ ለንግድ ስራ አመቺ ከሆኑ 10 አፍሪካ ሀገራት ውስጥ ቀዳሚዋ ሆናለች። ======================= አዲስ አበባ 08/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ቢዝነስ ኢንሳይደር ባወጣው ዘገባ አ
ኢትዮጵያ ለንግድ ስራ አመቺ ከሆኑ 10 አፍሪካ ሀገራት ውስጥ ቀዳሚዋ ሆናለች። ======================= አዲስ አበባ 08/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ቢዝነስ ኢንሳይደር ባወጣው ዘገባ አፍሪካ በአለም ፈጣን  ኢኮኖሚ እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ተርታ የምትመደብ ስትሆን እ.ኤ.አ 2023 ለንግድ ስራ ምቹ የሆኑትን ሀገራት ዝርዝር ሲያወጣ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ሀገር መሆኗን አስታውቋል። ሀገራቱ ከተገመገሙበት ጉዳዮች ውስጥ ንግድን ከብሄራዊ ድንበሮች አልፎ ለአዳዲስ ገብያዎች እና ኢንቨስትመንት የከፈቱትን እድል ተጠቃሽ ምክንያት አድርጎ አስቀምጦታል።                  ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

photo content

ኢትዮጵያ ለንግድ ስራ አመቺ ከሆኑ 10 አፍሪካ ሀገራት ውስጥ ቀዳሚዋ ሆናለች። ======================= አዲስ አበባ 08/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ቢዝነስ ኢንሳይደር ባወጣው ዘገባ አፍሪካ በአለም ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ተርታ የምትመደብ ስትሆን እ.ኤ.አ 2023 ለንግድ ስራ ምቹ የሆኑትን ሀገራት ዝርዝር ሲያወጣ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ሀገር መሆኗን አስታውቋል። ሀገራቱ ከተገመገሙበት ጉዳዮች ውስጥ ንግድን ከብሄራዊ ድንበሮች አልፎ ለአዳዲስ ገብያዎች እና ኢንቨስትመንት የከፈቱትን እድል ተጠቃሽ ምክንያት አድርጎ አስቀምጦታል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

/start

ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት መጀመሩ የተገልጋዮችን ቅሬታ ቀንሷል፡፡ ====================== አዲስ አበባ 02/02/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) ኦን ላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት መስጠት ከተጀመረ ወዲህ በተገልጋዮች ይቀርብ የነበረው ቅሬታ መቀነሱንና በንግዱ ማህበረሰብ ዘንድ መተማመን መፍጠሩን የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ከወረቀት ንክኪ ነፃ በመሆኑና አገልግሎት ሰጪው ከተገልጋዮች ጋር በአካል የሚገናኙበት ሁኔታን ስላስቀረ የተገልጋዮችን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ በመቀነሱ በተገልጋዮች ዘንድ ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ ቅሬታዎችን ያስቀረ ከመሆኑም ባሻገር በንግዱ ማህበረሰብ ዘንድ መተማመንን የፈጠረ መሆኑን አቶ ሙሃመድ ሐምዴ የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አስታውቀዋል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ኦንላይን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ከተጀመረበት ከሀምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም አንስቶ እስከ መስከረም 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ 16,311 የሚሆኑ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች በኦንላይ መሰጠቱ ተገልጿል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

ውድ ደንኞቻችን ኮኔክሽን ሰሞኑን ከነበረው አንጻር በእኛ በኩል ጥሩ መሆኑን ያሳያል። በእንተ ውድ ደንበኞችችን በኩል ያለውን ፍጥነት ለማረጋገጥ ይህን አስተያየት እንድትሞልን እንጠይቃለን
Anonymous voting

ስለ ጥራት፣ ደረጃ እና መስፈርት ምን ያህል ያውቃሉ? =============== አዲስ አበባ 25/1/2016ዓ.ም(ንቀትሚ) የጥራት ምንነት:- ፨ ጥራት በቀጥታ የተገለጸንና በተዘዋዋሪ የተመለከተን ፍላጎት የማሟላት ችሎታን የሚገልጽ የአንድ ምርት ወይም አገልግሎት አጠቃላይ ባህሪ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ምርት ወይም አገልግሎት ጥራቱን አሟልቷል የሚባለው የሚፈለገውን መስፈርት አሟልቶ ለታለመለት አላማ በብቃት ሲቀርብ ነው ፡፡ የደረጃ ምንነት:- ፨አንድ ምርት ወይም አገልግሎት ወይም ሂደት ለታለመለት ተገባር ተስማሚ መሆኑን ለማረጋገጥ መመሪያዎችን፤ዝርዝር ቴክኒካዊ መስፈርቶችን፣የቃላት ፍቺዎችን፣የአስተሻሸግ መለያን፣ አርማን፣ ስያሜን፣ የፍተሻ ዘዴዎችንና ሌሎች ተፈላጊ ሁኔታዎችን ለመግለጽ በሚመለከታቸው አካላት በስምምነት የሚዘጋጅና እውቅና ባለው አካል ፀድቆ ለጋራና ተደጋጋሚ ጠቀሜታ የሚውል ሰነድ ነው። የመስፈርት ምንነት፡- ፨የህብረተሰቡን ጤና ደህንነትና ጥቅም እንዲሁም የአካባቢ ደህንነትን፤ለማስጠበቅ ሥልጣን ባለው የመንግሥት አካል የተደነገጉ ሂደቶች፣ምርቶች ወይም አገልግሎቶች ማሟላት ያለባቸው ተፈላጊ ዝርዝር ሁኔታዎች ናቸው፡፡ የደረጃዎች አተገባበር በሁለት የሚከፈል ሲሆን ሀ/ በፈቃደኝነት የሚተገበር ደረጃዎች ፨ በምርቶችና አገልግሎቶች እንዲሁም ከአመራረቱ/ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ለተገናኙ ንድፎችና ሂደቶች ተፈላጊ በሆኑ መስፈርቶች ላይ ለመስማማት ፈቃደኛ በሆኑ የኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት ሲሆን ትግበራቸዉም በፈቃደኝነት ላይ ተመስርቶ ነዉ፡፡ ፨ እንደ መርህ ኢንዱስትሪዉ ባለቤት የሚሆንበት ለ/ በአስገዳጅነት የሚተገበር ደረጃዎች ሲሆን ፨ መንግስት በዋናነት ከህብረተሰቡ ጤንነት፣ከእንስሳትና ከአካባቢ ደህንነት ለማስጠበቅና ተያያዥነት ያላቸዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ለማስፈፀም ምርቶች ወይም አገልግሎቶች ተለይተው በህግ ማዕቀፍ ዉስጥ አካትቶ በህግ አስገዳጅነት እንድተገበሩ የሚያስገድድ ስርዓት ነው፡፡ ፨ እንዲህ ዓይነቶቹ አስገዳጅ ደረጃዎች የቴክኒክ ደንቦች በመባል ይታወቃሉ፡፡ ፨ መንግስት ብቻ በባለቤትነት የሚያስፈፅመዉ ፨ ምርት ወይም አገልግሎት በደረጃዉ ዉስጥ የተገለፁትን መስፈርቶች ማሙዋላቱ በፍተሻ ተረጋግጦ ሳይፈቀድ ለሸማቾች አይቀርብም፣ ማስተዋወቅም ክልክል ነዉ፡፡

ሠላም ውድ ድንበኞቻችን ፣ የገጠመንን ችግር የፈታን መሆኑን እያሳወቅን፣ ከበፊቱ የተሻላ ፍጥነት ስናገለግሎት በደስታ ነው።

ሠላም ውድ ድንበኞቻችን ትናንት ሲሰተማችን ወጣ ገባ ሲል በመዋሉ እና ዛሬ ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ ይቅርታ እየጠየቅን፣ የገጠመንን ቴክኒካል ችግር ለመፍታት ባለሙያዎቻችን ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ ። ችግሩን እስክንፈታ ድረስ በትግስት እንድትጠብቁን እንገልጻለን።

የነጋዴ ግዴታዎች ምንድን ናቸው? ================ አዲስ አበባ 21/01/2015ዓ.ም (ንቀትሚ) 1. የንግድ ዕቃዎቹንና የአገልግሎቶቹን ታክስ፣ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና ሌሎች ሕጋዊና ክፍያዎችን ያካተተ የዋጋ ዝርዝር በንግድ ቤቱ በግልፅ በሚታይ ቦታ የማመልከት ወይም በንግድ ዕቃዎቹ ላይ መለጠፍ (አንቀፅ 15)፤ 2. በሚሸጣቸው የንግድ ዕቃዎች ላይ መግለጫ የመለጠፍ ወይም በተለየ ወረቀት ላይ ጽፎ ለሸማቹ መስጠት (አንቀፅ 16)፤ 3. መግለጫው የዕቃውን ስም፣ የተሠራበትን ሀገር፣ ክብደቱን፣ ብዛቱን፣ ጥራቱን፣ ይዘቱን፣ አጠቃቀሙን፣ የአገልግሎት ማብቂያ ጊዜ …ወዘተ ያካትታል፤ (አንቀፅ 16/2 ሀ-ኀ) ለነጋዴ የተከለከሉ ድርጊቶች (አንቀጽ 22) 1. የንግድ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ስላላቸው ጥራት ወይም መጠን ወይም ብዛት ወይም ተቀባይነት ወይም ምንጭ ወይም ባህርይ ወይም ውሁድ ወይም ጥቅም የተሳሳተ መረጃ መስጠት(22/1)፤ 2. የንግድ ዕቃዎች ስለአዲስነታቸው ወይም ስለሞዴላቸው ወይም አገልግሎታቸው የቀነሰ ወይም የተለወጡ ወይም እንደገና የተሠሩ ወይም በአምራቹ እንዲሰበሰቡ የተባሉ ወይም ያገለገሉ ስለመሆናቸው በትክክል አለመግለጽ(22/2)፤ 3. የሌላውን ነጋዴ የንግድ ዕቃዎች በአሳሳች ሁኔታ መግለፅ(22/3)፤ 4. የንግድ ዕቃዎችና አገልግሎቶችን በማስታወቂያ እንደተነገረላቸው አለመሸጥ ወይም ማስታወቂያው የመጠን ውሱንነት መኖሩን ካልገለፀ በስተቀር ሸማቾች በሚፈልጉት መጠን ልክ አለመሸጥ (22/4)፤ 5. ስለዋጋ ቅናሽ ሀሰተኛ ወይም አሳሳች መረጃ ማስተላለፍ(22/5) 6. የሸማቹን መብት የሚጠብቅ ባልሆነ ምክንያት የንግድ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን አልሸጥም ማለት(22/12)፤ 7. የንግድ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን በንግድ መደብሩ ውስጥ ከተለጠፈው ዋጋ አስበልጦ መሸጥ(22/14)፤ 8. ከሽያጭ ጋር በተያያዘ የተገባ የዋስትና ግዴታን አለመወጣት(22/7)፤ 9. የንግድ ዕቃ የሚያስፈልገው ጥገና ወይም የሚተኩ ክፍሎች እንደማያስፈልጉት አድርጎ ማቅረብ(22/8) 10. የንግድ ዕቃዎች የተሠሩበትን ሀገር አሳስቶ መግለጽ(22/15)፤ 11. በሸማቾች መካከል ተገቢ ያልሆነ አድልዎ መፈጸም(22/16)፤ 12. ማንኛውንም አገልግሎት የመስጠት ሥራን በንግድ ሥራው ከሚታወቀው ደረጃ በታች ወይም ባልተሟላ ሁኔታ መስጠት922/9)፤ 13. በግብይት ወቅት ማንኛውንም የማጭበርበር ወይም የማደናገር ተግባር መፈፀም(22/11)፤ 14. ደረጃ የሚያስፈልጋቸውን የንግድ ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች ያለደረጃ ማህተም ለሽያጭ ማቅረብ (22/13)፤ 15. አንድን የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ለመሸጥ ሸማቹ ያልፈለገውን ሌላ የንግድ ዕቃ አብሮ እንዲገዛ ማስገደድ(22/17)፤ 16. ሕገ ወጥ በሆነ ማንኛውም የመለኪያ መሣሪያ መጠቀም(22/18)፤ 17. ለሰው ጤናና ደህንነት አደገኛ የሆነ፣ ምንጩ ያልታወቀ፣ የጥራት ደረጃው የወረደ፣ ወይም የተመረዘ፣ አገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈ ወይም ከባዕድ ነገሮች ጋር የተደባለቁ የንግድ ዕቃዎችን ለሽያጭ ማቅረብ ወይም መሸጥ(22/10)፤ 18. አንድ ሸማች አንድን የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት በመግዛቱ ወይም የገንዘብ መዋጮ በማድረጉ እና በሸማቹ አሻሻጭነት ከእሱ ቀጥሎ ሌሎች ሸማቾች የንግድ ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን የሚገዙ ወይም የገንዘብ መዋጮ የሚያደርጉ ከሆነ ወይም በሽያጭ ስልቱ ውስጥ የሚገቡ ከሆነ በሸማቾቹ ቁጥር ልክ ተጨማሪ የገንዘብ ወይም የዓይነት ጥቅም እንደሚያገኝ የሚገልጽ ፒራሚዳዊ የሽያጭ ስልት ተግባራዊ ማድረግ(22/6)፤ • ከላይ ከተጠቀሱት መብቶች ውስጥ ያልተከበረ ካለ ግብይቱን በፈጸሙበት አካባቢ ለመገኝ ንግድ ቢሮ ወይም ለፖሊስ በማቅረብ በሕግ ምላሽ እንዲሰጥዎ ያድርጉ፡፡ • በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ በተፈጸመ ግብይት በሸማቹ ላይ ለደረሰ ጉዳት የካሳ ትያቄ በፍትህ ሚኒስቴር የንግድ ውድድና የሸማቾች ጥበቃ ዳኝነት ችሎት ማቅረብ ይቻላል፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

በኦን ላይን ከአራት መቶ ሺ በላይ አገልግሎት መሰጠት ተችሏል። ========================= አዲስ አበባ 14/01/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሐምሌ 1/2
+1
በኦን ላይን ከአራት መቶ ሺ በላይ አገልግሎት መሰጠት ተችሏል። ========================= አዲስ አበባ 14/01/2016ዓ.ም (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሐምሌ 1/2015 እስከ መስከረም 8/2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ 401,830 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶችን በኦን ላይን መስጠቱን አስታወቀ። ሚኒስቴር መስራ ቤቱ ከሐምሌ1/2015 ዓ.ም ጀምሮ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጡን በሀገር አቀፍ ደረጃ በኦን ላይን ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህም ከፌደራል እስከ ክልል ባሉት የንግድ ተቋማትና መዋቅሮች 401,830 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በኦን ላይን ተሰቷል። በኦንላይን ከተሰጡ የአገልግሎት የንግድ ምዝገባ፣ አዲስ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት፣ የንግድ ስራ ፈቃድ ስረዛ፣ የንግድ ስም ማሻሻያ እና ሌሎችም የሚገኙበት ሲሆኑ አገልግሎቱ በኦን ላይን በመሰጠቱ የተገልጋዮችን እንግልት ማስቀረት፣ ወጪ እና ጊዜያቸውንም በመቆጠብ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ተችሏል። ተጨማሪ መረጃዎችን:- Email: fdremotri@gmail.com fdremotri@motri.gov.et facebook:- Ethiopianministryof tradeandregionalitegration For trade license : www.etrade.gov.et website: www.motri.gov.et telegram channel :https://t.me/motri_gov_et https://t.me/etrade_gov_et https://www.youtube.com/@ethiopian_ministry_of_trade

photo content

photo content